Blog

አዲሱ የአውሮፓ ህብረት ሕግ በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች ላይ የሕልውና አደጋ ደቅኗል ተባለ

አዲሱ የአውሮፓ ህብረት ሕግ በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች ላይ የሕልውና አደጋ ደቅኗል ተባለ

የአውሮፓ ህብረት ከሁለት ሳምንት በፊት ባወጣው አዲስ ህግ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን የሚጎዱ ምርቶችን ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት ገበያዎች እንዳይገቡ እና እንዳይሸጡ አደርጋለሁ ብሏል፡፡ የምድርን ሙቀት ለመከላከል እና የደን ምንጣሮን ለመከላከል ይረዳል በሚል የተዘጋጀው ይህ ህግ ከደን ምርቶች ጋር የተያያዙ ምርቶች በአውሮፓ የገበያ እድል እንዳያገኙ መከልከል እና የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን ማበረታታት የህጉ ዋነኛ ዓላማ ነው፡፡ ይህ ሕግ የጫካ ቡናዎችን ወደ አውሮፓ እና ሌሎች ዓለም ገበያ መዳረሻዎች የምትልከው ኢትዮጵያን እንደሚመለከት ስጋቶች ተነስተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቡና ማህበር ጉዳዩ እንዳሳሰበው ገልጾ አዲሱ የአውሮፓ ህግ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ እንዲረዳ ካልተደረገ ሚሊዮኖች ወደ ድህነት ሊወርዱ ይችላሉ ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ሁሴን አምቦ (ዶ/ር) ለአልዐይን እንዳሉት “በኢትዮጵያ ቡና…
Read More
ኢትዮጵያ የክሪፕቶከረንሲ መረጃ ማዕከል መሆን የሚያስችላትን ስምምነት ተፈራረመች

ኢትዮጵያ የክሪፕቶከረንሲ መረጃ ማዕከል መሆን የሚያስችላትን ስምምነት ተፈራረመች

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የምናበዊ ገንዘብ ወይም የክሪፕቶከረንሲ ግብይት ፍላጎት እየጨመረ ሲሆን በኢትዮጵያም አጀንዳ ከሆነ አምስት ዓመት ሆኖታል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የትኛውንም ክሪፕቶ ከረንሲ ግብይት እንዳልፈቀደ እና ግብይት ሲፈጽሙ የተገኙ ሰዎችም በህግ ተጠያቂ እንደሚሆኑ አስታውቆ ነበር፡፡ ካሳለፍነው ዓመት ጀምሮ በኢትዮጵያ የቢትኮይን ግብይት መፈጸም የሚያስችሉ መሰረተ ልማት ግንባታ የሚያደርጉ ኩባያዎች ፍላጎት እየጨመረ መጥቷል፡፡ ኢትዮጵያ አሁንም የክሪፕቶከረንሲ ግብይት እንዲደረግ ያልፈቀደች ሲሆን የዳታ ማዕከል ግንባታዎች እንዲካሄዱ ግን ስምምነቶችን በመፈራረም ላይ ነች፡፡ በዛሬው ዕለትም ዌስት ዳታ ማዕከል የተሰኘው ኩባንያ የ250 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በአዲስ አበባ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ጋር ተፈራርሟል፡፡ በዚህ ስምምነት መሰረት የቢትኮይን ግብይት እና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ጉዳዮች ዙሪያ ስልጠና መስጠት…
Read More
ራይላ ኦዲንጋ ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት እንደሚወዳደሩ ገለጹ

