Business

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ ከሶስት ዓመት በፊት የተቀሰቃሰው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የአሜሪካንን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ይጎዳል በሚል ነበር ጦርነቱ እንዲቆም ጫና ስታደርግ የቆየችው፡፡ ይህ ጦርነት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በተደረገ የሰላም ስምምነት ቢቆምም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ግን እንደቀጠሉ ናቸው በሚል ማዕቀቡ ተራዝሟል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ እየተፈጸሙ ናቸው የተባሉት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ምስራቅ አፍሪካን እና አሜሪካንን ይጎዳል በሚል የተለያዩ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች፡፡ በዋሸንግተን ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል በኢትዮጵያ ላይ ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ ማዕቀብ የሚባል ሲሆን በፈረንጆቹ መስከረም 2021 ላይ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ማዕቀብ ተጥሎ ነበር፡፡ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ይህ ማዕቀብ ከአንድ ዓመት በፊት ለተጨማሪ አንድ ዓመት እንዲራዘም መፈረማቸው አይዘነጋም፡፡ ፕሬዝዳንቱ ፈርመውበት የነበረው…
Read More
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዮሀንስ አያሌው ከኃላፊነት ለቀቁ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዮሀንስ አያሌው ከኃላፊነት ለቀቁ

የልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዮሀንስ አያሌው ስራቸውን የለቀቁት "በፈቃዳቸውና በግል ምክንያት" መሆኑን ተናግረዋል። በተጠባባቂነት የባንኩ ምክትል ፕሬዝዳን ጌታቸው ዋቄ ሀለፊነቱን እንደተረከቡ ተገልጿል። ዮሀንስ አያሌው በስራ ዘመናቸው ባንኩ ከነበረበት ውስብስብ ችግርና ክስረት  ወደ ተሻለ አቋም እንዲመለስ ማስቻላቸውን የዘርፉ ባለሙያዎች ይመስክሩላቸዋል። በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ጠለቅ ያለ እውቀት እንዳላቸው የሚነገርላቸው ዶክተር ዮሀንስ አያሌው ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክን በምክትል ገዥነት እና በዋና ኢኮኖሚስትነት አገልግለዋል። በዚህም በገንዘብ ኢኮኖሚስትነታቸው ብዙዎች የሚያደንቋቸው ሲሆን ከአምስት አመት በፊት የኢትዮጵያ ልማት ባንክን በቦርድ አባልነት አገልግለዋል፡፡ የቀድሞው የልማት ባንኩ ፕሬዝዳንት ሀይለኢየሱስ በቀለ ሲለቁ የተኩት ዮሃንስ የባንኩ ፕሬዝዳንት በመሆን ለአራት አመታት የባንኩን ፖሊሲ  መርተዋል ሲል ዋዜማ ሬዲዮ ዘግቧል። የኢትዮጵያ ልማት ባንክን ዶክተር…
Read More
ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ የሚዘልቅ የነዳጅ መስመር ልገነባ ነው አለች

ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ የሚዘልቅ የነዳጅ መስመር ልገነባ ነው አለች

የተትረፈረፈ የነዳጅ ሀብት ካላቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ደቡብ ሱዳን ከዚህ በፊት ነዳጇን በሱዳን በኩል አድርጋ ለዓለም ገበያ ስታቀርብ ቆይታለች፡፡ ሱዳን በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ መሆኗን ተከትሎ እስከ ፖርት ሱዳን የተዘረጋው የደቡብ ሱዳን ነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር በጦርነቱ ወድሞባታል፡፡ በዚህም ምክንያት ሀገሪቱ በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ ወደብ ድረስ የተዘረጋ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት ማቀዷ ተገልጿል፡፡ በቻይና አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ሲሳተፉ የነበሩት ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ ወደብ ድረስ የሚዘረጋ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ዙሪያ መክረዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ ከቻይና ብሔራዊ ነዳጅ ኮርፖሬሽን ሃላፊ ዳይ ሁሊያንግ ጋር በቤጂንግ መምከራቸውን የደቡብ ሱዳን ዜና አገልግሎት ዘግቧል፡፡ እንደ ዘገባው ከሆነ የቻይናው ነዳጅ ኮርፖሬሽን…
Read More
ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በቻይና የዲጂታል ጉብኝት እያደረጉ ነው

ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በቻይና የዲጂታል ጉብኝት እያደረጉ ነው

ሶስት ኢትዮጵያውያን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በሁዋዌ አዘጋጅነት ለስምንት ቀናት በሚቆይ የዲጂታል ጉብኝት እየተሳተፉ ሲሆን ጉብኝቱ በቻይና ሼንዘን ተጀምሮ ቤጂንግ ላይ የሚጠናቀቅ ይሆናል። ለተመረጡ የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ቴክ ፎር ጉድ “Huawei Seeds for the Future (SFTF) Tech 4 Good” ያለፈው ዓመት ሰልጣኞች የተዘጋጀው ጉብኝቱ ነሐሴ 26 ተጀምሮ እስከ ጳጉሜ 3, 2016 ዓ.ም ድረስ ይቀጥላል። ጉብኝቱ ለተማሪዎች የቻይናን ዲጂታል መልከዓ ምድር ለመቃኘት፣ የአይሲቲ ክህሎት እና የቴክኖሎጂ ጅምሮችን ለማዳበር፣ እንዲሁም ተማሪዎቹ ስለሚሰሯቸው ስራዎች ግንዛቤ እንዲኖራቸው እና ከኢንዱስትሪ ኃላፊዎች ጋርም ውይይት እንዲያደርጉ ልዩ እድል ይሰጣል። ተማሪዎች በዚህ ስልጠና እንዲሳተፉ ለማድረግ የማጣራት ሂደትን ያለፉ ሲሆን ከ2023 የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ቴክ ፎር ጉድ ፕሮግራም ተሳታፊዎች…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ መብረር አቆመ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ መብረር አቆመ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው መግለጫ ከነገ ነሀሴ 28 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን በረራ እንደሚያቆም አስታውቋል፡፡ ከአዲስ አበባ ወደ አስመራ እና ከአስመራ ወደ አዲ አበባ የሚደረጉ በረራዎችን አቋርጫለሁ ያለው አየር መንገዱ በኤርትራ ያለው አሰራር አስቸጋሪ እና ከቁጥጥሩ ውጪ መሆኑ ለበረራው መቋረጥ በምክንያትነት ተጠቅሷል፡፡ ጉዞ ለማድረግ ቲኬት የገዙ መንገደኞችም በመረጡት አየር መንገዶች እንዲበሩ እንደሚያደርግ እና የዋጋ ጭማሪ እንደማያደርግም አየር መንገዱ ገልጿል፡፡ ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ከመስከረም 30 በኋላ ወደ አስመራ እንዳይበር መከልከሏ ይታወሳል፡፡ የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከአንድ ወር በፊት ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ በሚጓዙ ተጋዦች ላይ “የተደራጀ እና ስልታዊ የሻንጣ ስርቆት፣ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ፣…
Read More
ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ “የእልል ያልኩ ሐበሻ” የብራንድ አምባሳደር ሆኖ ተመረጠ

ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ “የእልል ያልኩ ሐበሻ” የብራንድ አምባሳደር ሆኖ ተመረጠ

ወጣቱ ድምፂዊ የሀበሻን ባህላዊ እሴቶችን እንዲሁም ሐበሻ ቢራን እንዲያስተዋውቅ የተመረጠው በሐበሻ ቢራ ፉብሪካ  ነው። በአንድ አልበም እና በተለያዮ ነጠላ ዜማዎች  ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው  ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ በመመረጡ የሀበሻ መገለጫ የሆኑ እሴቶች በዓለም አደባባይ ጎልተው እንዲወጡ ይሰራል። "እልል ያልኩ ሀበሻ " በሐበሻ ቢራ አዘጋጅነት የደመቀ ዝግጅት ተካሄዷል። በቃና ዌርሀውስ በተዘጋጀው በአይነቱ ለየት ያለ ፐሮግራም  የኢትዮያዊያን ባሀል፤ ዕሴት፤ማንነት እና ወግ በተለያዩ ክዋኔዎች ባህላዊውን ከዘመነኛው ጋር ያሰናሰኑ ዝግጅቶች ቀርበዋል። በዚህም በምግብ አዘገጃጀት፤በፋሽን ትርዒት፤ በሙዚቃ እና በሌሎች የጥበብ ስራዎች ባሀላዊው ከዘመናዊ ጋር በማሠናሠል ስራ የበረቱ  ባለሞያዎች ስራዎቻቸውን አቅርበዋል። የዝግጅቱ ዓላማም የሀበሻ መገለጫ የሆኑ አለባበሰ፣ምግብ ዝግጅት ፣ሙዚቃ እና የመሳሰሉትን በተለያዩ ሀገረኛ መድረኮች…
Read More
ኢትዮጵያ ከአንድ ወር በኋላ ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ሀይል መሸጥ እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ ከአንድ ወር በኋላ ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ሀይል መሸጥ እንደምትጀምር ገለጸች

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሀይል የማመንጨት አቅም በዕጥፍ ጨምሯል ተብሏል ኢትዮጵያ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ የምታመነጨውን የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ከእጥፍ በላይ ማሳደጓን አስታወቀች። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ሥራ አስፈጻሚ አሸብር ባልቻ በሰጡት መግለጫ በቅርቡ ሁለት ተጨማሪ ተርባይኖች አገልግሎት በመጀመራቸዉ ከግድቡ የሚመረተዉ የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ወደ 1 ሺሕ 550 ሜጋዋት ከፍ ብሏል። ከዚሕ ቀደም ሥራ የጀመሩት ሁለት ተርባይኖች እያንዳዳቸዉ 375 ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሲያመነጩ ቆይተዋል፡፡ ሰሞኑን የተመረቁት ሁለት ተጨማሪ ተርባይኖች ደግሞ እያንዳዳቸዉ 400 ሜጋዋት ኃይል እንደሚያመነጩ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ ከግብፅና ሱዳን ጋር የሚያወዛግባትን ግዙፍ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ በአባይ ወንዝ ላይ መገንባት የጀመረችዉ ከመጋቢት 2003 ዓ.ም ጀምሮ ነበር። ይህ የአፍሪካ ትልቁ ግድብ በ2014 ዓ.ም ላይ…
Read More
በአዲስ አበባ ያለው ከባድ አየር ንብረት የአውሮፕላን በረራዎችን አስተጓጎለ

