መነሻ ገፅ

ኢትዮጵያን በመጎብኘት ላይ የነበረ ሩሲያዊ ዜጋ ህይወቱ አለፈ

ኢትዮጵያን በመጎብኘት ላይ የነበረ ሩሲያዊ ዜጋ ህይወቱ አለፈ

ግለሰቡ በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማን በመጎብኘት ላይ እያለ ህይወቱ ማለፉ ተገልጿል፡፡ የ55 ዓመት እድሜ እንዳለው የተገለጸው ይህ ሩሲያዊ በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ ኩሪፍቱ ሀይቅ ላይ በመዋኘት ላይ እያሉ ህይወቱ አልፏል ተብሏል፡፡ በቢሾፍቱ ኩርፊቱ ሀይቅ በመዝናናት ላይ ከነበሩት የዉጭ ሀገር ዜጎች መካከል አንድ የሩሲያ ዜግነት ያለዉ የ 55 ዓመት ህይወቱ ማለፉን እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል። የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ እንደተናገሩት ግለሰቡን ለሞት ያበቃዉ በኩሪፍቱ ሀይቅ 150 ሜትር ጥልቀት ባለው ኩሪፍቱ ሀይቅ ዘልቆ በመዋኘት ላይ ሳለ ህይወቱ ማለፉን ተገልጿል፡፡ ግለሰቡ ባሳለፍነው እሁድ ሰኔ 18 ቀን 2015 ዓ.ም ለመዋኘት ወደ ሀይቁ ውስጠኛው ክፍል ከገባ በኋላ ሳይመለስ ቀርቷል…
Read More
ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ

ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ

ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ ከ2011 ዓ.ም ታህሳስ ወር ጀምሮ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሆነው ስራ የጀመሩት ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ በጠየና ምክንያት የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ሰማያዊ ማረጋገጫ ባለው የፌስቡክ ገጻቸው ላይ ገልጸዋል፡፡ “ባለፉት  አራት አመት ከስድስት ወራት ሶስት ህዝበ ውሳኔዎችን እና አገራዊ ምርጫን በማካሄድ እና ፓለቲካ ፓርቲዎችን በማስተዳደር የተሰጡኝን ሃላፊነቶች ህጋዊነት ፍትሀዊነት እና ቅንነትን በተከተለ ሁኔታ ለማከናወን ስጥር ቆይቻለሁ” ብለዋል። “ሆኖም ጤናዬን በሚገባ ለመጠበቅ የረጅም ጊዜ እረፍት የሚያስፈልገኝ ሆኖ በመገኘቱ ከ ነሀሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቦርድ ሰብሳቢነቴ በገዛ ፍቃዴ  መልቀቄን ለተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ጽህፈት ቤት ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም አሳውቄያለሁ” ሲሉም…
Read More
ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች

ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች

ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ በቅርቡ ባህር ዳር እና ሀዋሳ የተሰኙ ሁለት መርከቦች ለኪሳራ ዳርገውኛል በሚል መሸጡ ይታወሳል። በተሸጡት ሁለት መርከቦች ምትክም አባይ የተሰኘች አዲስ መርከብ ከቻይና መግዛቱን አስታውቋል። አዲሷ መርከብም በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ታሪክ በግዙፍነቷ አቻ የላትም የተባለ ሲሆን መርከቧ በኢትዮጵያ እጅ መግባቷን ድርጅቱ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ድርጅት በ3 ሺህ ቶን የመጫን አቅም ባላቸው መርከቦች ስራውን መጀመሩ ይታወሳል። ኢትዮጵያ የተረከበቻት አባይ የተሰኘችው አዲሷ መርከብ 63 ሺህ 229 ቶን የመጫን አቅም አላት ተብሏል። በቻይናው ያንግዡ ዳያንግ ሺፕ ቢዩልዲንግ የተገነባችው ይህች መርከብ 200 ሜትር ርዝመት እንዳላትም ተገልጿል። ይሁንና…
Read More
ተጠባቂው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቡና ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

ተጠባቂው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቡና ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

28ኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ጨዋታ የሊጉ መሪ የሆነው ቅዱስ ጊዮርጊስን ከኢትዮጵያ ቡና አገናኝቷል። በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ይህ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። እስማኤል ኦሮ አጎሮ ቅዱስ ጊዮርጊስን ቀዳሚ ያደረገች ጎል ሲያስቆጥር ብሩክ በየነ ደግሞ የኢትዮጵያ ቡናን አቻ ያደረገች ጎል አስቆጥሯል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ የሊጉ መርሐግብር ከመቻል ጋር እንዲሁም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር የሚጫወቱ ይሆናል ተብሏል። ከአራት ቀናት በኋላም ባህር ዳር ከተማ ከሲዳማ ቡና፣ አርባምንጭ ከተማ ከድሬዳዋ፣ ወላይታ ዲቻ ከወልቂጤ ከተማ፣ አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ መድህን እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከፋሲል ከነማ ይጫወታሉ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊጉን በ59 ነጥቦች ሲመራ ባህርዳር በ54 እንዲሁም ኢትዮጵያ መድን ደግሞ በ48 ነጥብ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።…
Read More
በኢትዮጵያ በአንድ ሳምንት ውስጥ 100 ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ በአንድ ሳምንት ውስጥ 100 ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በአንድ ዓመት ውስጥ ደግሞ ከ5 ሺህ በላይ ሰዎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ሰላም ጥናት ማዕከል አስታውቋል የኢትዮጵያ ፒስ ኢብዘርቫቶሪ የተሰኘው ተቋም ባወጣው ሪፖርት መሰረት በአንድ ሳምንት ውስጥ 100 ኢትዮጵያዊያን ተገድለዋል ብሏል። ከሰኔ 3 ቀን እስከ 9 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ባሉት ሰባት ቀናት ውስጥ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተፈጠሩ የፖለቲካ ግጭቶች ምክንያት 100 ሰዎች መገደላቸውን የግጭት ሁኔታ መረጃዎችን የሚያቀርበው “ኢትዮጵያ ፒስ ኦብዘርቫቶሪ” አስታውቋል። ዓለም አቀፍ የግጭት ሁኔታ እና የክስተት የመረጃ በመሰብሰብና በመተንተን የሚታወቀው “The Armed Conflict Location & Event Data Project” የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ይህንኑ ሥራ በኢትዮጵያ እንዲሠራ በፕሮጀክት ደረጃ ያቋቋመው፣ “Ethiopia Peace Observatory” የተባለው ተቋም ባወጣው ሳምታዊ ሪፖርት፤ በሳምንቱ ከተገደሉት 100…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም 52 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለጸ

ኢትዮ ቴሌኮም 52 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለጸ

ድርጅቱ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ 103 ሚሊዮን ዶላር ማስገባቱንም አስታውቋል ኢትዮ ቴሌኮም የበጀት ዓመቱን የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸሙን ልሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በሪፖርታቸው ላይ እንዳሉት ኢትዮ ቴሌኮም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 52 ቢሊዮን ብር ገቢ አግኝቷል፡፡ እንዲሁም ድርጅቱ በሰጣቸው አገልግሎቶች 103 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማስገባቱንም ስራ አስፈጻሚዋ ተናግረዋል፡፡ የመንግሥትና የንግድ ተቋማት የክፍያ ስርዓታቸውን በቴሌ ብር እንዲፈፅሙ በማድረግ 30.5 ሚሊየን በላይ የቴሌ ብር ተጠቃሚዎችን ማፍራት መቻሉም ተገልጿል፡፡ በአጠቃላይ በቴሌብር አማካኝነት ከ394 ቢሊየን ብር በላይ ግብይት መፈጸሙን ስራ አስፈጻሚዋ ተናግረዋል፡፡  በኢንተርኔት ላይ የተጣለው ገደብ ተቋሙን የሚመለከት ሳይሆን፤ በመንግሥት አካል የተጣለ ገደብ ስለሆነ ከሚመለከተው አካል በሚሰጥ ፍቃድ የሚነሳ…
Read More
ኢትዮጵያ ለአምስት የውጭ አገር ባንኮች ፍቃድ እንደምትሰጥ ገለጸች

ኢትዮጵያ ለአምስት የውጭ አገር ባንኮች ፍቃድ እንደምትሰጥ ገለጸች

አምስት የውጭ አገር ባንኮች ኢትዮጵያ ውስጥ ገብተው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸው ፈቃድ እንደሚሰጣቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ። አገር በቀል ባንኮች ከወዲሁ ከፍተኛ ዝግጅት ማድረግ እና ቀድሞ የነበራቸውን ስትራቴጂ መከለስ እንዳለባቸውም ባንኩ አሳስቧል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ ተቋማት ዘርፍ ምክትል ገዥ አቶ ሠለሞን ደስታ እንዳሉት የአገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማትን ከማጠናከር ጎን ለጎንም የውጭ ባንኮችን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት እየተሰራ ነው። ‹‹ሥራውን አሁን እያጠናቀቅን ነው። አዋጁን የመከለስ ሥራውንም እያጠናቀቅን ነው:: ከለጋሾች አንዳንድ ግብዓቶችን እየጠየቅን ነው። በወራት ዕድሜ ለህዝብ እንደራሴዎች ይቀርባል:: ስለዚህ ስራው እየተፋጠነ ነው” ብለዋል አቶ ሠለሞን። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት እስከ አምስት ለሚደርሱ የውጭ ባንኮች ፈቃድ ለመስጠት እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ሠለሞን…
Read More
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ አንዋር ሶሳ ከሓላፊነት ለቀቁ

