Year: 2026

የእስራኤል- ኢራን ጦርነት ለነዳጅ ድጎማ የሚወጣውን ገንዘብ ጨምሮታል ተባለ

የእስራኤል- ኢራን ጦርነት ለነዳጅ ድጎማ የሚወጣውን ገንዘብ ጨምሮታል ተባለ

ኢትዮጵያ ለነዳጅ ግዢ በየዓመቱ ከ4 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ወጪ እንደምታደርግ ተገልጿል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ዛሬ መጋቢት 2፣ 2018 በሰጡት መግለጫ በእስራኤል-አሜሪካ እና ኢራን መካከል በተጀመረው ጦርነት ምክንያት ለነዳጅ ድጎማ የሚያወጣው ወጪ እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ አህመድ ገለጻ ይህ ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ኢትዮጵያ አንድ ሊትር ቤንዚን በ129 ብር ለተጠቃሚዎች ስታቀርብ የነበረ ሲሆን ድጎማው ቢቀር ግን የአንድ ሊትር ቤንዚን መሸጫ ዋጋ 157 ብር ይሆን ነበር፡፡ እንዲሁም ነጭ ናፍጣ 129 ነበር በሊትር ሲሸጥ ነበር የተባለ ሲሆን ድጎማው ቢነሳ 182 ነጥብ 8 ብር መሸጥ ነበረበት ተብሏል፡፡ ሚኒስትሩ አክለውም በመካከለኛው ምስራቅ የተጀመረው ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ኢትዮጵያ ቤንዚን የ28 ነጥብ…
Read More
የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን 60 ሰራተኞቹ እንደተገደሉበት አስታወቀ

የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን 60 ሰራተኞቹ እንደተገደሉበት አስታወቀ

የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ባለፉት 60 ዓመታት ቢያንስ 60 ሠራተኞቹን በሥራ ላይ እያሉ ህይወታቸውን እንዳጡ ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ባለፉት 6 አሥርት ዓመታት የዱር እንስሳትን እና የተፈጥሮ ሀብትን በመጠበቅ ሂደት ውስጥ ቢያንስ 60 ሠራተኞቹ በሥራ ላይ እያሉ ሕይወታቸውን ማጣታቸውን አስታውቋል። ባለሥልጣኑ ዛሬ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የ60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን የፊታችን መጋቢት 3 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚያከብር አስታውቋል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጅራ፣ ሠራተኞቹ ሕይወታቸውን ያጡት ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጋር በተያያዙ የተለያዩ የሥራ ላይ ፈተናዎች መሆኑን ገልጸዋል። ባለሥልጣኑ ባለፉት 60 ዓመታት ውስጥ ከ1 ሺህ 700 በላይ ለሚሆኑ ልዩ ልዩ የዱር እንስሳት ዝርያዎች ጥበቃ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሴት ፓይለቶች ቁጥር 95 መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሴት ፓይለቶች ቁጥር 95 መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (ማርች 8) በማስመልከት፣ በሴቶች ባለሙያዎች ብቻ የሚመሩ 8 በረራዎችን በተመሳሳይ ጊዜ ወደ ተለያዩ የአለም ሀገራትና የሀገር ውስጥ መዳረሻዎች እንደሚያከናውን ገልጿል። አየር መንገዱ ዕለቱን በማስመልከት ባከናወነው መርሃግብር ላይ እንደገለጸው ወደ ካይሮ፣ ጅቡቲ፣ ናይሮቢ፣ ፍራንክፈርት፣አክራ፣ ሙምባይ፣ ዊንድሆክ እና ድሬዳዋ የሚደረጉ በረራዎች ሙሉ በሙሉ በሴት ፓይለቶች፣ ቴክኒሻኖች እና የበረራ አስተናጋጆች የሚመሩ ይሆናሉ ተብሏል። ይህ ልዩ የበረራ መርሃ ግብር ሴቶች በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ ያላቸውን አቅምና ተሳትፎ ለማሳየት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ገልጸዋል። እንደ ዋና ስራ አስፈጻሚው መረጃ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ካሉ ጠቅላላ ሰራተኞች መካከል 40 በመቶ ያህሉ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሳምንት የ137 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እያስተናገደ መሆኑን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሳምንት የ137 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እያስተናገደ መሆኑን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በእስራኤል-ኢራን ጦርነት ምክንያት በሳምንት የ137 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እያስተናገደ መሆኑን ገለጸ ከሰባት ቀናት በፊት የተጀመረው የእስራኤል-ኢራን ጦርነት ጉዳቱ በመላው ዓለም ላይ ሲሆን ኢትዮጵያም የጦርነቱ ተጎጂ ሆኗ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንዳስታወቀው በዚህ ጦርነት ምክንያት በየሳምንቱ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የካርጎ በረራን ሳይጨምር የመንገደኞችን ብቻ 101 በላይ በረራዎችን እየሰረዘ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በረራዎቹ በመሰረዛቸው ምክንያትም እስከ 137 ሚሊዮን ዶላር በማጣት ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡ አየር መንገዱ የእስራኤል- ኢራን ጦርነት ከመጀመሩ በፊት በቀን ወደ ዱባይ ሦስት ጊዜ ፣ ወደ ሻርጃ አንድ ጊዜ፣ ወደ እስራኤል ሦስት ጊዜ፣ ወደ አቡዳቢ፣ ወደ አማን ሁለቴ መንገደኞችን ያመላልስ ነበር። በጦርነቱ ምክንያት አየር መንገዱ በአማካኝ በየዕለቱ 15…
Read More
መንግስት በኦሮሚያ ክልል አርሲ በቂ የጸጥታ ሀይል እንዲያሰማራ ኢሰመኮ ጠየቀ

