Blog

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ። አየር መንገዱ ወደ ሻንግሀይ ከተማ የካቲት 1973 የመጀመሪያ የቻይና በረራውን በማድረግ አገልግሎቱን የጀመረ ሲሆን ከጥቅምት 1973 ጀምሮ ደግሞ መዳረሻውን ወደ ቤጂንግ ከተማ በመቀየር አገልግሎን ቀጥሏል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት በ5 የመንገደኛ እና 9 የእቃ ጭነት መደበኛ በረራዎች በአጠቃላይ 66 ሳምንታዊ በረራዎችን ወደ 10 የቻይና ከተሞች በማድረግ ላይ ይገናል። ቤጂንግ፣ ጓንዡ፣ ሼንጁ፣ሻንግሀይ፣ ሸንዘን ፣ ውሀን፣ቻንግሻ፣ዢያመን፣ቸንዱ እና ሆንግ ኮንግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚበርባቸው የቻይና ከተሞች ናቸው። የአፍሪካ ግዙፍ የአቪዬሽን ተቋም የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች አሉት። በ1945 የተመሰረተው የኢትዮጵያ አየር መንገድ 70ኛ የምስረታ በዓሉን ከአንድ ዓመት በፊት…
Read More
ኢትዮጵያዊው ወጣት በሚያምነው ፈረሱ ተገደለ

ኢትዮጵያዊው ወጣት በሚያምነው ፈረሱ ተገደለ

በደቡብ ኢትዮጵያ አንድ ወጣት ለጭነትና ለመጓጓዣ በሚጠቀምበት ፈረስ ህይወቱ አልፏል። በደቡብ ክልል ጌድኦ ዞን ይርጋ ጨፌ ከተማ ለጭነትና ለመጓጓዣ በሚጠቀምበት የገዛ ፈረሱ የአንድ ወጣት ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ። ወጣት ቅጤሳ አለሙ በጌድኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ ከሚኖርበት የገጠር ቀበሌ እንጨት ጭኖ ወደ ከተማ በማምጣት እንጨቱን ሸጦ ወደ ቤቱ በመመለስ ላይ ነበር። ይህ የ26 ዓመት ወጣት ፈረሱ ላይ ተቀምጦ ወደ ቤቱ በመመለስ ላይ እያለ ፈረሱ በሞተር ብስክሌት ድምፅ ደንብሮ ወጣቱን መሬት ላይ ጥሎታል ተብሏል። ወጣቱ ከፈረሱ አንገት ላይ የነበረ ረዥም ገመድ በወገቡ እንደመቀነት ታጥቆት ኖሮ  በርግጎ በሚሮጠዉ ፈረስ መሬት ለመሬት እየተጎተተ ከድንጋይና ከግንድ ጋር ይላተማል። በአካባቢዉ ህብረተሰብ ትጋትና ርብርብ እንደምንም ፈረሱን ማስቆም…
Read More
የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና መኮንኖች ኢትዮጵያን ጎበኙ

የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና መኮንኖች ኢትዮጵያን ጎበኙ

የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት የጦር ጀነራሎች እና ከፍተኛ የጦር አመራር መኮንኖች በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገዋል። ኤርትራ ወታደራዊ ልኡክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት፣ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዓቅም እና እየተከናወኑ ያሉ የምርምር እና ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና፤ ኢንስቲትዩቱ እያከናወናቸው ባሉ የቴክኖሎጂ ሥራዎች ዙሪያ ለቡድኑ አባላት ገለጻ ማድረጋቸውን ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል፡፡ የኤርትራ የጦር ጀነራሎች እና ከፍተኛ የጦሩ አመራሮች ቡድን አስተባባሪ ጀነራል አብርሃ ካሳ፤ በኢንስቲትዩቱ ያደረጉት ጉብኝት ለአገራቸው ብዙ ልምድ የቀሰሙበት መሆኑን መናገራቸው ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በቴክኖሎጂው ዘርፍም አብረው መስራት የሚያስችላቸው እድል ስለመኖሩም የተገነዘቡበት ጉብኝት መሆኑን መጠቆማቸውም ተመላክቷል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ከ20 ዓመት በፊት ወደ ደም አፋሳሽ…
Read More
መልቲቾይዝ ኢትዮጵያ ለአማርኛ እና ኦሮሚኛ ተመልካቾች አዳዲስ ፕሮግራሞችን እንደሚያቀርብ አስታወቀ