በአዲስ አበባ ያለው ከባድ አየር ንብረት የአውሮፕላን በረራዎችን አስተጓጎለ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲስ አበባ በተከሰተው ከፍተኛ ጭጋጋማ አየር ምንክንያት ወደ ሌላ አየር ማረፊያዎች እያዘዋወረ መሆኑን አስታወቀ በአዲስ አበባ በተከሰተዉ ከፍተኛ ጭጋጋማ አየር አብዛኛው በረራዎች ቦሌ አዉሮፕላን ማረፊያ ሊያርፍ ባለመቻሉ ምክንያት ወደ ሌላ አየር ማረፊያዎች እንዲቀየሩ መደረጉን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል ። አየር መንገዱ እንደገለፀው ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ባለዉ ከፍተኛ ጭጋግ ( ጉም) ምክንያት የአየር ማረፊያዎችን ወደ ሌላ ቦታ እያዘዋወረ መሆኑን እና ይህም በሀገር ዉስጥ እና በአለም አቀፍ በረራዎች ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል ብሏል። በተጓዦች ላይ ለደረሰዉ መጉላላት ይቅርታ የጠየቀው አየር መንገዱ በተጓዦች ላይ ሊደርሱ የሚችሉ መጉላላቶችን ለመቀነስ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አውሮፕላን ጣቢያ…
Read More
ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ያሉ የዲፕሎማሲ ተቋማት በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖችን እንዳያስገቡ ከለከለች

ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ያሉ የዲፕሎማሲ ተቋማት በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖችን እንዳያስገቡ ከለከለች

ኢትዮጵያ በሀገሪቱ የሚገኙ ሁሉም የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን እንዳያስገቡ እገዳ ጥላለች፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ የሚገኙ ሁሉም ዲፕሎማቲክ እና ሚሲዮኖች የነዳጅ መኪናዎችን እንዳያስገቡ እገዳ የጣለች ሲሆን በምትኩ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ማስመጣት ብቻ እንዳለባቸው አሳስቧል። የዉጪ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በአዲስ አበባ ለሚገኙ የዲፕሎማቲክ እና የቆንስላ ሚስዮኖች፣ ለቀጠናው እና ለአለም አቀፍ ድርጅቶች በፃፈው ደብዳቤ " የተወሰደው እርምጃ ኢትዮጵያ የበካይ ጋዝ ልዕቀት ቅነሳና ወደ ታዳሽ ኃይል ለመሸጋገር ካላት ቁርጠኝነት የተነሳ መሆኑን" አስረድተዋል ። በዚህም የዲፕሎማሲ መብት ያላቸው ሁሉ ተሽከርካሪዎችን ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ የተሰጠውን አቅጣጫ አክብረዉ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን ብቻ ማስመጣት ይጠበቅባቸዋል ብሏል። ኢትዮጵያ ከመጋቢት 2016 ዓ.ም ጀምሮ በነዳጅ የሚሰሩ የግል አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ወደ…
Read More
አሚአ ኩባንያ በ620 ሚሊዮን ዶላር የንፋስ ሀይል ማመንጫ ሊገነባ ነው

አሚአ ኩባንያ በ620 ሚሊዮን ዶላር የንፋስ ሀይል ማመንጫ ሊገነባ ነው

ኢትዮጵያ በ620 ሚሊዮን ዶላር የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለመገንባት ከአለም አቀፉ አሚአ ፓወር ኩባንያ ጋር ተስማምታለች፡፡ ስምምነቱ በዱባይ ከአራት ቀናት በፊት የኢትዮጵያ ኤሌክተሪክ እና አሚአ ኩባንያ ሀላፊዎች መካከል ተካሂዷል፡፡ ኢትዮጵያ በሶማሌ ክልል ለሚገነባዉ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ ለማልማት በታዳሽ ኃይል ልማት ላይ ከተሰማራው እና መቀመጫዉን የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ኩባንያ ካደረገዉ ከአሚአ ፓወር ጋር ስምምነት አድርጓል። በታዳሽ ኃይል ልማት፣ ግንባታና አስተዳደር ዘርፍ የተሰማራው አሚአ ፓወር በአይሻ አንድ የንፋስ ኃይል 300 ሜጋ ዋት አመንጭቶ ለኢትዮጵያ ለመሸጭ ነው ሥምምነቱን የፈረመው። በኢትዮጵያ 300 ሜጋ ዋት የንፋስ ሃይል ፕሮጀክትን ለማልማት እና ለማንቀሳቀስ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ጋር የኃይል ግዢ ስምምነት እና የትግበራ ስምምነት መፈራረሙን ያስታወቀው…
Read More