ዜና

ኢትዮጵያ በአዲሱ የሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ስስ ሳትካተት ቀረች

ኢትዮጵያ በአዲሱ የሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ስስ ሳትካተት ቀረች

የተባበሩት መንግስታ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ልዑክ (አትሚስ) የስራ ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ (አውሶም) እንዲተካው ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ ምክር ቤቱ በትላንትናው ዕለት ባደረገው ስብሰባ አልሸባብን ለመዋጋት በሚደረገው ጥረት የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪዎች ከቀናት በኋላ አዲሱን ተልዕኮ እንዲጀምሩ ፈቅዷል፡፡ ውሳኔውን ለማጸደቅ ትላንት በተደረገው ድምጽ አሰጣጥ ላይ ከ15 አባል ሀገራት በ14ቱ ድጋፍ ያገኝ ሲሆን ለሰላም አስከባሪ ሀይሉ በሚደረገው የገንዘብ ድጋፍ ቅሬታ ያነሳቸው አሜሪካ በድምጸ ተአቅቦ ወጥታለች፡፡ ቀደም ሲል በጸደቀው የምክር ቤቱ የውሳኔ ሀሳብ መሰረት በሶማሊያ የሚሰማሩ የሰላም አስከባሪ ሀይሎችን 75 በመቶ ወጪ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንደሚሸፍን ይገልጻል፡፡  በምክር ቤቱ ድምጽ መስጠት የማይችሉት ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ…
Read More
በኢትዮጵያ የስራ ማቆም አድማ ሊደረግ እንደሚችል ተገለጸ

በኢትዮጵያ የስራ ማቆም አድማ ሊደረግ እንደሚችል ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን አባል ማህበራት የሰራተኞች ጥያቄ ካልተመለሱ  ስራ የማቆም አድማና ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ሲል አስጠንቅቋል፡፡ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል በመንግስት እንዲወሰንና ከደመወዝ ላይ የሚቆረጠው ከፍተኛ_ግብር እንዲቀንስ መንግስት በተደጋጋሚ ቢጠየቅም እስካሁን ምላሽ አልሰጠም ተብሏል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በኋላ ሰራተኞች ወደ ስራ ማቆም አድማና ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያመሩ እንደሚችሉ ማህበራቱ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን የኢትዮጵያን ሰራተኞች ይወክላሉ ከሚባሉት አባላቱ ጋር ባሳለፍነው ሳምንት አድርጎት በነበረው ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ አባላቱ በሰራተኞች ጥቅም ዙሪያ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል፡፡ ማህበራቱ በመግለጫቸው እስካሁን ስናነሳቸው የነበሩ ጥያቄዎቻችን በመንግስት ባለመመለሳቸው ከዚህ በኋላ የስራ ማቆም አድማ ለማድረግ እንዲሁም በሰላማዊ ሰልፍ ለመጠየቅ እንገደዳለን ማለታቸውን የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን የውጭና ህዝብ…
Read More
ኢትዮጵያ በሶማሊያ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ በሶማሊያ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች

ከአንድ ዓመት በፊት ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ጋር የወደብ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡ ስምምነቱን ተከትሎ ሶማሊያ ሉዓላዊነቴን የሚጥስ ነው በሚል ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት አቋርጣም ነበር፡፡ የሁለቱም ሀገራት ወዳጅ የሆነችው ቱርክ በአንካራ የውይይት መድረክ ያዘጋጀች ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ በአንካራ መስማማታቸውን ከሁለት ሳምንት በፊት ተናግረው ነበር፡፡ በቱርክ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አደራዳሪነት የተስማሙት ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ አንዳቸው የሌላኛቸውን ሉዓላዊነት ለማክበር ኢትዮጵያም የወደብ አገልግሎት ከሶማሊያ እንደምታገኝ ተስማምተውም ነበር፡፡ ከአንካራው ስምምነት በኋላ የሶማሊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ እና የደህንነት ባለስልጣናት ወደ አዲስ አበባ መጥተው ተወያይተዋል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ሬድዋን ሁሴን የሶማሊያ ብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት…
Read More
በሐረር ከተማ 35 የባንክ ቅርንጫፎች ለኮሪደር ልማት ገንዘብ አላዋጣችሁም በሚል ታሸጉ