ራይላ ኦዲንጋ ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት እንደሚወዳደሩ ገለጹ

ኬንያዊው ራይላ ኦዲንጋ የወቅቱ የወቅቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማትን ለመተካት በሚደረገው ምርጫ ላይ መወዳደር እንደሚፈልጉ ተናግረዋል፡፡ ከፈረንጆቹ 2017 ጀምሮ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሃማት የስልጣን ጊዜያቸው የፊታችን ሐምሌ ያበቃል፡፡ ይህን ተከትሎም ሙሳ ፋኪ መሀማትን ለመተካት ሀገራት ከወዲሁ እጩዎቻቸውን እያቀረቡ ሲሆን ኬንያዊው ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋ ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት እንደሚወዳደሩ አስታውቀዋል፡፡ ራይላ ኦዲንጋ ለዚህ እንዲረዳቸው የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ መልዕክተኛ ኦሊሶጎኖ ኦባሳንጆ ሀገራትን እንዲያሳምኑለት እንደመረጣቸውም ተናግሯል፡፡ የኬንያ ፕሬዝዳንት ለመሆን አራት ጊዜ ተወዳድረው የተሸነፉት ራይላ ኦዲንጋ በቀጣይ ግንቦት በሚደረገው ምርጫ ለማሸነፍ የተወሰኑ ሀገራትን ለማሳመን ጥረት መጀመራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ይሁንና ራይላ ኦዲንጋ…
Read More
የአፍሪካ ህብረት ሳይጋበዙ ጉባኤውን ለመሳተፍ የሚመጡ ሰዎችን አስጠነቀቀ

የአፍሪካ ህብረት ሳይጋበዙ ጉባኤውን ለመሳተፍ የሚመጡ ሰዎችን አስጠነቀቀ

የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች የሚሳተፉበት 44ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው። የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ደግሞ የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ የሚካሄድ ሲሆን በዚህ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ለሚመጡ ታዛቢ ሀገራት ማስጠንቀቂያ አውጥቷል፡፡ ህብረቱ ባወጣው መግለጫ በታዛቢነት እንዲሳተፉ ከተጋበዙ ሀገራት እና ተቋማት ውጪ የሚመጡ ተሳታፊዎችን እንደማያስተናግድ አስጠንቅቋል፡፡ 37ኛው የህብረቱ መሪዎች እና 44ኛው የህብረቱ ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ጉባኤን በታዛቢነት እንዲሳተፉ ከተፈቀደላቸው ሀገራት እና ተቋማት ውጪ እንዳይመጡ እና ፈቃድ የተሰጣቸው ደግሞ ከአንድ ተወካይ በላይ እንዳይመጡ ሲልም ህብረቱ አሳስቧል፡፡ ከዚህ በፊት በአፍሪካ ህብረት ጉባኤዎች ላይ በታዛቢነት እንዲሳተፉ ፈቃድ የተሰጣቸው ሀገራት እና ተቋማትም ፈቃዳቸውን እንዲያድሱ ሲልም…
Read More
የጀርመኑ ናቡ የተሰኘው የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የአፍሪካ ቢሮውን በኢትዮጵያ ከፈተ

የጀርመኑ ናቡ የተሰኘው የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የአፍሪካ ቢሮውን በኢትዮጵያ ከፈተ

ከ125 ዓመት በፊት የተመሰረተው የጀርመኑ የተፈጥሮ እና ብዝሀ ህይወት ጥበቃ ተቋም (ናቡ) የአፍሪካ ቢሮውን በአዲስ አበባ ከፍቷል፡፡ የናቡ ፕሬዝዳንት ጆርግ አንድሪያስ ክሩገር እንዳሉት ኢትዮጵያ የብዝሃ ህይወት ሀብት በብዛት ከሚገኙባቸው ሀገራት መካከል አንዷ በመሆኗ እና ከአፍሪካ ጋር ለሚኖረን ግንኙነት መግቢያ በመሆኗ ቢሯቸውን በአዲስ አበባ ለመክፈት እንደወሰኑ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እና ተቋማት ጋር ያለንን ግንኙነት በማቀላጠፍ ተጨማሪ የተፈጥሮ እና ብዝሃ ህይወት ጥበቃ ስራዎችን ለማስራት ቢሯችንን በአዲስ አበባ ለመክፈት አነሳስቶናልም ብለዋል፡፡ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረው ይህ የተፈጥሮ እና ብዝሃ ህይወት ጥበቃ ተቋም በአውሮፓ፣ እስያ እና አፍሪካ ሀገራት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በአፍሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ7 ሀገራት ላይ እየሰራ…
Read More
በደላንታ ኦፓል በማውጣት ላይ እያሉ የተቀበሩ 20 ወጣቶችን ለማትረፍ ህዝቡ ሌት ተቀን እየቆፈረ ነው ተባለ

