ዜና

ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ ተጠርጣሪ ኢትዮጵያዊያን ተላልፈው እንዲሰጧት ጠየቀች

ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ ተጠርጣሪ ኢትዮጵያዊያን ተላልፈው እንዲሰጧት ጠየቀች

ኢትዮጵያ በወንጀል የምትፈልጋቸውን ሰዎች አሜሪካ አሳልፋ እንድትሰጣት ጥያቄ አቅርባለች፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ  ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር ተወያይተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከአሜሪካው ኤፍ.ቢ.አይ (FBI) ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር አምባሳደሩ የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ኮሚሽነሩ በውይያታቸው ወቅት ጠይቀዋል ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያ በተለይም በአሜሪካን ሀገር እየኖሩ የሀገሪቱን ሰላም እያወኩ ነው በሚል የምትጠረጥራቸውን ሰዎች ተላልፈው እንዲሰጧት ለአምባሳደሩ ጥያቄ እንዳቀረቡም ተገልጿል፡፡ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በአሜሪካን መንግሥት የሚፈለጉ ወንጀለኞችን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አሳልፎ በመስጠት ላበረከተው አስተዋፅኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ተብሏል፡፡ አምባሳደሩ አክለውም ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ተመሳሳይ ድጋፎችን እንድታደርግ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል ሲል የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ኢትዮጵያ ከአሜሪካ…
Read More
ኢትዮጵያ ምዕራባዊ ሀገራት በቡድን መግለጫ እንዳስፈራሯት ገለጸች

ኢትዮጵያ ምዕራባዊ ሀገራት በቡድን መግለጫ እንዳስፈራሯት ገለጸች

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብዩ ተድላ በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ 18 ምዕራባውያን ሀገራት ኢምቢሲዎች ‘የዓለም የፕሬስ ነጻነት ቀንን’ አስመልክተው ባሳለፍነው ሳምንት ባወጡት የጋራ መግለጫ የኢትዮጵያን የጋዜጠኞች አያያዝ ተችተዋል። በኢትዮጵያ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እንዲከበር ከጠየቁ ሀገራት መካከልም አሜሪካ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ብሪታንያ፣ ጀርመን፣ ስዊድን፣ ቤልጂየም፣ ኖርዌይ፣ ስፔን፣ ኔዘርላንድ እና ሌሎችም ይገኛሉ፡፡ ሀገራቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ጋዜጠኞች ስራቸውን በመስራታቸው “ማስፈራሪያ እና እስር ይደርሰባቸዋል” ሲሉ በመግለጫቸው ላይ ጠቅሰውም ነበር። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይህን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ ምዕራባዊን ሀገራት በቡድን መግለጫ በማውጣት ሊያስፈራሩኝ ሞክረዋል ስትል አስታውቃለች፡፡ "ኢትዮጵያ መግለጫውን ካወጡት እያንዳንዳቸው ሀገራት ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት አላት፣ ግንኙነታችን…
Read More
በኢትዮጵያ በጎርፍ አደጋ አንድ ሚሊዮን ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ በጎርፍ አደጋ አንድ ሚሊዮን ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ በጎርፍ አደጋ ምክንያት አንድ ሚሊዮን የሚሆኑ ሠዎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ገለጸ ኢትዮጵያ ካሏት ሦስት ወቅቶች ውስጥ አንዱ የሆነውና አራት ወራትን የሚይዘው የበልግ ወቅት በደቡብ አጋማሽ ለሚገኙ የአገሪቱ አካባቢዎች ዋነኛ የዝናብ ወቅት ነው። ከየካቲት እስከ ግንቦት ያሉትን ወራቶችን በሚሸፍነው የበልግ ወቅት ለሶማሌ፣ ጉጂ፣ ቦረና፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ኢትዮጵያና ለደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ ክፍሎች 55 በመቶ የዝናብ ስርጭታቸውን በዚህ ወቅት ያገኛሉ። የበልግ ወቅት ለምስራቅና ደቡብ ትግራይ፣ ለሰሜንና ደቡብ ወሎ ዞኖች፣ ለአማራና ኦሮሚያ ሰሜን ሸዋ ዞኖች፣ እንዲሁም አዲስ አበባን ጨምሮ ለመካከለኛው የአገሪቱ አካባቢ፣ ለምስራቅ አካባቢዎች (ሀረርና ድሬዳዋ) ሁለተኛ የዝናብ ወቅት ተደርጎ ይወሰዳል። የኢትዮጵያ ሚትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የ2016 ዓ.ም. የበልግ ወቅት በተለይም ዋነኛና…
Read More
ህወሃት ታጣቂዎቹ በሱዳን ጦርነት እየተሳተፉ ነው መባሉን አስተባበለ

