Blog

የነቀምቴ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር በታጣቂዎች ተገደሉ

የነቀምቴ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር በታጣቂዎች ተገደሉ

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን የነቀምቴ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር በታጣቂዎች መገደላቸው ተገለፀ። የነቀምቴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ቦኮንጃ ዛሬ ጠዋት በመኖሪያ ቤታቸው በር ላይ መሳሪያ በታጠቁ ሰዎች መገደላቸውን የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት አስታውቋል። ኃላፊው ወደ ስራ ለመሄድ ከቤታቸው በወጡበት ጊዜ በተተኮሰባቸው ጥይት እንደተገደሉም ነው የከተማ አስተዳደሩ ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት በማህበራዊ ገጽ ባወጣው መግለጫ ያስታወቀው። አቶ ደሳለኝ ቦኮንጃ የነቀምቴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ከመሾማቸው አስቀድሞ የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የነቀምቴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊነትን ጨም በተለያዩ ስፍራዎች ላይ ሲያገለግሉ መቆየታቸውም ተገልጿል። የነቀምቴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ…
Read More
መንግሥት በህወሀት አመራሮች ላይ የመሰረተውን ክስ አቋረጠ።

መንግሥት በህወሀት አመራሮች ላይ የመሰረተውን ክስ አቋረጠ።

መንግሥት በህወሀት አመራሮች ላይ የመሰረተውን ክስ አቋረጠ። የፍትህ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ በፌዴራል መንግስት እና በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) መሃከል በተፈረመው የሰላም ስምምነት መሰረት ከግጭቱ ጋር ተያያዥ የሆኑ ወንጀሎች ተጠያቂነት በተመለከተ ያለውን ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ታሳቢ ባደረገ መልኩ በሽግግር ፍትህ ማዕቀፍ ሊታዩ እንደሚገባ ስምምነት ላይ ተደርሷል ብላል። በመሆኑም በወንጀል ተጠርጥረዉ ክስ ቀርቦባቸዉ የነበሩ የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮችን ክስ ማቋረጡን ሚንስቴሩ አስታውቃል። ክሱ የተቋረጠላቸው ተከሳሾች ጉዳያቸዉ በቀጣይ በሽግግር ፍትህ ማዕቀፍ እንደሚታይም ተገልጿል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ቀርቦ በክርክር ሂደት ላይ ይገኙ የነበሩ የወንጀል ክሶች በአዋጅ 943/2008 አንቀጽ 6 (3) (ሠ) መሰረት መነሳታቸውን ሚንስቴሩ ገልጻል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት…
Read More
የአማራ ክልል ከአገው ሸንጎ ጋር ሲያደርገው የነበረው ውይይት አለመሳካቱ ተገለጸ

የአማራ ክልል ከአገው ሸንጎ ጋር ሲያደርገው የነበረው ውይይት አለመሳካቱ ተገለጸ

የአገው ሸንጎ በህወሃት ድጋፍ የአገው ክልልን ለመመስረት የትጥቅ ትግል እያደረገ ያለ ፓርቲ መሆኑ ይታወሳል፡፡ የአማራ ክልል መንግስትም ከአገው ሸንጎ ታጣቂዎች ጋር የሰላም ውይይት በማድረግ ላይ መሆኑን የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ይልቃል ከፋለ ከሁለት ሳምንት በፊት ምክር ቤት ላይ መናገራቸው አይነጋም፡፡ ይሁንና ይህ የሰላም ውይይት አለመሳካቱን የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ስቡህ ገበያው ተናግረዋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ላለፉት 21 ወራት በህወሓት እና በአገው ዴሞክራሲዊ ንቅናቄ ታጣቂዎች ይዞታ ስር የቆየችውን የአበርገሌ ወረዳ ዋና ከተማን፤ የመከላከያ ሰራዊት መልሶ ተቆጣጥሯል። የመከላከያ ሰራዊት በአማራ ክልል በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስር ወደምትገኘው “ንየር አቑ” ከተማ የገባው፤ ታጣቂዎቹ አካባቢውን በትላንትናው ዕለት ለቅቀው ከወጡ በኋላ እንደሆነ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ…
Read More
በደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ታግተዋል ተባለ

በደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ታግተዋል ተባለ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች መታገታቸውን የታጋቾች ቤተሰቦችና ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡  ታጣቂዎቹ ነዋሪዎችን ማገትና ማፈናቀል ከጀመሩ ረዥም ጊዜያት ቢቆጠሩም፣ በ2015 ግን ለተወሰኑ ወራት ፋታ አግኝቶ እንደነበር፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ እንደ አዲስ እንደተቀሰቀሰና በዚህም ነዋሪዎቹ እየታገቱ፣ እየተፈናቀሉና ቤት እየተቃጠለ ነው ሲል ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ቁጥጥር ሥር የነበሩ የደራ ወረዳ ሰባት ቀበሌዎችን ከሁለት ወራት በፊት በተደረገ ዘመቻ ነፃ ማድረግ ተችሎ እንደነበር ያስረዱት ነዋሪዎቹ፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ግን ጥቃት ማገርሸቱን አክለው ገልጸዋል፡፡ ጋዜጣው በስልክ አነጋገርኳቸው ያላቸው አምስት የወረዳው ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ የአካባቢው ነዋሪዎች በታጣቂ ቡድኑ እየተሰቃዩ መሆናቸውን፣ በርካታ ሰዎች በየቀኑ እየታገቱና እየተፈናቀሉ እንደሆኑ፣ የታገቱ…
Read More
ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ እና ጫት ንግድ ፈተና እንደሆነባት ገለጸች

ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ እና ጫት ንግድ ፈተና እንደሆነባት ገለጸች

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ የሀገሪቱን የውጪ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ እየጎዳው ነው ብለዋል። በዘንድሮው ዓመት የወርቅ እና የጫት ምርት በኮንትሮባንድ ንግድ አማካይነት እየወጣ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት ከአሶሳ 20 ኩንታል ወርቅ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ይላክ ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ በዚህ  ዓመት ግን ሶስት ኩንታል ብቻ መላኩ ለወርቅ ኮንትሮባንድ ንግድ መስፋፋት ማሳያ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ ከእዚህ ባለፈ የታንታለም ምርት በከፍተኛ ደረጃ ጉጂ ላይ ቢመረትም በህጋዊ መንገድ ወደ ውጪ ተልኮ የውጪ ገቢ ከሚያስገኘው ይልቅ በህገ ወጥ መንገድ ለጎረቤት ሀገራት የሚሸጠው ከፍተኛ ቁጥር እንዳለው አክለው አንስተዋል፡፡ ይህንኑ ከፍተኛ…
Read More
ጠቅላይ ሚኒሰትር አብይ አህመድ ስልጣን እንዲለቁ ተጠየቁ

ጠቅላይ ሚኒሰትር አብይ አህመድ ስልጣን እንዲለቁ ተጠየቁ

ጠቅላይ ሚኒስትር የመንግስታቸውን የስድስት ወራት አፈጻጸም ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡ ከአንድ የምክር ቤት አባልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን እንዲለቁ ጠይቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዜጎችን ደህንነት እና የሀገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ ዝቅተኛው የመንግስት ኃላፊነት ቢሆንም ይህንን እያደረጉ እንዳልሆነ ጥያቄ ቀርቦባቸዋል፡፡ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ፣ ቤታቸው ይፈርሳል፣ ንብረታቸው ይወድማል የሀገር ሉዓላዊነትን በሚዳፈር መልኩ የጎረቤት ሀገራት ሰራዊቶች በኢትዮጵያ ሰሜን ምዕራብ፣ እና ደቡብ ምዕራብ ወሰኖች በርከታ ኪሎ ሜትሮችን ዘልቀው በመግባት ወረራ ፈፅመዋል ሲሉም ከምክር ቤቱ አባላት ጥያቄ ቀርቦባቸዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሪፖርቱ ደጋግሞ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚገደሉ ዜጎች፣ ስለሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ወንጀሎች ፣ መፈናቀሎች፣ ግድያዎች ፣ ቤት መፍረሶች…
Read More
“የኢትዮጵያ የረቂቅ ሙዚቃ እናት” እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ አረፉ

“የኢትዮጵያ የረቂቅ ሙዚቃ እናት” እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ አረፉ

ፒያኖን በድንቅ ብቃት ስለሚጫወቱ “የፒያኖዋ እናት” የሚል ስያሜን ያገኙት እማሆይ ፅጌማርያም በ100 አመታቸው ነው ያረፉትእማሆይ ጽጌማርያም ከ150 በላይ የረቂቅ ሙዚቃ ድርሰቶችን የጻፉ ሲሆን፥ ሦስት አልበሞችን በሲዲ እና በሸክላ ላይ ማሳተማቸውም ይታወሳል በኢትዮጵያ ቀዳሚዋ የቫዮሊን እና ፒያኖ አቀናባሪ እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ በ100 ዓመታቸው አርፈዋል።እማሆይ ፅጌማርያም ከአባታቸው ከአቶ ገብሩ ደስታ እና እናታቸው ወይዘሮ ካሣዬ የለምቱ በ1915 ዓ.ም በአዲስ አበባ ውስጥ ነው የተወለዱት። እማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ በልጅነታቸው ለትምህርት በሄዱባት ስዊዘርላንድ ፒያኖን በደንብ ተምረዋል። ከትምህርት መልስም በ19 አመታቸው ወደ ወሎ ግሸን ማርያም ገዳም በመሄድ በ21 አመታቸው ምንኩስናን መቀበላቸውን የኢቢሲ ዘገባ ያሳያል። ወላጆቻቸው ያወጡላቸው ስም የውብዳር ሲሆን ምንኩስናን ከተቀበሉ በኋላ መጠሪያቸው ወደ እማሆይ ፅጌማርያም ተቀይሯል።…
Read More
በአርባምንጭ ዙሪያ ጫሞ ሀይቅ ላይ በተፈጠረ  ማዕበል የስምንት ሰዎች ህይወት አለፈ

