Blog

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያቋረጠችውን እርዳታ ልትጀምር መሆኗን ገለጸች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያቋረጠችውን እርዳታ ልትጀምር መሆኗን ገለጸች

የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ከመጪው ወር ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ የምግብ እርዳታ አጀምራለሁ ብሏል፡፡ የአሜሪካ  መንግስት የዓለም አቀፍ ልማት ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) ካሳለፍነው ሰኔ ወር ጀምሮ በምግብ እርዳታ ስርቆት ምክንያት እርዳታ መስጠቱን ማቆሙ ይታወሳል፡፡ በለጋሾች የተገዛ የምግብ እርዳታ ለገበያ መቅረቡና ወደ ውጪ አገራት ጭምር መላኩን የጠቀሰው የተራድኦ ድርጅቱ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የእርዳታ ስርጭቱን በተመለከተ ተከታታይ ውይይት ማድረጉን ገልጿል። በዚህም ባለፈው ወር በሀገሪቱ ለሚገኙ ስደተኞች የምግብ እርዳታ ማቅረብ የጀመረ ሲሆን ከመጪው ወር ጀምሮ ደግሞ በመላው ኢትዮጵያ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች እርዳታ ማቅረብ እንደሚጀምር ገልጿል። ኢትዮጵያ የምግብ ድጋፍ ስርጭት ስርአቷን በመሰረታዊነት የሚያስተካክል ስራ መከወኗንና ለጋሽ ድርጅቶች እርዳታው ለተገቢው አካል መድረሱን እንዲከታተሉ መስማማቷን ድርጅቱ አስታውቋል። ለጋሽ…
Read More
ስድስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ተገለጸ

ስድስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ተገለጸ

ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ከግማሽ በላይ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎችን እንደሚመድብ ገልጿል፡፡ ይሁንና ስድስት የመንግስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ አስታውቋል፡፡ የሬሚዲያል ተማሪዎችን ከማይቀበሉ ዩንቨርሲቲዎች መካከልም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ አርሲ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዪኒቨርሲቲዎች ናቸው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር እነዚህ ዩንቨርሲቲዎች ለምን የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ምክንያታቸውን አልጠቀሰም፡፡ በ2015 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺሕ 099 ተማሪዎች ውስጥ፤ 817 ሺሕ 838 ተማሪዎች ከ50 በመቶ በታች የሆነ ውጤት ማምጣታቸው ይታወሳል፡፡ የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ ከአጠቃላይ 845 ሺሕ 099 ተፈታኞች ውስጥ…
Read More
የሱዳን ጦር አዛዥ ጀነራል አልቡርሃን ለይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ

የሱዳን ጦር አዛዥ ጀነራል አልቡርሃን ለይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ

የሱዳን ሉአላዊ ምክርቤት ፕሬዝዳንትና የሀገሪቱ ጦር አዛዥ ጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን ለይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል። ጀነራል አልቡርሃን በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታና በሌሎች የሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ይወያያሉ ተብሏል። ሰባተኛ ወሩን የያዘው የሱዳን ጦር እና የፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ ጦርነት ከ9 ሺህ በላይ ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል። ከ5 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ ሰዎችን ያፈናቀለው ጦርነት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲቆም የሚደረገው ጥረትም ቀጥሏል። ሁለቱ ሃይሎች በሪያድ በተደጋጋሚ ለድርድር ቢቀመጡም እስካሁን ከስምምነት ላይ አልደረሱም። በአዲስ አበባም በቅርቡ በሱዳን የሽግግር መንግስት ለማቋቋም ያለመና ከ80 በላይ የሀገሪቱ የፖለቲካና ሲቪል ድርጅቶች የተሳተፉበት ምክክር መደረጉ አይዘነጋም። በካርቱም የሚገኘው ኤምባሲዋ በአየር የተደበደበባት ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት…
Read More
ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ጥምረትን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ተገለጸ

ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ጥምረትን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ተገለጸ

ከ24 ዓመት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን የኢኮኖሚ ትስስር ለማሳለጥ የተቋቋመው የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ ጥምረት በየጊዜው አዳዲስ አባላትን በመሳብ ላይ ይገኛል። ጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ከአንድ ዓመት በፊት ይህን ጥምረት ለመቀላቀል በይፋ መጠየቋ ይታወሳል። ጥምረቱም የመቋዲሾን ጥያቄ ለመመለስ ባለሙያዎቹን አሰማርቶ የተለያዩ ግምገማዎችን ሲያደርግ ቆይቶ ሶማሊያን ስምንተኛዋ አባል ሀገር አድርጎ እንደሚቀበል አስታውቋል። ዋና መቀመጫውን አሩሻ ታንዛኒያ ያደረገው ይህ የኢኮኖሚ ጥምረት በሚቀጥለው ሳምንት በሚያደርገው ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ሶማሊያን በይፋ በአባልነት እንደሚቀበል ገልጿል። የጥምረቱ ዋና ጸሀፊ ፒተር ማቱኪ በሞሮኮ ማራካሽ በተካሄደው የኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ እንዳሉት "ሶማሊያ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ አባል ትሆናለች" ብለዋል። ዋና ጸሀፊው አክለውም "የጥምረቱ ቀጣይ አባል ሀገር ኢትዮጵያ ልትሆን ትችላለች፣ ኢትዮጵያ…
Read More
የማራቶን ባለ ሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻውን ዙር ተቀላቀለች

