Business

ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ“PW ማይኒንግ” ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ

ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ“PW ማይኒንግ” ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ

የከፊ ሚኒራልስ ኩባንያ አካል የሆነው ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ 'PW ማይኒንግ' ጋር የወርቅ ማዕድን ልማትና በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ አብሮ ለመስራት ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱ የተፈረመው ከትናንት ሚያዚያ 18/2015 ጀምሮ በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ በሚገኘው፤ “ኢንቨስት ኢትዮጵያ 2023” ዓለም አቀፍ የንግድ ተቋማትና ባለሃብቶች ፎረም ጎን ለጎን ነው። በፎረሙ ከዓለም ዙሪያ የተውጣጡ ባለሃብቶች፣ የንግድ ተዋንያን፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና ሥራ ፈጣሪዎች እየተሳተፉበት የሚገኝ ሲሆን፤ በመድረኩ የመግባቢያ ሰነድ ስምምነቶች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የተመረጡ ኩባንያዎች ጉብኝትና አውደ ርዕይዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኢንቨትመንት ኮሚሽን አዘጋጅነት የሚከናወነው ይህ ፎረም በግብርና፣ ማንፋክቸሪንግ፣ አይ.ሲ.ቲ፣ ማዕድን እና በቱሪዝም ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያ ኢንቨሰትመንት ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ፣…
Read More
ኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረትን መግለጫ እንደምትቀበል ገለጸች

ኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረትን መግለጫ እንደምትቀበል ገለጸች

ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ሕብረት ጋር ያላትን ትብብር በአዲስ መልክ እንደገና ለማደስ አበክራ እየሰራች እንደምትገኝም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓ ሕብረት ምክር ቤት ከትናንት በስቲያ ኢትዮጵያን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ዙሪያ ምላሽ አውጥቷል። ሚኒስቴሩ ምክር ቤቱ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ትግበራ ላይ የተገኙ ውጤቶችን ጨምሮ ለሌሎች ጉዳዮች እውቅና መስጠቱን ገልጿል። ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ሕብረት ጋር ያላትን ትብብር በአዲስ መልክ እንደገና ለማደስ አበክራ እየሰራች እንደምትገኝና የምክር ቤቱ መግለጫም ይሄንኑ ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑን አመልክቷል። ሕብረቱ በዘላቂ ግብርናና የምግብ ዋስትና ላይ ያተኮረውን ዓመታዊ የባለብዙ ዘርፍ የድጋፍ ፕሮግራም በድጋሚ ለመጀመር ያሳየውን ዝግጁነት፣ አበዳሪ አገራት ባቋቋሙት የጋራ ማዕቀፍ ስር የሚከናወነው የኢትዮጵያ የዕዳ ሽግሽግ የድርድር ሂደት በአፋጣኝ እንዲቋጭ ያቀረበው ጥሪና…
Read More
42 ማርኬትስ  ግሩፕ  አስር ሚሊየን ዶላር  ድጋፍ ማግኘቱን ገለፀ