በሐረር ከተማ 35 የባንክ ቅርንጫፎች ለኮሪደር ልማት ገንዘብ አላዋጣችሁም በሚል ታሸጉ

የኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር በሐረር ከተማ የታሸጉ 35 የባንክ ቅርንጫፎች ተከፍተው ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ እንዲደረግ ለሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቤቱታ አቅርቧል። የክልሉ መንግስት ቅርንጫፎቹ የታሸጉት “ግንባታቸው ባላለቁ ህንጻዎች አገልግሎት እየሰጡ በመሆኑ ነው” ቢልም፤ ማህበሩ ግን ከሌሎች የንግድ ድርጅቶች በተለየ መልኩ እርምጃው በእነርሱ ላይ መወሰዱ ለክልሉ የኮሪደር ልማት የተጠየቀው መዋጮ ተግባራዊ ባለመደረጉ ምክንያት የተፈጸመ እንደሆነ “ከድምዳሜ ላይ እንዲደርስ” እንዳደረገው ገልጿል ሲል ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። በሀረሪ ክልል የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ ባንኮች የሁለት ሚሊዮን ብር “ድጋፍ” እንዲያደርጉ በደብዳቤ የተጠየቁት የዛሬ ሶስት ሳምንት ገደማ ነበር። ደብዳቤውን ለባንክ ቅርንጫፎች የጻፈው የሀረሪ ክልል የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ፤ የገንዘብ መጠኑን በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ…
Read More
አቶ ካሳሁን ፎሎ በድጋሚ የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

አቶ ካሳሁን ፎሎ በድጋሚ የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አካሂዷል፡፡ (ኢሠማኮ) በአዲስ አበባ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ኮንፌዴሬሽኑን በቀጣዮቹ 5 ዓመታት አመራሮችን መርጧል፡፡ በዚህም ላለፉት ዓመታት ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለሶስተኛ ጊዜ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋ፡፡ ኮንፌዴሬሽኑ አቶ ድሪብሳ ለገሰ እና አቶ አብዱልሐኪም ሙሰማ ምክትል ፕሬዝዳንት አድርጎ እንደመረጠም ሰምተናል፡፡ አቶ ካሳሁን ከምርጫው በኋላ ባደረጉት ንግግር በሀላፊነት የሚቀጥሉት ለመጨረሻ ጊዜ እንደሆነ በጉባኤው ላይ ገልጸዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ አክለውም መንግሥት ለሠራተኞች ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን በድጋሚ ጠይቀዋል። ካሳሁን፣ መንግሥት ሠራተኞች በሚከፍሉት የደመወዝ ገቢ ግብር ላይ ቅናሽ እንዲያደርግ ኢሠማኮ በተደጋጋሚ ሲጠይቀው ለነበረው ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጥም አሳስበዋል። በዓለማቀፍና የአገር ውስጥ ችግሮች ሳቢያ ሠራተኞች የኑሮ ውድነቱን ሊቋቋሙት ከሚችሉት በላይ…
Read More
ቴክኖ ሞባይል  በኤይ አይ የታገዙ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ምርቶቹን አስተዋወቀ

ቴክኖ ሞባይል  በኤይ አይ የታገዙ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ምርቶቹን አስተዋወቀ