መንግስት በኦሮሚያ ክልል አርሲ በቂ የጸጥታ ሀይል እንዲያሰማራ ኢሰመኮ ጠየቀ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ንጹሃን ዜጎች ግድያ እንደተፈጸመባቸው አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ ኮሚሽኑ በሪፖርቱ ላይ እን ዳስታወቀው በዞኑ ያለው ሁኔታ ለተወሰኑ ጊዜያት እየተሻሻለ የነበረ ቢመስልም ከጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም ጀምሮ ታጣቂ ቡድኑ በሽርካ፣ በጉና፣ በመርቲ፣ በአሰኮ እና በኦንቆሌ ዋቤ ወረዳዎች በሰዎች ላይ በፈጸማቸው ጥቃቶች በሰዎች ሕይወት፣ አካልና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ገልጿል፡፡ እንዲሁም ከዚሁ ጋር በተያያዘ በተፈጠሩ የደህንነት ሥጋቶች ምክንያት የነዋሪዎች መፈናቀል መከሰቱን ኢሰመኮ የደረሱትን ጥቆማዎችና አቤቱታዎች መሠረት በማድረግ የተጎጂ ቤተሰቦችን፣ ነዋሪዎችን እና የየአካባቢዎቹን የመንግሥት ኃላፊዎች በማነጋገር ባሰባሰባቸው መረጃዎች ማረጋገጡን አስታውቋል። የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (በተለምዶ “ኦነግ ሸኔ”) የካቲት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በዞኑ ሽርካ ወረዳ ጃዊ…
Read More
አንድ የአሜሪካ ዶላር ዋጋ ወደ 156 ብር ከፍ ማለቱ ተገለጸ

