ዜና

ከ800 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ወደ ውጭ ሀገራት መሰደዳቸው ተገለጸ

ከ800 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ወደ ውጭ ሀገራት መሰደዳቸው ተገለጸ

ባለፉት አምስት ዓመታት ከ800 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ወደ ውጭ ሀገራት ፈልሰዋል የተባለ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 78 በመቶ የሚሆኑት ወጣት ከመሆናቸውም በላይ አብዛኞቹ ሴቶች መሆናቸው ተነግሯል ። የኢትዮጵያ ዜጎች በስራ ዕድል እጦት የተነሣ በተለያዩ መተላለፊያዎች ድንበር አቋርጠው እንደሚፈልሱ የተገለፀ ሲሆን ድህነት ፣ የሰላም እጦት፣ የመነሻ ሐብት ምንጭ እጥረት ፣ የአየር ንብረት መለዋወጥና የተፈጥሮ ውድመት ዋና ዋና ገፊ ምክንያቶች እንደሆኑ ተገልጿል ። በሌላ በኩል ኢትዮጵያዊያን ድንበር አቋርጠው እንዲፈልሱ ሳቢ ከሆኑ ምክንያቶች መካከል ለራሳቸውና ቤተሰባቸው ገቢ የማመንጨት  ፍላጎት መኖር እና  የተሻለ ህይወት ፍለጋ እንደሆነ ይጠቀሳሉ ተብሏል ። የኢትዮጵያ ፍልሰተኛ ሰራተኞች ለኢትዮጵያ መልካም ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ሲሆን ሀገሪቱ ውጭ ከሚኖሩና ከሚሰሩ ዜጎቿ ዳጎስ…
Read More
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ታንዛኒያን እንደሚጎበኙ ተገለጸ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ታንዛኒያን እንደሚጎበኙ ተገለጸ

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ኬንያ ያመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በናይሮቢ ቆይታቸው ከፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በሁለትዮሽ እና አካባቢያዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደተወያዩ ሲገለጽ የተለያዩ ተቋማትንም ጎብኝተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ወደ ኬንያ ሲጓዙ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜያቸው ነው፡፡ የኢትዮጵያ እና ኬንያ ከ70 ዓመት በፊት ጀምሮ ጥብቅ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን ከአንድ ሳምንት በፊትም የኢትዮ ኬንያ ሚኒስትሮች ጉባኤ በአዲስ አበባ አካሂደዋል፡፡ ኢትዮጵያዊያን ያለ ቪዛ ወደ ኬንያ እንዲሁም ኬንያዊያን ወደ ኢትዮጵያ ያለቪዛ እንዲገቡ የሚፈቅድ የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ…
Read More
ኢትዮጵያ ለተረጂዎች ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

ኢትዮጵያ ለተረጂዎች ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

በኢትዮጵያ እያሻቀበ ላለው የተረጂዎች ቁጥር ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ እንደሚያስፈልግ መንግስት አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ ምክንያቶች ለተፈናቀሉ ዜጎች የምግብ ርዳታ ለማቅረብ 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የኢትዮጵያ መንግሥት በጋራ ባወጡት ሪፖርት ላይ አስታውቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ከፍተኛ የሕዝብ ግንኙነት ባለሞያ አቶ አታለለ አቡሃይ፣ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ያለው የተረጅዎች ብዛት 6 ነጥብ6 ሚሊዮን መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የተፈጥሮ አደጋዎች፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ ጦርነት እና ሌሎች አደጋዎች ምክንያት የተፈናቃዮች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል፡፡ የብሪታንያ የአፍሪካ ልማት ዳይሬክተር በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ጉብኝት ካደረጉ በኋላ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም አሳሳቢ የምግብ…
Read More
ኑሮ ውድነት በመቀሌ ምን ይመስላል?

ኑሮ ውድነት በመቀሌ ምን ይመስላል?

በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመት በቆየው ጦርነት ምክንያት ከተጎዱ ክልሎች መካከል አንዱ ትግራይ ሲሆን በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች ከመሞታቸው በተጨማሪ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል፡፡ ይህ ጦርነት በደቡብ አፍሪካ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በተደረገው የፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ጦርነቱ የቆመ ሲሆን አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም ዳግም ስራ ጀምረዋል፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር ከተቋቋመ በኋላ ከፌደራል መንግስት እና ከሌሎች መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ተጎጂዎችን ለመርዳት እየተሰራም ይገኛል፡፡ ቀስ በቀስ ህይወት በትግራይ ከጦርነቱ በፊት ወደ ነበረበት ሁኔታ ለመመለስ የተለያዩ ጥረቶች እየተካሄዱ ሲሆን ኢትዮ ነጋሪ ወደ ክልሉ አምርታ በበርካታ ጉዳዮች ዙሪያ ምልከታ አድርጋለች፡፡ ከታዘብናቸው ጉዳዮች መካከል ህይወት በትግራይ መዲና መቀሌ ምን ይመስላል? የሚለው ሲሆን የኑሮ…
Read More
በባህርዳር 17 ንጹሃን ዜጎች በሀገር መከላከያ ሰራዊት ከህግ ውጪ መገደላቸው ተገለጸ