ቴክኖ ሞባይል የቴክኖ ኤአይ አጋዥ መተግበሪያን እና አዳዲስ በኤይ አይ የታገዙ የቴክኖሎጂ ምርቶቹን አስተዋውቋል፡፡ ቴክኖ ሞባይል በቅርቡ ለዓለም ያስተዋወቀው የቴክኖ ኤአይ አጋዥ መተግበሪያን እና አዳዲስ በኤይ አይ የታገዙ የቴክኖሎጂ ምርቶቹን በአዲስ አበባ ይፋ አድርጓል፡፡ አዲሱ የቴክኖ ኤአይ (Tecno AI) አጋዥ ቴክ ቋንቋን ከመተርጎም አንስቶ ፎቶን በራሱ አቅም ኤዲት ማድረግ፣ የተለያዩ ድምጾችን ወደ ፅሁፍ መቀየር እና መሰል ተያያዥ ስራዎች በቀላሉ እና በፍጥነት ለመስራት የሚያስችል አጋዥ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂን ተካቶለታል ተብሏል፡፡ የቴክኖ ኢትዮጵያ ብራንድ ማናጀር አቶ አሊክ "ቴክኖ በኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ላይ ጉልህ ሚናን እየተጫወተ እንደሚገኝ" ጠቅሰዋል። አቶ አሊክ "ቴክኖ ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለህብረተሰቡ ተደራሽ መሆኑን…
Read More
ኢትዮጵያ የክሪፕቶከረንሲ ግብይትን በይፋ ከለከለች

ኢትዮጵያ የክሪፕቶከረንሲ ግብይትን በይፋ ከለከለች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ “የክሪፕቶ አሴትን”  እና የዲጂታል ገንዘብን በኢትዮጵያ መጠቀም የሚያስችል መመሪያ በቀጣይ ሊያወጣ እንደሚችል ገልጿል፡፡ የተቋሙ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ እንደገለጹት ብሔራዊ ባንክ የክሪፕቶ ከረንሲ መመሪያውን የሚያወጣው በማዕከላዊ ባንኪንግ፣ በገንዘብ ፖሊሲ እና በገንዘብ አስተዳደር  ያሉ ዓለም አቀፍ ሁኔታዎችን እያየ መሆኑን ተናግረዋል።  የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከ16 ዓመት በፊት የወጣውን እና በስራ ላይ ያለውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅን አጽድቋል፡፡ በምክር ቤቱ ተገኝተው ከፓርላማ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡት አቶ ማሞ አዲሱ አዋጅ ካካተታቸው አዳዲስ ድንጋጌዎች መካከል ክሪፕቶ ከረንሲ እና የዲጂታል ገንዘብን መጠቀም የተመለከቱት ይገኙበታል፡፡ የጸደቀው አዋጅ “አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ብሔራዊ ባንክ ካልፈቀደ በስተቀር፤ ክሪፕቶ ከረንሲ ወይም ሌላ ማንኛውንም ዲጂታል…
Read More
ፕሬዚዳንት ማክሮን ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ ሊመጡ ነው ተባለ

ፕሬዚዳንት ማክሮን ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ ሊመጡ ነው ተባለ

ፕሬዝዳንት ማክሮን በአዲስ አበባ ቆይታቸው በእድሳት ላይ ያለውን ብሔራዊ ቤተ መንግሥት ይመርቃሉ ተብሏል የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከአምስት ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አፍሪካ ቀንድ ይመለሳሉ ተብሏል፡፡ ፕሬዝዳንቱ የፊታችን ሐሙስ ማለትም ታህሳስ 11 ቀን ጀምሮ በኢትዮጵያ እና ጅቡቲ ጉብኝት እንደሚያርጉ አፍሪካን ኢንተለጀንስ ዘግቧል። በዚህ ጉብኝት ፕሬዝዳንት ማክሮን አዲስ የታደሰውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መንግስትን ይመርቃሉ ተብሏል፡፡ ብሔራዊ ቤተ መንግስት ላለፉት 18 ወራት ሰፊ እድሳት የተደረገለት ሲሆን ከሚቀጥለው ሳምንት በኋላ ለጎብኚዎች ክፍት ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል። ቤተ መንግሥቱ ከ1955 ጀምሮ ዓ.ም የአፄ ኃይለ ሥላሴ ቤተ መንግስት የሚል ስያሜ ተሰጥቶት የነበረ ሲሆን ላለፉት ዓመታት የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ይፋዊ መኖሪያ ሆኖ እና የመንግሥት ሥራ የሚካሄድበት ቦታ…
Read More
ኢትዮጵያ በቱርኩ ያፒ መርከዚ የባቡር ግንባታ ኩባንያ ላይ ክስ መሰረተች