አንድ የአሜሪካ ዶላር ዋጋ ወደ 156 ብር ከፍ ማለቱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባከናወነው 20ኛው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ አንድ የአሜሪካ ዶላርን አማካይ በ155 ነጥብ 4 ብር መድረሱን ይፋ አድርጓል። ብሔራዊ ባንክ ለገበያ ያቀረበው የውጭ ምንዛሬ መጠን 70 ሚሊዮን ዶላር ቢሆንም፣ ከንግድ ባንኮች በኩል የቀረበው የፍላጎት መጠን ግን 177 ነጥብ 12 ሚሊዮን ዶላር ሆኖ ሆኗል። ይህም አቅርቦቱ ከፍላጎቱ ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ልዩነት እንዳለው ያሳያል። ከፍተኛው የማሸነፊያ ዋጋ 156 ነጥብ 05 ብር ሲሆን ዝቅተኛው የጨረታ ዋጋ ደግሞ 153 ነጥብ 8805 ብር ሆኗል። ባንኩ በዚህ ጨረታ አንድ ዶላርን 155 ነጥብ 88 ብር መሸጡን አስታውቋል። በዚሁ ጨረታ ላይ በአጠቃላይ 20 የንግድ ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ ካቀረቡት የዋጋ ተወዳዳሪነት አንጻር 9 ባንኮች ብቻ የቀረበውን የውጭ…
Read More
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የኢራንን ጥቃት አወገዙ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የኢራንን ጥቃት አወገዙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እሁድ ዕለት ኢራን በኩዌት ላይ የፈጸመችውን ጥቃት ተከትሎ ከኩዌት ልዑል አልጋ ወራሽ ሼክ ሳባህ ኻሊድ አል ሀማድ አል ሳባህ ጋር በስልክ መወያየታቸው ተገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከኩዌቱ ልዑል አልጋ ወራሽ ጋር ባደረጉት ውይይት በአገሪቱ ሉዓላዊ ግዛት እና የአየር ክልል ላይ የሚፈጸም ጥቃትን በጽኑ ማውገዛቸውን የኩዌት የዜና ወኪል ዘግቧል። ይህ በዚህ እንዳለም ኢራን በእስራኤል እና አሜሪካ በደረሰባት የአየር ላይ ጥቃት የአጸፋ እርምጃ በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ላይ በምትወስዳቸው እርምጃዎች ኢትዮጵያዊን መጎዳታቸው እየተገለጸ ይገኛል፡፡ በመቶ ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊን እስራኤልን ጨምሮ በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ተቀጥረው በመስራት ላይ ሲሆኑ ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኢምሬት፣ ኳታር፣ ኩዌት እና ባህሬን ብዙ ኢትዮጵያዊያን ይኖራሉ፡፡ ኢራን…
Read More
ብሔራዊ ባንክ ክሪፕቶ ከረንሲን በብር መገበያየትን ከለከለ

ብሔራዊ ባንክ ክሪፕቶ ከረንሲን በብር መገበያየትን ከለከለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በተለያዩ በዲጂታል የንግድ መንገዶች አማካኝነት በብር የሚከናወኑ የሰው-ለሰው (P2P) የገንዘብ ዝውውሮች እና የክሪፕቶ ከረንሲ ግብይቶች ሕገ-ወጥ መሆናቸውን አስታውቋል። ባንኩ ዛሬ የካቲት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፣ በማንኛውም መድረክም ሆነ የልውውጥ ማዕከል በብር የሚደረጉ የዲጂታል ሀብት ግብይቶች ያለ ባንኩ ፈቃድ በፍጹም የተከለከሉ መሆናቸውን አስታውቋል። ይህ እገዳ ማንኛውንም በብር የሚሰላ የክሪፕቶ ከረንሲ ልውውጥን የሚያካትት መሆኑም ተገልጿል። እንደ ብሔራዊ ባንክ ማብራሪያ፣ እነዚህ መድረኮች ለከፍተኛ የዋጋ መዋዠቅ፣ ለገንዘብ ማጭበርበር እና ለውጭ ምንዛሪ ዋጋ መዛባት እጅግ ተጋላጭ ናቸው። በተጨማሪም እንደ ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን የመሳሰሉ የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል የሚያስችሉ ሥርዓቶች በእነዚህ መድረኮች ላይ ባለመኖራቸው ኅብረተሰቡ ለከፍተኛ አደጋ ሊጋለጥ…
Read More
የብልጽግና ፓርቲ ከነጋዴው ማህበረሰብ በአስገዳጅነት ገንዘብ መሰብሰቡን እንዲያቆም ተጠየቀ