ህወሃት ታጣቂዎቹ በሱዳን ጦርነት እየተሳተፉ ነው መባሉን አስተባበለ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዛሬ ባወጣው መግለጫ "የህወሓት ኃይሎች" ከሱዳን ጦር ጎን በቅጥረኝነት ተሰልፈው ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ጋር እየተዋጉ ነው መባሉን አስተባብሏል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች በትናትናው እለት ባወጣው መግለጫ የህወሓት ኃይሎች ከሱዳን ጦር እና ተባባሪ ሚሊሻዎች ጋር ሆነው እየተዋጉት እንደሆነ ማረጋገጡን መግለጹን ተከትሎ ነው። የሱዳን ጦርነት ከተጀመረበት ከሚያዝያ 2023 ወዲህ የሱዳን ጦር የውጭ ቅጥረኞችን እርዳታ እየፈለገ ነው የሚል ክስ ያቀረበው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ጦር፣ በጦርነት ወቅት ተገድለው የተገኙ ቅጥረኞችን መመዝገቡን ጠቅሷል። የህወሓት ኃይሎች ከሱዳን ጦር ጎን ተሰልፈው  እየተዋጉ ነው የሚለውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች "መሰረተ ቢስ ክስ" በጽኑ እንደሚያወግዝ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ገልጿል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደገለጸው ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች…
Read More
ኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት የማይከበርባት ሀገር ናት መባሏን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት የማይከበርባት ሀገር ናት መባሏን ውድቅ አደረገች

የኢትዮጵያ መንግስት ምዕራባውያን በፕሬስ ነጻነት አያያዝ ዙሪያ ያቀረቡበትን ትችት እንደማይቀበለው አስታውቋል፡፡ ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ 18 ምዕራባውያን ሀገራት ኢምቢሲዎች 'የዓለም የፕሬስ ነጻነት ቀንን' አስመልክተው ባወጡት የጋራ መግለጫ የኢትዮጵያን የጋዜጠኞች አያያዝ ተችተዋል። በኢትዮጵያ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እንዲከበር ከጠየቁ ሀገራት መካከልም አሜሪካ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ብሪታንያ፣ ጀርመን፣ ስዊድን፣ ቤልጂየም፣ ኖርዌይ፣ ስፔን፣ ኔዘርላንድ እና ሌሎችም ይገኛሉ፡፡ ሀገራቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ጋዜጠኞች ስራቸውን በመስራታቸው "ማስፈራሪያ እና እስር ይደርሰባቸዋል" ብለዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይህን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ ሀገራቱ በኢምባሲዎቻቸው በኩል ያወጡትን መግለጫ እንደማይቀበለው ገልጿል። ኢትዮጵያ ከሁሉም አጋሮቿ እና ባለድርሻ አካላት ጋር ገንቢ የሆነ ንግግር ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን የገለጸው ሚኒስቴሩ "አባታዊ ወደሆነ መግለጫ ማምራት የሁለትዮሽ ግንኙነት…
Read More
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ተጨማሪ ማስፋፊያ አደርጋለሁ አለ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ተጨማሪ ማስፋፊያ አደርጋለሁ አለ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ተጨማሪ ማስፋፊያ አደርጋለሁ አለ፡፡ ኢትዮጵያ ለውጭ የቴሌኮም አገልግሎት ሰጪ በሯን መክፈቷን ተከትሎ ነበር ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ወደ አዲስ አበባ የመጣው፡፡ ድርጅቱ ዓለም አቀፍ አጋርነት ለኢትዮጵያ በሚል ሰኔ ወር 2013 ዓ.ም ላይ በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ህጋዊ ፍቃድ ከተቀበለ ከአንድ ዓመት በኋላ ስራ ጀምሯል፡፡ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለአል ዐይን እንዳስታወቀው በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ውስጥ ለኔትወርክ ማስፋፊያ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር መድቤያለሁ ብሏል፡፡ ተቋሙ አክሎም በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎችበተጠቀሱት ዓመታት ውስጥ 5 ሺህ አዳዲስ የኔትወርክ ማማዎችን እንደሚተክልም አስታውቋል፡፡ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በተደረገ የሁለትዮሽ ስምምነት የኔትወርክ አገልግሎቱን ለደንበኞቹ እየሰጠ መሆኑን ያሳወቀው ሳፋሪ ኮም ቀስ በቀስ የራሱን የኔትወርክ…
Read More
ኢትዮጵያ የጉበት በሽታ እየተስፋፋባቸው ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗ ተገለጸ

ኢትዮጵያ የጉበት በሽታ እየተስፋፋባቸው ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗ ተገለጸ

የዓለም ጉበት በሽታ ጉባኤ በፖርቹጋል ተካሂዷል፡፡ በዚህ ጉባኤ ላይ እንደተገለጸው በዓለማችን በየዕለቱ 3 ሺህ 500 ሰዎች በጉበት በሽታ እየሞቱ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ በዓለም ጤና ድርጅት የኤችአይቪ፣ ሄፓ ታይተስ እና ተላላፊ በሽታዎች ፕሮግራም ሃላፊ ሜግ ዶሂርቴ እንዳሉት በጉበት በሽታ ከሚሞቱት ውስጥ 83 በመቶዎቹ በሄፓታይተስ ቢ በተሰኘው የጉበት በሽታ የሚሞቱ ናቸው ብለዋል፡፡ በጉበት በሽታ የሚጠቁ ዜጎች እየጨመረ ነው ያሉት ሃላፊው 63 በመቶ ያህሉ ተጠቂዎች በአፍሪካ የሚገኙ ዜጎች እንደሆኑም ተናግረዋል፡፡ በየዕለቱ ስድስት ሺህ ሰዎች በጉበት በሽታ እየተጠቁ ነው ያለው የዓለም ጤና ድርጅት ተጠቂዎች በቂ ህክምና እያገኙ እንዳልሆነም አስታውቋል፡፡ በሽታው ከተስፋፋባቸው ሀገራት መካከል 75 በመቶ ያህሉ ሽታው እየተስፋፋባቸው ካሉ የዓለማችን ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ፣ቻይና፣ ባንግላዲሽ፣ ናይጀሪያ፣ሕንድ…
Read More
ኢትዮጵያ ከ6 ሺህ በላይ የስፖርት ውርርድ ቤቶችን ዘጋች

ኢትዮጵያ ከ6 ሺህ በላይ የስፖርት ውርርድ ቤቶችን ዘጋች

በአዲስ አበባ ባለፉት 9 ወራት ውስጥ ከ6 ሺህ በላይ የስፖርታዊ ውርርድ ቤቶች መታሸጋቸው ተገልጿል፡፡ የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ባለፉት 9 ወራት የህብረተሰቡን ሰላም አውከዋል ባላቸው የተለያዩ ስራዎች ላይ እርምጃ ወስጃለሁ ብሏል፡፡ የቢሮው ሀላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ የውርርድ ቤቶችን ጨምሮ ጫት ማስቃም፣ ሽሻ ማስጨስና የመሳሰሉ ጉዳዮች ይፈፀሙባቸው የነበሩና የወንጀል ድርጊት የሚታይባቸው ተግባራት ላይ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል፡፡ እነዚህ ድርጊቶች ትምህርት ቤቶች አካባቢ የመማር ማስተማር ሂደትን እያስተጓጉሉ የነበሩ ናቸውም ተብሏል። የከተማዋ አስተዳድር ከዘጋቸው ተቋማት መካከል 6 ሺህ 726 የሚሆኑ የስፖርታዊ ውርርድ  ቤቶች መታሸጋቸውን አስታውቋል፡፡ በዚህ ዘርፍ ተሰማርተው የነበሩ የንግድ ድርጅቶች ወደ ሌላ የስራ ዘርፍ እንዲቀይሩ እየተደረገ መሆኑን ሃላፊዋ አክለው ተናግረዋል፡፡ ፍርድ…
Read More
ኢትዮጵያ የትምባሆ አጫሾችን ቁጥር ለመቀነስ ከአፍሪካ ስኬታማዋ ሀገር መሆኗ ተገለጸ