በአርባምንጭ ዙሪያ ጫሞ ሀይቅ ላይ በተፈጠረ ማዕበል የስምንት ሰዎች ህይወት አለፈ

በደቡብ ክልል ጫሞ ሐይቅ ላይ በጀልባ ሲጓዙ የነበሩ 8 ሰዎች ባጋጠማቸው የማዕበል አደጋ ምክንያት ሰጥመው ህይወታቸው አለፈ። " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " የአማሮ ልዩ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው አደጋው የደረሰው ትላንት ቅዳሜ ከሰዓት ለኃላ ነው። ባለሞተር ጀልባው የአማሮ ልዩ ወረዳ አልፋጮ ቀበሌ ነዋሪዎችን አሳፍሮ ወደ አርባ ምንጭ በመጓዝ ላይ እያለ በጫሞ ሐይቅ ላይ በነበረው ማዕበል የመስጠም አደጋው አጋጥማል። በአደጋው የጀልባውን ሹፌር ጨምሮ ስምንት ሰዎች ህይወታቸው አልፏል። አደጋው መከሰቱ እንደታወቀ የተጎጂዎችን ህይወት ለማትረፍ ጥረት ቢደረግም በጫሞ ሐይቅ ላይ በነበረው ከፍተኛ ማዕበል ምክንያት አልተሳካም። ከአደጋው መድረስ በኋላ ከአርባ ምንጭ ከተማ በመጡ ዋናተኞች ጭምር ሕይወት ለማዳን ቢሞከርም በሰዓቱ የነበረው ማዕበል አላስቻለም ተብሏል። በጫሞ…
Read More
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የህወሀትን ከሽብር መዝገብ መሰረዝን ተቃወሙ

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የህወሀትን ከሽብር መዝገብ መሰረዝን ተቃወሙ

የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባት (ህወሀት) በትግራይ ክልል ያለውን የሀገር መከላከያ ሰሜን እዝ ላይ ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ ነበር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተጀመረው። ለሁለት ዓመት የዘለቀው ይህ ጦርነት ከ800 ሺህ በላይ ዜጎችን እና ከ20 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ የንብረት ውድመት አድርሷል። በፌደራል መንግሥት እና ህወሀት መካከል የተደረገው ይህ ጦርነት ባሳለፍነው ህዳር በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ የሰላም ስምምነት ተፈርሟል። ይህን ስምምነት ተከትሎም ጦርነቱ የቆመ ሲሆን በትግራይ ክልል ጊዜያዊ መንግሥት በመመስረት ላይ ይገኛል። እንዲሁም ህወሀት በግንቦት 2021 ላይ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ተፈርጆ ነበር። ይህ ህግ አውጪ ምክር ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ህወሀትን ከሽብር መዝገብ ላይ ሰርዟል። የኢትዮጵያ ማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ እና የአማራ…
Read More
የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ

የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ

የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ከሰሞኑ በትግራይ አህጉረ ስብከት በተሰጠ መግለጫ ዙሪያ ምላሽ ሰጥታለች። ቤተ ክርስቲያኗ በመግለጫዋ እንዳለችው በጦርነቱ ምክንያት በቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ መዋቅርና በትግራይ ክልል አህጉረ ስብከት መካከል አስተዳደራዊና መዋቅራዊ ግንኙነት ተቋርጦ መቆየቱን ገልጻለች። ይህንንም ተከትሎ በጦርነቱ ምክንያት ሁሉም የባንክ ተቋማት ሥራቸውን በማቆማቸው በየጊዜው እንደሌሎች አህጉረ ስብከት ለትግራይ አህጉረ ስብከት ይላክ የነበረው በጀት መላክ አልተቻለም ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቀጣይ እርምጃ ምንድን ነው? ቤተክርስቲያኗ ተፈጥሮ የነበረውን ችግር በቀኖናው መሰረት መፈታቱን ገለጸችምንም እንኳን በባንክ መዘጋት ለአገልጋይ ሠራተኞች በጀት መላክ ባይቻልም የደመወዝ መክፈያ የባንክ…
Read More