የማራቶን ባለ ሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻውን ዙር ተቀላቀለች

አትሌት ትግስት አሰፋ ለአለም አትሌቲክስ በዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱ ምርጥ 10 የዓለም አትሌቶች መካከል አንዷነበረች። የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በ2023 ዓመት በተካሄዱ የተለያዩ ውድድሮች ላይ ስኬታማ የሆኑ አትሌቶችን ዝርዝር ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በመጀመሪያው ዙር 11 ምርጥ የዓለማችን አትሌቶች ዝረዝር ውስጥም የ5 ሺህ ሜትር ባለ ሪከርዷ ጉዳፍ ጸጋዬ እና የማራቶን ባለሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱ አትሌቶች ነበሩ። ዎርልድ አትሌቲክስ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት በውድድሩ ለመጨረሻ ዙር ያለፉ አትሌቶችን ዝርዝር አውጥቷል። በዚህም የማራቶን ባለሪከርዷ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለመጨረሻ ዙር ውድድር ከቀረቡ አትሌቶች መካከል እንዷ ሆናለች። ከአትሌት ትግስት አሰፋ በተጨማሪ ኬንያዊቷ አትሌት ፋይዝ ኪፕዬጎን፣ ጃማይካዊቷ ሸሪካ ጃክሰን፣ የኔዘርላንዷ…
Read More
የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ጃል መሮ ፊት ለፊት ተገናኙ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ጃል መሮ ፊት ለፊት ተገናኙ

የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራር እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት መሪው ጃል መሮ ፊት ለፊት መገናኘታቸው ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂ ቡድን መካከል በታንዛኒያ የሁለተኛ ዙር የሰላም ንግግር መጀመራቸው ተሰምቷል። ቢቢሲ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ባወጣው ዘገባ የሰላም ንግግሩ ጥቂት ቀናትን እንዳስቆጠረና ከሁለቱም ወገኖች የተወጣጡ የጦር አባላት ተወካዮች በተገኙበት በመካሄድ ላይ ይገኛል። ከዚህ ቀደም ራስ ገዝ ግዛት በሆነችው ዛንዚባር የተካሄደውን ድርድር የምሥራቅ አፍሪካ በየነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ)፣ አሜሪካ፣ ኖርዌይ እና ኬንያ አስተባባሪ እና አሸማጋይ ሚና መውሰዳቸው ይታወሳል። አሁን የተጀመረውን ንግግር ማን እንደሚያደራድር ግልጽ ባይሆንም፣ ኢጋድ ከዚህ ቀደም የነበረውን ሚና ሳያስቀጥል እንዳልቀረ ተጠቅሷል። ከዚህ በተጨማሪ አዲስ…
Read More
አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ዋልያዎቹን በአሰልጣኝነት ተረከቡ

አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ዋልያዎቹን በአሰልጣኝነት ተረከቡ

የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሐየራዊ ቡድን አሰልጣን የነበሩት ገብረመድህን ሀይሌ በድጋሚ ዋልያዎቹን እንዲያሰለጥኑ ተመርጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እንዳስታወቀው የኢትዮጵያ መድን እግር ኳ ክለብን በማሰልጠን ላይ የነበሩት አሰልጣኝ ገብረመድህን ሀይሌ በአንድ ዓመት ውል ብሔራዊ ቡድኑን እንዲያሰለጥኑ ተመርጠዋል፡፡ አሰልጣኙ የብሔራዊ ቡድን ስራቸውን ከኢትዮጵያ መድን እግር ኳስ ክለብ ጋር ደርበው እንዲያካሂዱ ከፌዴሬሽኑ ጋር እንደተስማሙም ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ የሚያደርጋቸውን ሁለት ቀጣይ የሜዳው ጨዋታዎችን ወደ ሞሮኮ ተጉዘው ያካሂዳሉም ተብሏል። የመጀመርያው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ከሴራሊዮን ኅዳር 5 እንዲሁም ሁለተኛው ጨዋታ ከቡርኪና ፋሶ ጋር ኅዳር 11 የሚደረግ ሲሆን ሁለቱም ጨዋታዎች በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም ይደረጋሉ፡፡ ብሄራዊ ቡድኑን በኢንተርናሽናል ውድድር ተፎካካሪ ማድረግ የሚጠብቅባቸው አሰልጣኝ ገብረመድህን…
Read More
የጸጋ ተስፋዎች እና በህይወት የመኖር ትግል