በባህርዳር 17 ንጹሃን ዜጎች በሀገር መከላከያ ሰራዊት ከህግ ውጪ መገደላቸው ተገለጸ

አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው ሪፖርት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባህር ዳር ንጹሃንን ከህግ አግባብ ውጪ ገድሏል ብሏል። ተቋሙ በአማራ ክልል ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት አስመልክቶ ሰፋ ያለ ሪፖርቱን አውጥቷል። በአቡነ ሃራ፣ ልደታ እና ሳባ ታሚት በተባሉ አካባቢዎች ከ17 በላይ ንጹሃን በመከላከያ ተተኩሶባቸው መገደላቸውን ከአይን እማኞች ማረጋገጡን የጠቆመው አምነስቲ ኢንተርናሽናል አንዳንድ ቤተሰቦቻቸው የተገደሉባቸው ሰዎች አስከሬን መውሰድ እና መቅበር ተከልክለዋል ተብሏል፡፡ ሪፖርቱ በአማራ ክልል የመከላከያ ሰራዊትና የፋኖ ታጣቂዎች ውጊያ እንደጀመሩና ከሶስት ወር በኋላ በባህር ዳር ተፈጸሙ የተባሉ ግድያዎችን ብቻ የቃኘ ነው። የኢንተርኔት አገልግሎት መዘጋት እና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ያስከተላቸው ክልከላዎች በአማራ ክልል እየተካሄደ ባለው ጦርነት የተፈጸመውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በዝርዝር…
Read More
በኢትዮጵያ ሶስት ቦታዎች በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የ24 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡

በኢትዮጵያ ሶስት ቦታዎች በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የ24 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡

በትናንትናው ዕለት በዱከም፣ በወላይታ እና ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ በደረሱ ሶስት የትራፊክ አደጋዎች ምክንያት የ24 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡ አደጋዎቹ የደረሱባቸው ኮሙንኬሽን ጽህፈት ቤቶች ባወጡት መረጃ መሰረት የትራፊክ አደጋዎቼ ሰቅጣጭ የሚባሉ ናቸው የተባለ ሲሆን በአጠቃላይ ከ24 ሰዎች ህይወት ማለፍ በተጨማሪ 20 ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል፡፡ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው ዱከም ክፍለ ከተማ የደረሰው የትራፊክ አደጋ አንድ ሲኖትራክ ተሽከርካሪ ከሁለት ሚኒባሶች እና አንድ ላንድ ክሮዘር ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ አደጋው ደርሷል ተብሏል፡፡ በዚህ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ 11 ሰዎች ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው በቢሾፍቱ ሆስፒታል በሕክምና ላይ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡ ሌላኛው የትራፊክ አደጋ የተከሰተው በአዲሱ ማዕከላዊ…
Read More
በትግራይ ክልል የኤች አይ ቪ ስርጭት ወደ ከፋ ደረጃ መሻገሩን ክልሉ አስታወቀ