የብልጽግና ፓርቲ ከነጋዴው ማህበረሰብ በአስገዳጅነት ገንዘብ መሰብሰቡን እንዲያቆም ተጠየቀ

ለሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ በምርጫው የሚሳተፍ ሀገር አቀፍ እና ክልላዊ ፓርቲዎች በምርጫው ላይ ጉልህ ተሳትፎ ለማድረግ የድርሻቸውን ዝግጅት እያደረጉ ይገኛሉ። ከዝግጅቶቻቸው መካከልም ዋነኛው ለምርጫው የሚያስፈልጋቸውን ገንዘብ እና ሀብት ከአባላቶቻቸው እና ከደጋፊዎቻቸው በተቀመጠው የህግ አግባብ መሰረት ማሰባሰብ አንዱ መሆኑን ኢዜማ ገልጿል። ይህ የገንዘብ እና ቁሳቁስ ማሰባሰብ ሂደት የአገሪቱን የፋይናንስ አሰራር ስረዓት እንዲሁም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፓለቲካ ፓርቲዎች የሀብት አሰባሰብን በተመለከተ ያስቀመጣቸውን ጥብቅ የህግ ድንጋጌዎች ባከበረ መልኩ መሆን እንዳለበትም ፓርቲው አስታውቋል። ኢዜማ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ብልፅግና ፓርቲ የህግ ድንጋጌዎች በጣሰ መልኩ በማንአለብኝነት መንፈስ ከፍተኛ ገንዘብ አባል ካልሆኑ ነጋዴዎች እና ባለሀብቶች በግዳጅ እያሰባሰበ እንደሆነ ደርሼበታለሁ ብሏል። "16 ሚሊዮን አባል አለኝ የሚለው ብልፅግና…
Read More
አዲስ ስታንዳርድ ሚዲያ ፈቃድ መሰረዙ ተገለጸ

አዲስ ስታንዳርድ ሚዲያ ፈቃድ መሰረዙ ተገለጸ

የኢትዮጵያ  መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን እንዳስታወቀው የአዲስ ስታንዳርድ የበየነ-መረብ መገናኛ ብዙኃን ምዝገባ ምስክር ወረቀት ከየካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ  ተሰርዟል ብሏል፡፡ እንደ ባለስልጣኑ መግለጫ ከሆነ አዲስ ስታንዳርድ የበየነ-መረብ መገናኛ ብዙኃን የሚዲያ ስነ ምግባርን፣ የኢትዮጵያ ሕጎች እና የሀገርንና የሕዝብን ብሔራዊ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥሉ ዘገባዎችን በተደጋጋሚ በማሰራጨት ላይ ይገኛል ሲል አስታውቋል፡፡ በመሆኑም ባለሥልጣኑ ይህንኑ ድርጊት በመመርመር አዲስ ስታንዳርድ የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን እንዲታረም እና ከአጥፊ አካሄዱ እንዲቆጠብ በተደጋጋሚ ምክር ሲሰጥ ቢቆይም ለመታረም ፈቃደኛ ሳይሆን በመቅረቱ ፈቃዲ እንደተሰረዘ ባለስልጣኑ ገልጿል። በተጨማሪም በሚዲያ ዘርፉ ላይ የሙያ ስነምግባር እና የሀገርና የህዝብ ብሔራዊ ጥቅም አክብሮ እንዲሰራ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ እና ማስጠንቀቂያ ቢሰጠውም ለመታረም ፈቃደኛ አልሆነም ያለው…
Read More