የጸጋ ተስፋዎች እና በህይወት የመኖር ትግል

ጸጋ ትባላለች በትግራይ ክልል ደንጎላት በተባለ አካባቢ የተወለደች ሲሆን እድገቷም ሆነ የትዳር ሕይወቷን በዚያው ያደረገች ወጣት እናት ናት። ጸጋ ወደ ትዳር ስትገባ የ16 ዓመት ታዳጊ ነበረች በወቅቱ በቤተሰብ ስምምነት በተፈጸመው በዚህ ትዳር 2 ሴት እና 2 ወንድ በአጣቃላይ 4 ልጆችን አፍርተውበታል። በወቅቱ በነበሩበት አካባቢ በቆሎ በማምረት እና በመሸጥ ከባለቤቷ ጋር ጥሩ ኑሮ ይኖሩ የነበሩ ሰዎችም ነበሩ። ነገር ግን ይህ ጥሩ የሚባለው ኑሮ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ የተገላቢጦች እየሆነ መጣ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተፈጠረው ጦርነት ነገሮች መስመራቸውን እየለቀቁ መጡ... በወቅቱ የንግድ እንቅስቃሴዎች እየቀነሱ መምጣታቸው መሠረታዊ የሚባሉ ነገሮች በተለይም ምግብ ነክ ሸቀጦች ዋጋቸው የማይቀመስ ሆነ እንደ ቡና፣ ጨው፣ ስኳር እና መሰል ነገሮችን ማግኘት…
Read More
ኢትዮጵያ ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ማምጠቂያ ጊዜን አራዘመች

ኢትዮጵያ ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ማምጠቂያ ጊዜን አራዘመች

ኢትዮጵያ ETRSS-02 የሚል ስያሜ የተሰጣትን ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት በወራት ውስጥ እንደምትመጥቅ ተገልጾ የነበረ ቢሆንም መራዘሙ ተገልጿል፡፡ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከሶስት ወራት በፊት በሰጠው መግለጫ በቅርቡ ሶስተኛዋን ሳተላይት አመጥቃለሁ ሲል ገልጾ ነበር፡፡ ይሁንና ETRSS-02 የተሰኘችው ሳተላይት በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥ እንደምትመጥቅ አስታውቋል፡፡ ከዚህ በፊት በቻይና አጋዥነት ወደ ሕዋ የመጠቁት ሳተላይቶች የተቀመጠላቸውን የአገልግሎት ጊዜ በመጨረስ ተልዕኳቸውን በስኬት ማጠናቀቃቸውም ኢንስቲትዩቱ ገልጿል። የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ፤ ሶስተኛውን ሳተላይት መምጠቅን በተመለከተ መንግስት የፋይናንስና የኢኮኖሚ አዋጪነት ጥናት ማድረጉን ገልጸዋል። ጥናቱ ከዚህ በፊት ወደ ሕዋ ከመጠቁት ሳተላይቶች ተሞክሮ በመውሰድ የቀጣዩን ሳተላይት መረጃ ከመጠቀም አልፎ ሌሎች ተልዕኮዎችን በግልጽ ማስቀመጡንም አመልክተዋል። የሳተላይቱን ጨረታ…
Read More
የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ አንድ ዓመት ሞላው

የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ አንድ ዓመት ሞላው

ህወሀት የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን እዝን ማጥቃቱን ተከትሎ ነበር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተቀሰቀሰው። ለሁለት ዓመት የዘለቀው ይህ ጦርነት 800 ሺህ ገደማ ኢትዮጵያዊያን ህይወታቸውን እንዲያጡ ሲያደርግ 26 ቢሊዮን ዶላር የኢኮኖሚ ኪሳራም አድርሷል። ለዚህ ጦርነት መቆም ምክንያት የሆነው የሰላም ስምምነት ከአንድ ዓመት በፊት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተፈርሟል። የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ስለ ስምምነቱ እና ሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በፌደራል መንግሥት እና ትግራይ ሀይሎች መካከል የተካሄደው የሰላም ስምምነት ለኢትዮጵያ ምን ጥቅም አስገኘ? በሚል ከጋዜጠኞች ጥያቄ ለቃል አቀባዩ ተነስቶላቸዋል። አምባሳደር መለስ በምላሻቸውም " ስምምነቱ በሁለቱ ወገኖች መካከል ጦርነት እንዲቆም ከማድረግ በተጨማሪ ኢትዮጵያ ላይ…
Read More