42 ማርኬትስ  ግሩፕ  አስር ሚሊየን ዶላር  ድጋፍ ማግኘቱን ገለፀ

ድርጅቱ ድጋፉን ያገኘው  በግል ባለሀብት ከሚንቀሳቀሰውና  በደቡብ ሰሀራ ሀገራት   በቴክኖሎጂ ላይ ከሚሰራው  ከኮንቨርጀንስ  ፓርተንርስ እና  ከ14  ዓለም ዓቀፍ   የገንዘብ ልማት  ላይ ከሚሰሩ ታዋቂ  የገንዘብ  ተቋማት ነው። በቅርቡ  በዲጂታል   የመሰረተ ልማት ላይ ስራዎች የገንዘብ አቅርቦት ፕሮጅክቱን በ 296 ሚልየን የአሜሪካ ዶላር ያጠናቀቀው  42 ማርኬትስ ግሩፕ ለተጠቃሚዎች ወይም ለንግድ ድርጅቶች የገንዘብ ልውውጥ  ላይ ከሚሰራው ፊንቴክ ቡድን ወስጥ አንዱ  ቡድን ነው። የ 42 ማርኬትስ ግሩፕ  ስራ አስኪያጅ  አንድሪስ ብሪንክ እንዳሉት  "የተገኘው ገንዘብ ድጋፍ  የዲጂታል ገንዘብ መሰረተልማቱ   ትክክለኛ መተማመኛ እንዲያገኝ ከማድረጉ ባሻገር    ለቀዘቀዘውም  ሆነ እያደገ ለሚመጣ  ገበያ  በጎ የኢንቨስትመንት  ተፅዕኖ እንዲኖረው ያደርጋል" ብለዋል። ከ42 ማርኬትስ ግሩፕ   የበሰሉ ስራዎች ከሚሰሩት  ድርጅቶች መካከል የካፒታል እና  ገበያ አገልግሎቶች …
Read More
የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ የዘጠኝ ወራት የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ። የንግድ እና ቀጠናዊ ውህደት ሚንስቴር እንደገለጸው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከወጪ ንግድ 3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ ነበር። ይሁንና የተገኘው ገቢ ግን በአንድ ቢሊዮን ዶላር ቀንሶ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል ተብሏል። ለገቢው መቀነስ የጸጥታ ችግሮች፣ ህገወጥ ንግድ፣ የዓለም ንግድ መቀዛቀዝ እና የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት በምክንያትነት ተጠቅሰዋል። ከተገኘው ገቢ ውስጥም ግብርና የ77 በመቶ ድርሻ ሲያዝ ቀሪው ማዕድን፣ ኢንዱስትሪ እና ኤሌክትሪክ ሽያጭ እንደሆኑ ሚንስቴሩ ገልጿል ባለፉት ሁለት ዓመታት በጦርነት ውስጥ የቆየችው ኢትዮጵያ የወጪ ንግዷ ተዳክሞ የቆየ ሲሆን በአሜሪካ የተጣለባት ማዕቀብ፣ ህገወጥ የማዕድን ገበያ መስፋፋት ለወጪ ንግዱ ዋነኛ ችግሮች…
Read More
አሜሪካንን ጨምሮ በርካቶች ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን እያስወጡ ነው

አሜሪካንን ጨምሮ በርካቶች ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን እያስወጡ ነው

አሜሪካን ጨምሮ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ዲፕሎማቶቻቸውን ከሱዳን ካርቱም ማስወጣት ጀምረዋል፡፡ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ በሱዳን ካርቱም የሚገኙ ዲፕሎማቶች እና ቤተሰቦቻቸው በዛሬው ዕለት ሀገሪቷን ለቀው መውጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ ዲፕሎማቶቹ የአሜሪካ ጦር ባካሄደው የተሳካ ኦፕሬሽን ከሱዳን ካርቱም በሰላም መውጣት ችለዋል ተብሏል። ፕሬዚዳንት ባይደን ዲፕሎማቶችን ለማስወጣት ለተደረገው የተሳካ ስራ ለኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ እና ሳዑዲ ዓረቢያ መንግስታት ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ አሁን ላይ በሱዳን የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ አገልግሎት መስጠት እንዳቆመ አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ 150 የሚሆኑ የሳዑዲ ዓረቢያ፣ ግብጽ፣ ካናዳ፣ ሕንድ፣ ኩዌት፣ ፓኪስታን እና የቱኒዚያ ዲፕሎማቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት አመራሮች በባህር ከሱዳን ሳዑዲ ዓረቢያ መግባታቸው ተገልጿል። ፈረንሳይ፣ ቻይና፣ ብሪታንያ፣ ስፔን እና ሌሎች ሀገራትም በሱዳን ካርቱም የሚገኙ ዲፕሎማቶቻቸውን…
Read More
በሱዳን ያሉ የውጭ ዜጎችን በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ተጀመረ