በደላንታ ኦፓል በማውጣት ላይ እያሉ የተቀበሩ 20 ወጣቶችን ለማትረፍ ህዝቡ ሌት ተቀን እየቆፈረ ነው ተባለ

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ 018 ቀበሌ ልዩ ስሙ አለኋት ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ነበር ኦፓል ማዕድን በማውጣት ላይ የነበሩ ወጣቶች መውጫ ስፍራ በአለት የተደፈነባቸው፡፡ በማህበር ተደራጅተው ኦፓል እንዲያወጡ የተደራጁት እነዚህ ወጣቶች ቁጥራቸው 20 ሲሆን ከመሩት በህይወት ለማትረፍ የአካባቢው ማህበረሰብ ሌት ተቀን በፈረቃ እየቆፈረ መሆኑን የዞኑ መንግስት ኮሙንኬሽን መምሪያ ሃላፊ አቶ እያሱ ለአልዐይን ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ እያሱ ገለጻ ከሆነ ወጣቶቹ ሌሊት ላይ ማዕድኑን ለማውጣት እየቆፈሩ እያሉ መውጫቸው በዓለት የተዘጋ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ በተመሳሳይ ስራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ጉዳዩን ለህዝብ አሳውቀዋል፡፡ ጥር 30 ቀን የተከሰተው ይህ አደጋ ከመሬት ውስጥ ባለው ዋሻ ውስጥ ያሉትን ወጣቶች የደላንታ ወረዳ እና የአካባቢው ማህበረሰብ በዘመቻ…
Read More
የ2023 አፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ በኮቲዲቯር አሸናፊነት ተጠናቀቀ

የ2023 አፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ በኮቲዲቯር አሸናፊነት ተጠናቀቀ

37ኛው የአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር በውድድሩ አዘጋጅ ሀገር ኮቲዲቯር አሸናፊነት ተጠናቋል። ጥር 3 ቀን ተጀምሮ የካቲት 3 ቀን 2016 ዓ.ም ፍጻሜውን ያገኘው ይህ ውድድር ናይጀሪያ እና ኮቲዲቯር ለዋንጫ ተጫውተዋል። ናይጀሪያ በመጀመሪያው አጋማሽ በአምበሏ ኢኮንግ ጎል ቀድማ ጎል ያስቆጠረች ቢሆንም ኬሲ እና ሀለር ኮቲዲቯርን የዋንጫ ባለቤት ያደረጉ ጎሎችን አስቆጥረዋል። ይህን ውድድር ደቡብ አፍሪካ ሶስተኛ እንዲሁም ዲሞክራቲክ ኮንጎ አራተኛ ሆነው አጠናቀዋል። በዚህ ውድድር ላይ የኮቲዲቯር አሰልጣኝ ኤምሬ ፋኤ ኮከብ አሰልጣኝ፣ ሲሞን አዲንጋራ ምርጥ ኮከብ ወጣት ተጫዋች ናይጀሪያዊው ዊሊያም ኢኮንግ የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች፣ የ34 ዓመቱ የኢኳቶሪያል ጊኒው ኤምሊያኖ ኑስ በአምስት ጎሎች ኮከብ ግብ አግቢ እንዲሁም ሮንውን ዊሊያምስ ኮከብ ግብ ጠባቂ በመሆን ተመርጠዋል።…
Read More
ኢትዮጵያ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው የውጭ ሀገራት ዜጎች መመዝገቢያ ጊዜን አራዘመች

ኢትዮጵያ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው የውጭ ሀገራት ዜጎች መመዝገቢያ ጊዜን አራዘመች

