Nationaldialogue

ሐገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከክልሎች የምክክር አጀንዳ ሊያሰባስብ መሆኑን አስታወቀ

ሐገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከክልሎች የምክክር አጀንዳ ሊያሰባስብ መሆኑን አስታወቀ

ኮሚሽኑ በክልሎች የሚያደርገውን የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የማሰባሰብ ስራ በመጪው ሳምንት እንደሚጀምር አስታውቋል። አጀንዳ የማሰባሰብ ስራው ድሬዳዋ ከተማ አሰተዳደርን ጨምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ እና በሀረሪ ክልሎች እንደሚካሄድም ነው ያስታወቀው ኮሚሽኑ። ሂደቱን በማስመልከት መግለጫ የሰጡት የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ ዘገየ አስፋው አጀንዳ በማሰባሰብ ስራው የሚሳተፉ ተወካዮች መረጣ አስቀድሞ በመጠናቀቁ ስራው ድሬዳዋን ጨምሮ በሶስቱ ክልሎች ይካሄዳል ብለዋል። ከሳምንት በኋላ ቀደም ሲል በተጠቀሱት ሶስት ክልሎች ይካሄዳል የተባለው አጀንዳ የማሰባሰብ ስራ ከአዲስ አበባው ጋር ተመሳሳይ በሆነ ሂደት እንደሚፈጸምም ነው ኮሚሽነር ዘገየ የተናገሩት። በየክልሉ ካሉ 10 የህብረተሰብ ክፍሎች የተመረጡ የወረዳ ተወካዮች ወደ ክልል ከተሞቹ እንዲመጡ ከተደረገ በኋላ ተመካክረው አጀንዳዎቻቸውን እንዲለዩና ከክልል ባለድርሻ አካላት ጋር እንዲመካከሩ ይደረጋል…
Read More
ኢሕአፓ ከሀገራዊ ምክክሩ ራሱን አገለለ

ኢሕአፓ ከሀገራዊ ምክክሩ ራሱን አገለለ

ኢሕአፓ ያስቀመጣቸው ቅድመሁኔታዎች እስከሚሟሉ ድረስ ከዛሬ ከግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ. ም ጀምሮ እራሱን ከሀገራዊ ምክክሩ ያገለለ መሆኑን አስታወቋል። ኢሕአፓ ኮሚሽኑ ሲመሠረት ከነበረው እውነታ ባሻገር የተፈጠሩ ግጭቶችን ለሀገራችን ቀውስም ወሳኝ ቦታ ያላቸው ሁኔታዎችን ለማካታት የሚያስችል ተልዕኮም ይሁን ህጋዊ ማዕቀፍ አለመኖሩ አሁን እየተካሄደ ባለበት መልኩ የኮሚሽኑ የሥራ ውጤት በአገራችን ውስጥ ዘላቂ ሰላምን ያመጣል ብሎ እንደማያምን ገልጿል። ኢሕአፓ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተስፋፉ የመጡትን ቀውሶች በአገራዊ በቅንነት ምናልባት በድርድርና ምክክር ሊፈቱ ይችሉ ይሆናል በሚል ተስፋ ለተወሰኑ ዐመቶች ሲሳተፍባቸው የቆየ መሆኑን በመግለጽ ''ገዥዎቻችን ችግሮችን በቅንነትና በከፍተኛ የሃላፊነት ስሜት ለመፍታት ከመሞከር ይልቅ አገራዊ ምክክርና መግባባትን የራሳቸውን ሥልጣን ማጠናከሪያና የዓለምአቀፉን ማኅበረሰብ ማደናገሪያ'' አድርገው ሲጠቀሙበት ቆይተዋል ብሏል። አሁን…
Read More