በሱዳን ያሉ የውጭ ዜጎችን በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ተጀመረ

ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14 ቀን 2014 ዓ.ም:- ሀገራት ዜጎቻቸውን እያስወጡ ያሉት በጋላባት-መተማ በኩል ነው ተብሏል ዜጎችን የማስወጣት ስራው በካርቱም ካለው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ጋር በመነጋገር ነው በሱዳ. ያሉ የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ተጀመረ የተለያዩ ሀገራት በሱዳን ያሉ ዜጎቻቸውን በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ጀምረዋል። በሱዳን ብሔራዊ ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ መካከል የተጀመረው ጦርነት ስምንተኛ ቀኑ ላይ ይገኛል። ለኢድ በዓል ተብሎ የሶስት ቀን ተኩስ አቁም ቢደረግም ጦርነቱ ዛሬም እንደቀጠለ ነው ተብሏል። ይህ በዚህ እንዳለ የተለያዩ ሀገራት በሱዳን የሚገኙ ዜጎቻቸውን ለማስወጣት ትረቶች ላይ ይገኛሉ። ከካርቱም ዜጎቻቸውን በአየር ትራንስፖርት ለማውጣት ያልተሳካላቸው ሀገራት በየብስ ትራንስፖርት በኢትዮጵያ ድንበር በኩል እያስወጡ መሆኑን ሰምተናል። ሀገራቱ…
Read More
በአዲስ አበባ በ1 ነጥብ 5 ቢልየን ብር ወጪ የተገነባው “ስቴይ ኢዚ ፕላስ” ሆቴል ወደ ሥራ ሊገባ ነው

በአዲስ አበባ በ1 ነጥብ 5 ቢልየን ብር ወጪ የተገነባው “ስቴይ ኢዚ ፕላስ” ሆቴል ወደ ሥራ ሊገባ ነው

በአዲስ አበባ ከአዲሱ ገበያ ከፍ ብሎ እንጦጦ መስመር ላይ የተገነባው፤ "ስቴይ ኢዚ ፕላስ" ሆቴል ከኹለት ሳምንታት በኋላ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ የሆቴሉ ስራ አስኪያጅ አቶ አሚር ሰኢድ እንዳሉት ሆቴሉ በጥንዶቹ ዳግማዊ መኮንን እና ህይወት አየለ ባለቤትነት የተገነባ ሲሆን ሆቴሉ ከአንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ ፈጅቷል ብለዋል፡፡ በአምስት ዓመት ውስጥ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ታስቦ ግንባታው የተጀመረው ይህ ባለ ስምንት ወለል ህንጻ ኮሮና ቫይራ ተጨምሮበት በስምንት ዓመት ውስጥ መጠናቀቁን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ሆቴሉ በባለ አምሰት ኮከብ ደረጃ መገንባቱን የተናገሩት ደግሞ የሆቴሉ ባለቤት እና ማኔጂንግ ዳይሬክተር ወይዘሮ ሂወት አየለ ናቸው፡፡ እንደ ወይዘሮ ሂወት ገለጻ ሆቴሉ በአጠቃላይ 103 ክፍሎች፣ ከ15 እስከ 1 ሺሕ…
Read More
በኢትዮጵያ ተጨማሪ አምስት ቴሌቪዥኖች ወደ ስርጭት ሊገቡ ነው ተባለ

በኢትዮጵያ ተጨማሪ አምስት ቴሌቪዥኖች ወደ ስርጭት ሊገቡ ነው ተባለ

አምስት የንግድ የቴሊቪዥን ጣቢያዎች የስርጭት ፈቃድ ሊሰጣቸው እንደሆነ ተገልጿል፡፡ አምስት የንግድ የሳተላይት ቴሌቪዥን ብሮድካስት አገልግሎት ጣቢያዎች ፈቃድ እንዲሰጣቸው  መወሰኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን አስታውቋል። ፈቃዱን የሚያገኙት ጎህ ቴሌቪዥን፣ ኤፕላስ ቲቪ፣ ሸካል ቲቪ፣ ከገበሬው ቴሌቪዥን እና ኢሲኤን ቴሌቪዥን መሆናቸውን ባለስልጣኑ አስታውቋል። ፈቃድ የሚሰጣቸውም የገንዘብ አቅምና ምንጫቸው ስራውን ለማስኬድ አስተማማኝ እንደሆነ በመታመኑ ነው ያለው ባለስልጣኑ፣ አገልግሎቱን ለመስጠት ድርጅታዊ ብቃት ያላቸው መሆኑ መጣራቱ ተገልጿል፡፡ እንዲሁም የፕሮጀክት ሰነዳቸው፣ ያቀረቧቸው መሳሪያዎችና ቴክኖሎጂዎች አገልግሎቱን ለመስጠት ብቃት ያላቸው መሆናቸው ተጣርቶ መወሰኑን ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡ የንግድ ቴሌቪዥን ፈቃድ ለማገኘት የቀረቡ አመልካቾች በባለሥልጣኑ መስሪያ ቤት በመቅረብ ውል እንዲዋዋሉና ከዛሬ ጅምሮ ፈቃዳቸውን መውሰድ እንደሚችሉም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።…
Read More
ኢትዮጵያ ለሁለት የወርቅ አውጪ ኩባንያዎች ፈቀድ ሰጠች