ኢትዮጵያ የትምባሆ አጫሾችን ቁጥር ለመቀነስ ከአፍሪካ ስኬታማዋ ሀገር መሆኗ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከጠቅላላው ህዝብ ውስጥ አምስት በመቶ ያህሉ ሲጋራ አጫሾች እንደሆኑ አንድ ጥናት አመላከተ፡፡ በኢትዮጵያ ከ6 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ከአጫሾች በሚወጣ የትምባሆ ጭስ እንደሚቸገሩ ከዚህ በፊት የተደረገ ጥናት ያሳያል፡፡ ጥናቱ ኢትዮጵያ የሲጋራ አጫሾችን ቁጥር በመቀነስ ስኬታማ ከሆኑ የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ እንደሆነችም ጠቁሟል፡፡ ኢትዮጵያ የሲጋራ አጫሾችን ቁጥር ለመቀነስ እና የዜጎችን ጤንነት ለመጠበቅ ጠንካራ የህግ ማዕቀፍ በየጊዜው ስታዘጋጅ ቆይታለች፡፡ ከእነዚህ መካከልም ትምባሆ መግዛት የሚችሉት እድሜያቸው ከ21 ዓመት በላይ የሆኑ፣ የመዝናኛ እና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ውስጥ ትምባሆ ማጨስ እንደማይቻል፣ ሰው በተሰበሰበባቸው ቦታው ትምባሆ ማጨስ እና መስጨስ መከልከሉ አስገዳጅ ህግ መደረጋቸው ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ህጻናትን ከትንባሆ ነጻ የማደረግ እንቅስቃሴ (Campaign for Tobacco Free Kids )…
Read More
አውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ የጣለውን የቪዛ ገደብ እንዲያነሳ ተጠየቀ

አውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ የጣለውን የቪዛ ገደብ እንዲያነሳ ተጠየቀ

የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ባሳለፍነው ሰኞ ዕለት ለኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ የመስጠት ሂደት ላይ ጊዜያዊ ገደቦች ማስቀመጡን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ህብረቱ ውሳነውን ያሳለፈው የኢትዮጵያ መንግስት በአውሮፓ ህጋዊ መኖሪያ ያላገኙ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተባባሪ አልሆነም በሚል የቪዛ ገደብ ጥያለሁ ብሏል፡፡ በህብረቱ አዲስ ውሳኔ መሰረትም ኢትዮጵያዊያን ከዚህ በፊት ወደ አውሮፓ ሀገራት በ15 ቀናት ውስጥ ለቪዛ ጥያቄቸው ምላሽ ያገኙ የነበረ ሲሆን በአዲሱ ውሳኔ መሰረት ይህንን ወደ 45 ቀናት ከፍ አድርጓል፡፡ ውሳኔው የአገልግሎት እና ዲፕሎማቲክ ፓስፖርት የያዙ የቪዛ አመልካች ኢትዮጵያዊያንንም እንደሚጨምር በወቅቱ ተገልጾ ነበር፡፡ በአውሮፓ ህብረት ዋና ከተማ ብራስልስ ያለው የኢትዮጵያ ኢምባሲ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የአውሮፓ ህብረት ውሳኔ የሚያበሳጭ ነው ብሏል፡፡ ኢምባሲው በመግለጫው…
Read More