መልቲቾይዝ ኢትዮጵያ ለአማርኛ እና ኦሮሚኛ ተመልካቾች አዳዲስ ፕሮግራሞችን እንደሚያቀርብ አስታወቀ

ከመልቲቾይዝ ኩባንያዎች መካከል አንዱ የሆነው ዲኤስቲቪ ለኢትዮጵያ ተመልካቾች የተለያዩ መዝናኛ ፕሮግራሞችን በማቅረብ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ድርጅቱ በኢትዮጵያ የይዘት ቀንን በአዲስ አበባ ያከበረ ሲሆን በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ አንጋፋ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ብዙሃን መገኛኛ ባለሙያዎች እና ሌሎችም ተገኝተዋል፡፡ ድርጅቱ በዚህ ወቅት እንዳለው ከዚህ በፊት ለኢትዮጵያ ተመልካቾች ሲያቀርባቸው ከነበሩት የመዝናኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪ አዳዲስ ይዘቶችን እንደሚያቀርብ ገልጿል፡፡ በድርጅቱ በኩል ለኢትዮጵያ ተመልካቾች ይቀርቡ ከነበሩት ይዘቶች በተጨማሪ አዳዲስ ፕሮግራሞችን በአማርኛ እና በኦሮሚኛ ቋንቋዎች የሚተላለፉ ይዘቶችን በቅርቡ እጀምራለሁም ብሏል፡፡ ዲኤስቲቪ አሁን ላይ በአቦል ቲቪ እና አቦል ዱካ ፕሮግራሙ አደይ፣ ደራሽ፣ አስኳላ፣ ሶረኔ፣ አጋሮቹ፣ ገብርዬ እና ሌሎችንም መዝናኛዎች በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ የመልቲቾይዝ ኢትዮጵያ ዳይሬክተር ገሊላ ገብረሚካኤል በፕሮግራሙ ላይ…
Read More
በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚቃወም እና የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ

በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚቃወም እና የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ

በኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን የመጡበትን ቀን በድጋፍ ሰልፍ ሲያከብሩ በአማራ ክልል ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን የመጡባትን ቀን መከራ እና ሞት እንጂ ለውጥ አላመጣልንም ሲሉ በሰላማዊ ሰልፍ ላይ ገልጸዋል፡፡ ከአምስት ዓመት በፊት በህወሃት የበላይነት ይመራ የነበረው ኢህአዴግ ህዝባዊ ተቃውሞ መበርታቱን ተከትሎ ነበር የወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ሀይለማርያም ደሳለኝ መጋቢት 2010 ዓ.ም ስልጣን የለቀቁት፡፡ ይህን ተከትሎም አብይ አህመድ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝን ተክተው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይም ሹመቱን በተቀበሉበት ወቅት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቃለ መሀላ ሲፈጽሙ የበርካቶችን ድጋፍ እና አድናቆት ያገኙ ቢሆንም በሁለት ዓመት ውስጥ ግን ድጋፋቸው አሽቆልቁሏል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለይም…
Read More
የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የድጎማ በጀት እንደሚልክ ገለጸ

የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የድጎማ በጀት እንደሚልክ ገለጸ

የፌደራል መንግስት ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ለትግራይ ክልል የበጀት ድጎማ መልቀቅ እንደሚጀምር የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ተናግረዋል። ለክልሉ የሚለቀቀው በጀት፤ ለሌሎች ክልሎች እንደሚደረገው ሁሉ በወራት ተከፋፍሎ የሚላክ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። የፌደራል መንግስት ለትግራይ በጀት ለማስተላለፍ ከስምምነት ላይ መድረሱን በተመለከተ አቶ ጌታቸው ረዳ ከቀናት በፊት ተናግረው ነበር። ባለፈው ሳምንት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተሾሙት አቶ ጌታቸው፤ የፌደራል መንግስት በጀት መፍቀዱን፤ ሆኖም የገንዘብ መጠኑን በተመለከተ ግን “ገና እንነጋገራለን” ማለታቸው ይታወሳል። የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታው በበኩላቸው፤ የትግራይ ክልል በጀት “የሚታወቅ” መሆኑን ገልጸዋል። የፌደራል መንግስት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እስኪቋቋም የበጀት ድጎማ ሳይለቅቅ ቢቆይም፤ በክልሉ ውስጥ…
Read More
የኬንያው ኬሲቢ ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ድርሻ ለመግዛት መወሰኑን አስታወቀ

የኬንያው ኬሲቢ ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ድርሻ ለመግዛት መወሰኑን አስታወቀ