ኢትዮጵያ ለሁለት የወርቅ አውጪ ኩባንያዎች ፈቀድ ሰጠች

ለሁለት ሀገር በቀል ኩባንያዎች የከፍተኛ ደረጃ የደለል ወርቅ ምርት ፈቃድ ተሰጥቷል። የማዕድን ሚኒስቴር ለሁለት ኩባንያዎች የከፍተኛ ደረጃ የደለል ወርቅ የማምረት ፈቃድ መስጠቱን ገልጿል። ፈቃድ የተሰጣቸው ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ እና ኢልኔት ቴክኖሎጂ ግሩፕ የተሰኙት ሀገር በቀል ኩባንያዎች ናቸው። "ቤአኤካ" ፈቃድ የተሰጠው በጋምቤላ ብሄራዊ ክልል ማጃንግ ዞን፣ ማንግሽ ወረዳ ሲሆን ለፕሮጀክቱ ከ138 ሚሊየን ብር በላይ መመደቡ ተገልጿል፡፡ ይህ ኩባንያ በሚቀጥሉት 4 ዓመታት ውስጥ 911 ሺህ ኪሎ ግራም ወርቅ ያመርታል ተብሏል። ሌላኛው ፈቃድ የተሰጠው ተቋም "ኢልኔት ቴክኖሎጂ ግሩፕ" ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አሶሳ ዞን፣ አሶሳ እና ሁዱሉ ወረዳዎች እንደሆነ ተገልጿል። ይህ ኩባንያ ለፕሮጀክቱ ከ148 ሚሊየን ብር በላይ መመደቡ አስታውቋል፡፡ የፈቃዱ የአገልግሎት ዘመን…
Read More
ኢትዮጵያ የቤት ሰራተኞችን ወደ ሳውዲ አረቢያ መላክ ጀመረች

ኢትዮጵያ የቤት ሰራተኞችን ወደ ሳውዲ አረቢያ መላክ ጀመረች

ኢትዮጵያ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ዜጎቿን ወደ ሳውዲ አረቢያ ለመላክ በምልመላ ላይ እንደሆነች ተገልጿል። የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለው የሴቶች የጅምላ ምልመላ እንደሚያሳስባቸው ተናግረዋል ። የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች የሳውዲ አረቢያ የሰብዓዊ መብት አያያዟ ደካማ እንደሆነ ገልጸዋል። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለው የሴት ሠራተኞች የጅምላ ምልመላ አሳሳቢ ነው ብለዋል፡፡ አሁንም ቢሆን በርካታ ኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች በሳውዲ አረቢያ ከሠራተኛ ሕጎች የተገለሉ እና በዘመናዊ ባርነት ስርዓት ለጥቃት የተጋለጡ ናቸው ተብሏል፡፡ “ካፋላ” በተሰኘው ስርዓት አንድ ሠራተኛ በደል ቢደርስባት እና ከአሠሪዎቿ ብትሸሽ ፓስፖርቷን ጨምሮ የተለያዩ የሰነድ መረጃዎቿን እንድታጣ እንደሚደረግ እና ይህ ስርዓት አሁንም ለውጥ እንዳልተደረገበት ተገልጿል። ‹‹ሳውዲ አረቢያ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን በዘፈቀደ በማሰር እና አሰቃቂ…
Read More