የኢትዮጵያ ኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ከሁለት ሳምንት በፊት ባወጣው መግለጫ የውጭ ሀገር ዜጎች ሀሰተኛ ሰነዶችን ተጠቅመው ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸውን ደርሼበታለሁ ብሎ ነበር፡፡ የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በሰጡት መግለጫ በርካታ የውጭ ሀገር ዜጎች ሀሰተኛ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ሀሰተኛ ጊዚያዊ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ሀሰተኛ ፓስፖርት፣ ሀሰተኛ ቪዛ እና ሀሰተኛ ሰነድ አዘጋጅተው በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እየኖሩ ይገኛል ብለዋል። በተደረገው የማጣራት ስራ ከ18 ሺህ በላይ ሀሰተኛ ጊዚያዊ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ከ1 ሺህ 500 በላይ ሀሰተኛ ቪዛ እና ከአንድ ሺህ 800 በላይ የትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያን ያሰሩ ዜጎች በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች መገኘታቸውንም ዳይሬክተሯ ተናግረዋል። በመሆኑም ህገወጥ ሰነድ ያለቸው ዜጎች ከጥር እስከ ጥር 30 ቀን 2016…
Read More
ኢትዮጵያ የሳሞአ ስምምነትን እንድትሰርዝ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠየቀ

ኢትዮጵያ የሳሞአ ስምምነትን እንድትሰርዝ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠየቀ

የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ እንዳስታወቀው ኢትዮጵያ በአውሮፓ ኅብረት፣ አፍሪካ፣ ካሪቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት መካከል የተፈረመውንና የሳሞአ ስምምነት በመባል የሚታወቀውን የንግድና የኢኮኖሚ አጋርነት ስምምነትን ውድቅ እንድታደርግ ጠይቋል፡፡ ተቋሙ ይህ ስምምነት የተጠቀሰው የወሲብና የስነ ተዋልዶ ጤና እና መብቶች በሚል ዘርፍ የተደረገው ስምምነት ከግብረሰዶም መብቶች፤ ከፆታ መቀየር፤ ከጽንስ ማቋረጥ እንዲሁም የወሲብ ንግድን የሚያበረታታ እንደሆነ አስታውቋል፡፡ በስምምነቱ የአፍሪካ ፕሮቶኮል አንቀፅ 40.6 ላይ በአህጉሪቱ ለሚገኙ ልጆችና ታዳጊዎች ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርት የተባለ እጅግ አደገኛ ልቅ የወሲብ ትምህርት እንዲማሩ የሚያስገድድ በመሆኑ እንደሚቃወመውም ገልጿል፡፡ ሌላኛው ተቋሙ የተቃወመው የፆታ ትንኮሳን ማስቀረት በሚል የተቀመጠው ይዘት በጣም አሻሚ የሆነ ግብረሰዶማዊ አስተሳሰቦችን ለማስረፅ እንዲረዳው በሰነዱ በበርካታ ክፍሎች ውስጥ " አካታች "…
Read More
አሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ በኢትዮጵያ ቢሮውን እንደሚከፍት አስታወቀ

አሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ በኢትዮጵያ ቢሮውን እንደሚከፍት አስታወቀ

ድርጅቱ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በአፍሪካና በምስራቅ አውሮፓ ሀገራት ውስጥ 30 ወኪል ቢሮዎችን እከፍታለሁ ብሏል፡፡ ሪቭኤክሴል እና አሜሪካን ሆስፒታል ዱባይ ከሰሃራ በታች ባሉ ሀገራት የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ስትራቴጂያዊ አጋርነትን እንደፈጠሩ አስታውቋል፡፡ አሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ በአፍሪካና ምስራቅ አውሮፓ 30 ወኪል ቢሮዎችን የመክፈት ዕቅዱን ያስጀመረ ሲሆን በዱባይ ጤና ባለስልጣን ዕውቅና ያላቸው 3 የህክምና ቱሪዝም ቢሮዎችን በናይጄርያ የተለያዩ ከተሞች ከፍቷል፡፡ በዓለምአቀፍ የንግድ መፍትሄዎች መሪ ተዋናይ የሆነው ሪቭኤክሴል ዓለምአቀፍ ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራትን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለማሳደግ ያለውን ቁርጠኝነት በማጠናከር ከአሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ ጋር የለውጥ ስትራቴጂያዊ አጋርነቱን በይፋ አሳውቋል፡፡ የአሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ ይህንን ያረጋገጠው በ30 ወሳኝ የአፍሪካና የምስራቅ አውሮፓ ከተሞች የወኪል ቢሮዎች የማስፋፍያ ዕቅዱ አካል ሆኖ በናይጄርያ…
Read More