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ አንዋር ሶሳ ከሓላፊነት ለቀቁ

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ አንዋር ሶሳ ከሓላፊነት ለቀቁ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት ዓለም አቀፍ ጨረታ ማሸነፉን ተከትሎ ነበር አንዋር ሶሳ ወደ አዲስ አበባ የመጡት። ከ2019 ጀምሮ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያን በስራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የቆዩት አንዋር ሶሳ አሁን ላይ ከሀላፊነት መነሳታቸውን ድርጅታቸው አስታውቋል። ይሁንና ሳፋሪኮም ለምን አንዋር ሶሳን ከሀላፊነት እንዳነሳቸው እስካሁን ይፋ አላደረገም። ከአንድ ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎቶችን መስጠት የጀመረው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአጭር ወራት ውስጥ ከሶስት ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን እንዳፈራ አስታውቋል። የኔትወርክ አገልግሎቶችን ከኢትዮ ቴሌኮም በመከራየት ደንበኞችን እያገለገለ የሚገኘው ሳፋሪ ኮም የኢትዮጵያ ገበያው ያሰበውን ያህል እንዳልሆነለት ከዚህ በፊት መግለጹ አይዘነጋም። ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን መሾሙ ይታወሳል። ላለፉት ሶስት…
Read More
ኢትዮጵያ ከኮቲዲቯሩ የአፍሪካ ዋንጫ ውጪ ሆነች

ኢትዮጵያ ከኮቲዲቯሩ የአፍሪካ ዋንጫ ውጪ ሆነች

በኮቲዲቯር አዘጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች በመካሄድ ላይ ናቸው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የዚህ ማጣሪያ ጨዋታ አንድ አካል የሆነው ጨዋታ ከማላዊ አቻው ጋር አድርጓል። ይህ ጨዋታ ዜሮ ለዜሮ በሆነ አቻ ውጤት የተጠናቀቀ ሲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከኮቲዲቫሩ የአፍሪካ ዋንጫ መውደቁን አረጋግጧል። ምድቡን እየመራች ያለችው ግብጽ አስቀድማ ማለፏን ያረጋገጠች ሲሆን ጊኒ ደግሞ ሁለተኛ በመሆን ለአፍሪካ ዋንጫው ማለፏን አረጋግጣለች። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት ውበቱ አባተ በውጤት ማጣት መሰናበታቸው ይታወሳል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከአሰልጣኝ ውበቱ ጋር በስምምነት እንደተለያየ ከዚህ በፊት አስታውቋል። በያዝነው ዓመት ለሚካሄደው የ2023 የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጇ ኮቲዲቯርን ጨምሮ ከ15 በላይ ሀገራት ማለፋቸውን አረጋግጠዋል። ኮቲዲቯር፣ ኢኳቶሪያል ጊኒ፣ ደቡብ አፍሪካ፣…
Read More
በኦሮሚያ ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ ከ50 በላይ ሰዎች ታገቱ

በኦሮሚያ ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ ከ50 በላይ ሰዎች ታገቱ

በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች የታገቱትን ሰዎች ለማስለቀቅ ለእያንዳንዳቸው አንድ ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ ተጠይቀዋል በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ ባሳለፍነው ቅዳሜ ማለዳ ላይ ከአዲስ አበባ ወደ ባህርዳር በመጓዝ ላይ የነበሩ ከ50 በላይ መንገደኞች ታይተዋል ። እገታውን የፈጸሙት የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ናቸው የተባለ ሲሆን ለአንድ ሰው አንድ ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ የታጋች ቤተሰቦች ታጣቂዎቹ እየደወሉ መጠየቃቸው ተገልጿል። እገታው የተፈጸመበት ስፍራ ከኢትዮጵያ ዋና ከተማ 75 ኪሎ ሜትር ላይ ሲሆን የፌደራል ፖሊስም ሆነ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ታጣቂዎቹ በዜጎች ላይ እገታውን ሲፈጽሙ ማስጣል እንዳልቻለ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል ። በዚህ አካባቢ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች የሚያደርሱትን ጥቃት በመፍራት የሌሊት ጉዞ ከቆመ አንድ ዓመት እንዳለፈውም ነዋሪዎቹ…
Read More