ኢትዮጵያ በቱርኩ ያፒ መርከዚ የባቡር ግንባታ ኩባንያ ላይ ክስ መሰረተች

የቱርኩ ያፒ መርከዚ ኩባንያ በኢትዮጵያ የጀመረውን የባቡር መስመር ግንባታ ሳያጠናቅቅ ከሀገር ወጥቷል ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣ የቱርኩ ተቋራጭ ያፒ መርከዚ ኩባንያ የአዋሽ-ወልድያ-መቀሌ የባቡር ሐዲድ ግንባታን ሳያጠናቅቅ በመውጣቱ 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ካሳ እንዲከፍለው ክስ መመስረቱ ተገልጿል፡፡ ያፒ መርከዚ የተሰኘው የቱርክ ስራ ተቋራጭ ኩባንያ በ2007 ዓ.ም 392 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የባቡር መስመር ግንባታ በማካሄድ ላይ ነበር፡፡ ይህ የባቡር መስመር የመካከለኛ እና ሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች ከጅቡቲ ወደብ ጋር የተሳለጠ የትራንስፖርት እንቅስቀሴ እንዲኖራቸው ታስቦ በመገንባት ላይ ነበር፡፡ ከቱርኩ ኤግዚም ባንክ በተገኘ 1 ነትብ 9 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ግንባታው እየተካሄደ የነበረው ይህ የባቡር መስመር ሊጠናቀቅ ጥቂት መሰረተ ልማቶች ሲቀሩት በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት…
Read More
በደን አጠባበቅ ላይ የተሻለ የፈጠራ ስራ ያቀረቡ ወጣቶች ተሸለሙ

በደን አጠባበቅ ላይ የተሻለ የፈጠራ ስራ ያቀረቡ ወጣቶች ተሸለሙ

ውድድሩ የኢትዮጵያ አየር ንብረት ለውጥ ትብብር፣ኢንፉሌንሰርስ እና ቬንደንስ የተሰኙ ተቋማት በጋራ አዘጋጅተውታል፡፡ ሶስቱ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሚሰሩት ተቋማት ከሁለት ወራት በፊት ወጣቶች በደን አጠባበቅ ዙሪያ በኢሴይ ራይቲንግ፣ ኢንፎ ግራፊ እና ቪዲዮ የታገዘ ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርበው ነበር፡፡ የኢንፉሌንሰርስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ናሆም ፈቃዱ እንዳሉት በተደረገው ማስታወቂያ መሰረት 80 ወጣቶች በውድድሩ ላይ እንደተሳተፉ ተናግረዋል፡፡ ከሁሉም ተወዳዳሪዎች ውስጥ ከአንድ እስከ ሶስተኛ ደረጃ የወጡ ወጣት አሸናፊዎች  ከ10 ሺህ እስከ 20 ሺህ ብር ሽልማት ተሸልመዋል፡፡ ወጣት ናሆም እንዳሉት ተቋማቸው ኢንፉሌንሰርስ ሁሉም ሰው ለአካባቢ ጥበቃ የራሱን ድርሻ እንዲወጣ በሚል መቋቋሙን ተናግረዋል፡፡ ለአካባቢ ጥበቃ የራሳቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት ለሚፈልጉ ሰዎች ነው የተቋቋመው፣የአየር ንብረት ለውጥ የባሰ ጉዳት የሚያደርሰው…
Read More