31
Jan
የኢትዮጵያ ሐገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሁሉን አቀፍ የሆነ ብሔራዊ ምክክር ለማድረግና ከዚህ በፊት ይነሱ የነበሩ ትርክቶች መቋጫ እንዲያገኙ በሚል ነበር በ2014 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተቋቁሞ ስራ የጀመረው፡፡ በዚህም ባለፉት ሶስት ዓመታት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ገብቶ የአጀንዳ መለየትና ሌሎች እንቅስቃሴዎችንም በመስራት ላይ ይገኛል። ኮሚሽኑ ባለፉት ዓመታት አዲስ አበባን ጨምሮ በሲዳማ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሊ፣ አፋር፣ጋምቤላ፣ አሶሳ፣ ደቡብ ምዕራብ ፣ ኦሮሚያ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች አጀንዳዎችን መለየቱን አስታውቋል፡፡ ይህን ተከትሎ ኢትዮ ነጋሪ የሲዳማ ክልል የሕብረተሰብ ክፍሎች በአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ላይ ያላቸውን ዕምነት እና በኮሚሽኑ በአጀንዳነት እንዲካተት ስለሚፈልጓቸው ጉዳዮች ዙሪያ ቃለ መጠይቅ አድርጓል፡፡ የ19 ዓመቷ ተማሪ ምህረት ከበደ የሐዋሳ ከተማ ነዋሪ ስትሆን ሐገራዊ ምክክር ኮሚሽን…