13
Nov
ከ24 ዓመት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን የኢኮኖሚ ትስስር ለማሳለጥ የተቋቋመው የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ ጥምረት በየጊዜው አዳዲስ አባላትን በመሳብ ላይ ይገኛል። ጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ከአንድ ዓመት በፊት ይህን ጥምረት ለመቀላቀል በይፋ መጠየቋ ይታወሳል። ጥምረቱም የመቋዲሾን ጥያቄ ለመመለስ ባለሙያዎቹን አሰማርቶ የተለያዩ ግምገማዎችን ሲያደርግ ቆይቶ ሶማሊያን ስምንተኛዋ አባል ሀገር አድርጎ እንደሚቀበል አስታውቋል። ዋና መቀመጫውን አሩሻ ታንዛኒያ ያደረገው ይህ የኢኮኖሚ ጥምረት በሚቀጥለው ሳምንት በሚያደርገው ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ሶማሊያን በይፋ በአባልነት እንደሚቀበል ገልጿል። የጥምረቱ ዋና ጸሀፊ ፒተር ማቱኪ በሞሮኮ ማራካሽ በተካሄደው የኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ እንዳሉት "ሶማሊያ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ አባል ትሆናለች" ብለዋል። ዋና ጸሀፊው አክለውም "የጥምረቱ ቀጣይ አባል ሀገር ኢትዮጵያ ልትሆን ትችላለች፣ ኢትዮጵያ…