Nationaldialogue

የአማራ ክልል ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ተጠናቀቀ

የአማራ ክልል ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ተጠናቀቀ

የአማራ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ሲያካሄዱት የቆየው የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ተጠናቋል፡፡ የአማራ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ካለፈው እሁድ ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት ሲያካሄዱት የቆየው የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት መጠናቁን ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ የማህበረሰብ ተወካዮቹ፤ በመጪዎቹ ቀናት ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በሚደረግ የምክክር ሂደት የሚሳተፉ 270 ወኪሎቻቸውንም መርጠዋል። በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባህር ዳር በተካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ከ263 ወረዳዎች የተመረጡ ከ4,500 በላይ የሚሆኑት የማህበረሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡ አስር የማህበረሰብ ክፍሎችን የወከሉት እነዚህ የሀገራዊ ምክክር ተሳታፊዎች፤ በባህርዳር ከተማ በነበራቸው ቆይታ ከዘጠኝ እስከ 12 አባላት በሚገኙባቸው ቡድኖች ተከፋፍለው በአበይት ክልላዊ እና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ሲወያዩ ቆይተዋል። ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን…
Read More
መንግሥት በአማራ ክልል የተናጥል የተኩስ አቁም እንዲያውጅ ተጠየቀ

መንግሥት በአማራ ክልል የተናጥል የተኩስ አቁም እንዲያውጅ ተጠየቀ

እስረኞች እንዲፈቱና በክልሉ ያለው ግጭት እንዲቆምም ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ጥሪ አቅርቧል በሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕሮፌሰር) የተመራ የኮሚሽኑ ልዑክ ወደ አማራ ክልል ባህርዳር ከተማ አቅንቶ ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር ውይይት አድርጓል። የኮሚሽኑ ልዑክ ወደ አማራ ክልል ያቀናው የአማራ ክልል የአጃንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ በሚካሄድበት አስቻይ ሁኔታ ላይ ከክልሉ መንግስት ጋር ለመነጋገር ነው። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ በተገኙበት በዚህ ውይይት የኮሚሽኑ የእስካሁን ስራዎች በዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ(ፕሮፌሰር) ቀርቦ የክልሉ አመራሮች ስለ ኮሚሽኑ የስራ እንቅስቃሴ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ተደርጓል። ከኮሚሽኑ የቅርብ ጊዜ የስራ እቅዶች መካከል አንዱ በአማራ ክልል የአጀንዳ ልየታ የምክክር ምዕራፍ ማካሄድ ስለመሆኑ የኮሚሽኑ…
Read More
ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን ሀይሉን ባልሆነ ቦታ እያባከነ ይሆን?

ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን ሀይሉን ባልሆነ ቦታ እያባከነ ይሆን?

የኢትዮጵያ ሐገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሁሉን አቀፍ የሆነ ብሔራዊ ምክክር ለማድረግና ከዚህ በፊት ይነሱ  የነበሩ ትርክቶች መቋጫ እንዲያገኙ በሚል ነበር በ2014 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተቋቁሞ ስራ የጀመረው፡፡ በዚህም ባለፉት ሶስት ዓመታት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ገብቶ የአጀንዳ መለየትና ሌሎች እንቅስቃሴዎችንም በመስራት ላይ ይገኛል። ኮሚሽኑ ባለፉት ዓመታት አዲስ አበባን ጨምሮ በሲዳማ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሊ፣ አፋር፣ጋምቤላ፣ አሶሳ፣ ደቡብ ምዕራብ ፣ ኦሮሚያ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች አጀንዳዎችን መለየቱን አስታውቋል፡፡ ይህን ተከትሎ ኢትዮ ነጋሪ የሲዳማ ክልል የሕብረተሰብ ክፍሎች በአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ላይ ያላቸውን ዕምነት እና በኮሚሽኑ በአጀንዳነት እንዲካተት ስለሚፈልጓቸው ጉዳዮች ዙሪያ ቃለ መጠይቅ አድርጓል፡፡ የ19 ዓመቷ ተማሪ ምህረት ከበደ የሐዋሳ ከተማ ነዋሪ ስትሆን ሐገራዊ ምክክር ኮሚሽን…
Read More
ሐገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከክልሎች የምክክር አጀንዳ ሊያሰባስብ መሆኑን አስታወቀ

ሐገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከክልሎች የምክክር አጀንዳ ሊያሰባስብ መሆኑን አስታወቀ

ኮሚሽኑ በክልሎች የሚያደርገውን የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የማሰባሰብ ስራ በመጪው ሳምንት እንደሚጀምር አስታውቋል። አጀንዳ የማሰባሰብ ስራው ድሬዳዋ ከተማ አሰተዳደርን ጨምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ እና በሀረሪ ክልሎች እንደሚካሄድም ነው ያስታወቀው ኮሚሽኑ። ሂደቱን በማስመልከት መግለጫ የሰጡት የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ ዘገየ አስፋው አጀንዳ በማሰባሰብ ስራው የሚሳተፉ ተወካዮች መረጣ አስቀድሞ በመጠናቀቁ ስራው ድሬዳዋን ጨምሮ በሶስቱ ክልሎች ይካሄዳል ብለዋል። ከሳምንት በኋላ ቀደም ሲል በተጠቀሱት ሶስት ክልሎች ይካሄዳል የተባለው አጀንዳ የማሰባሰብ ስራ ከአዲስ አበባው ጋር ተመሳሳይ በሆነ ሂደት እንደሚፈጸምም ነው ኮሚሽነር ዘገየ የተናገሩት። በየክልሉ ካሉ 10 የህብረተሰብ ክፍሎች የተመረጡ የወረዳ ተወካዮች ወደ ክልል ከተሞቹ እንዲመጡ ከተደረገ በኋላ ተመካክረው አጀንዳዎቻቸውን እንዲለዩና ከክልል ባለድርሻ አካላት ጋር እንዲመካከሩ ይደረጋል…
Read More
ኢሕአፓ ከሀገራዊ ምክክሩ ራሱን አገለለ

ኢሕአፓ ከሀገራዊ ምክክሩ ራሱን አገለለ

ኢሕአፓ ያስቀመጣቸው ቅድመሁኔታዎች እስከሚሟሉ ድረስ ከዛሬ ከግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ. ም ጀምሮ እራሱን ከሀገራዊ ምክክሩ ያገለለ መሆኑን አስታወቋል። ኢሕአፓ ኮሚሽኑ ሲመሠረት ከነበረው እውነታ ባሻገር የተፈጠሩ ግጭቶችን ለሀገራችን ቀውስም ወሳኝ ቦታ ያላቸው ሁኔታዎችን ለማካታት የሚያስችል ተልዕኮም ይሁን ህጋዊ ማዕቀፍ አለመኖሩ አሁን እየተካሄደ ባለበት መልኩ የኮሚሽኑ የሥራ ውጤት በአገራችን ውስጥ ዘላቂ ሰላምን ያመጣል ብሎ እንደማያምን ገልጿል። ኢሕአፓ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተስፋፉ የመጡትን ቀውሶች በአገራዊ በቅንነት ምናልባት በድርድርና ምክክር ሊፈቱ ይችሉ ይሆናል በሚል ተስፋ ለተወሰኑ ዐመቶች ሲሳተፍባቸው የቆየ መሆኑን በመግለጽ ''ገዥዎቻችን ችግሮችን በቅንነትና በከፍተኛ የሃላፊነት ስሜት ለመፍታት ከመሞከር ይልቅ አገራዊ ምክክርና መግባባትን የራሳቸውን ሥልጣን ማጠናከሪያና የዓለምአቀፉን ማኅበረሰብ ማደናገሪያ'' አድርገው ሲጠቀሙበት ቆይተዋል ብሏል። አሁን…
Read More