በትግራይ ክልል የኤች አይ ቪ ስርጭት ወደ ከፋ ደረጃ መሻገሩን ክልሉ አስታወቀ

በትግራይ ክልል ባለው አሁናዊ ሁኔታ የህጻናት የተጓዳኝ በሽታ መድኃኒት እና   የኤች አይ ቪ መመርመሪያ ኪት  እጥረት መኖሩን የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ አሰታወቀ፡፡ የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ የዘርፈ ብዙ ምላሽ የኤች አይ ቪ  መከላከል እና መቆጣጠር ስራ ሂደት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ፍሥሀ ብርሃነ ለትግራይ ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ከሶስት አመት በፊት በኤች አይቪ ስርጭት እና መቆጣጠር የተሻለ ጤና  አፈፃፀም ነበረው ብለዋል። አሁን ላይ ግን  የኤችአይቪ ስርጭቱ ወደ ከፋ ሁኔታ ውስጥ ገብቷል። በፀጥታ እጦት ወቅት በርካታ ሴቶች እና እናቶች የመደፈር አደጋ ተጋላጭ በመሆናቸው  እንዲሁም መድኃኒት ተጠቃሚ የነበሩ ሰዎችም በመድሀኒት እጥረት በማቋረጣቸው  ለበሽታው ስርጭት መስፋፋት ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም የክልሉ ጤና ቢሮ ባደረገው ጥናት…
Read More
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 30 ንጹሃን ተገደሉ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 30 ንጹሃን ተገደሉ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃ እና ወደራ ወረዳ ሳሲት በተባለች ከተማ ህዝብ ያሳፈረ አይሱዙ ተሽከርካሪ ላይ በተፈጸመው ጥቃት 30 ሰዎች ሲገደሉ 18 ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ከአምስት ቀን በፊት ሳሲት በተባለችው ከተማ አቅራቢያ 50 ሰዎችን ያሳፈረ አይሱዙ ተሽከርካሪ መንገደኞችን ለማውረድ በቆመበት ተፈጽሟል በተባለው ጥቃት 18 ሰዎች መቁሰላቸውንም ነው የአይን እማኞችን የጠቀሰው የሪሊፍ ዌብ ዘገባ የሚያሳየው። የድሮን ጥቃቱ ሲፈጸም በአካባቢው በመከላከያ ሰራዊትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ጦርነት እንዳልነበር የተናገሩት ነዋሪዎች፥ ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላም ድሮኖች በአካባቢው ሲሽከርከሩ እንደነበር ገልጸዋል። የድሮን ጥቃቱ የተፈጸመው መከላከያ ሰራዊት እና የፋኖ ታጣቂዎች ውጊያ ከሚያደርጉበት አካባቢ በ24 ኪሎሜትር ርቀት ላይ እንደተፈጸመ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ “መጀመሪያ ከባድ ፍንዳታ ሰማን ከዚያም…
Read More
የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም መቀሌ ቅርንጫፍ ቅሬታዎችን ማየት እንዳልቻለ ተናገረ

የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም መቀሌ ቅርንጫፍ ቅሬታዎችን ማየት እንዳልቻለ ተናገረ

በትግራይ ክልል ጦርነት የቆመ ቢሆንም ከጫፍ ጫፍ ተንቀሳቅሶ መስራት አደጋች ሆኗል ተብሏል፡፡ በክልሉ ከመልካም አስተዳድር ጥያቄዎች ይልቅ የምግብ ጉዳይ ዋነኛው ችግር እንደሆነም ተገልጿል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመት በቆየው ጦርነት ምክንት ስራ አቁሞ ከነበሩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠበቃ ተቋም መቀሌ ቀርንጫፍ አንዱ ነበር፡፡ ይህ ጦርነት በደቡብ አፍሪካ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በተደረገው የፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ጦርነቱ የቆመ ሲሆን አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም ዳግም ስራ ጀምረዋል፡፡ ከታህሳስ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ሥራውን በአዲስ መልክ የጀመረው የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም መቀሌ ቅርንጫፍ በበጀት እጥረት ምክንያት ጉዳዮችን ለመመልከት አዳጋች እየሆነበት እንደመጣ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ተወካይ የሆኑት ወ/ሮ ደጋፊት ረዳ ለኢትዮ ነጋሪ ተናግረዋል። ተወካይዋ እንዳሉት…
Read More
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከ4 ዓመታት በኋላ ወደ አዲስ አበባ ሊመለስ ነው

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከ4 ዓመታት በኋላ ወደ አዲስ አበባ ሊመለስ ነው

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 እግር ኳስ ውድድር የጨዋታ ፕሮግራም ባሳለፍነው ነሀሴ ከወጣ በኋላ መስከረም 20 ቀን 2016 ዓም መጀመሩ ይታወሳል፡፡ የፕሪሚየር ሊጉ የመክፈቻ ጨዋታን ባለሜዳው አዳማ ከነማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መካከል ተደርጎም ነበር፡፡ የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ላለፉት አራት ዓመታት በአዳማ፣ ድሬዳዋ፣ሐዋሳ እና ባህርዳር ስታዲየሞች ሲካሄዱ ቆይተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ስታዲየም በእድሳት ምክንያት የፕሪሚየር ሊግ እና የብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎችን ወደ ክልል ከተሞች እንዲዞሩ የግድ ሆኖ ቆይቶም ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሼር ካምፓኒ እንደገለጸው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የመጨረሻዎቹ ሶስት ሳምንታት በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚደረግ ገልጿል። የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር መርሃ ግብርና የውድድር ሜዳዎች ይፋ ተደርገዋል። በዚህም በስታዲየሞች…
Read More