ዋና መቀመጫውን ኬንያ ናይሮቢ ያደረገው ኬሲቢ ግሩፕ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ባንኮች የአክሲዮን ድርሻ በመግዛት ወደ ገበያው ለመግባት አማራጮችን እየገመገመ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ ግዙፍ ባንክ የሆነው ኬሲቢ ኬንያን ጨምሮ በቡሩንዲ፣ ሩዋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ታንዛንያ እና ዲሞክራቲክ ኮንጎ በባንክ ኢንዱስትሪ እየሰራ ይገኛል። ይህ ባንክ አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ ባንኮች የአክሲዮን ድርሻ ለመግዛት መወሰኑ ተሰምቷል። ይሁንና የኬንያው ባንክ ከየትኛው የኢትዮጵያ ባንክ አክስዮን ለመግዛት እንደወሰነ አልታወቀም። የባንኩ ፋይናንስ ዳይሬክተር የሆኑት ላውረንስ ኪማቲ ከቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ ጋር በነበራቸው ቆይታ በኢትዮጵያ ባንክ ገበያ ላይ ቅኝተ ማድረጋቸውን ገልጸው፤ ከተለያዩ ባንኮች ሰዎች ጋር መወያየታቸውንም ጠቁመዋል፡፡ ዳይሬክተሩ ከእነርሱ ጋር ሊሠሩ የሚችሉትን መለየታቸውንም በቆይታቸው ተናግረዋል፡፡ እንደ ላውረንስ የባንኮቹ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም የተሻለ…
Read More
የኦሮሚያ ክልል ያለበቂ ማጣራት ህጋዊ ቤቶችን እያፈረሰ እንደሆነ ኢሰመኮ ገለጸ

የኦሮሚያ ክልል ያለበቂ ማጣራት ህጋዊ ቤቶችን እያፈረሰ እንደሆነ ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያ የኦሮሚያ ክልል ውስጥ በቅርቡ በአዲስ መልክ በተደራጀው የሸገር ከተማ አስተዳደር የቤቶች ፈረሳ እና በግዳጅ ማስነሳት እየተከናወነባቸው ባሉ አካባቢዎች ምርመራ ማካሄዱን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ምርመራ ካደረገባቸው አካባቢዎች መካከል ቡራዩ፣ ሰበታ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ፣ መነ አብቹ እና በዙሪያው የሚገኙ አካባቢዎች ዋነኞቹ ናቸው። ቤቶቻቸው የፈረሱባቸው ሰዎች በግል እና በቡድን ለኮሚሽኑ ያቀረቡትን አቤቱታ ተከትሎ ከየካቲት 27 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ክትትልና ምርመራ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውቋል። ለኮሚሽኑ ቅሬታ ያቀረቡ ሰዎችን፣ የሚመለከታቸውን የከተማ አስተዳደር እና የጸጥታ አካላት በማነጋገር፤ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ቤቶችን የማፍረስ እና በግዳጅ የማስነሳት ሂደቱ የሚከናወንበትን ሁኔታ እንዲሁም ቀደም ሲል የፈረሱ ቤቶችን የመስክ ምልከታ በማድረግ መረጃ እና ማስረጃ ሰብስቤያለሁም ብሏል። ለኢሰመኮ ቅሬታቸውን ያቀረቡት ሰዎች ለኮሚሽኑ ሲያስረዱ በየአካባቢው ከቀድሞ/ነባር ባለ ይዞታዎች ቦታ ወይም ቤት በመግዛት ኑሮ…
Read More
አቶ ሮባ መገርሳ ከሀላፊነት ተነሱ

አቶ ሮባ መገርሳ ከሀላፊነት ተነሱ

የኢትዮጵያ ባህር ሎጅስቲክስ አገልግሎትን ላለፉት አምስት ዓመታት በሀላፊነት የመሩት አቶ ሮባ መገርሳ ከሀላፊነት ተነስተዋል። በዚህ ተቋም ከባለሙያነት ጀምሮ ያገለገሉት አቶ ሮባ ለምን ከሀላፊነት እንደተነሱ ይፋ አልተደረገም። በአቶ ሮባ ቦታም በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) ከትናንት መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ መሾማቸውን ኢትዮ ነጋሪ ከተቋሙ የኮሙንኬሽን ሀላፊ አቶ ደምሰው በንቲ አረጋግጣለች። አዲሱ ሀላፊ ከዚህ በፊት በኦሮሚያ ክልል ከወረዳ እስከ ፌደራል ተቋማት በተለያዩ የሀላፊነት ቦታዎች ላይ መስራታቸው ተገልጿል።
Read More
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን የ23 የቀድሞ አባቶችን ውግዘት አነሳች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን የ23 የቀድሞ አባቶችን ውግዘት አነሳች

ቤተ-ክርስቲያኒቱ ከህግ ውጭ ሲመተ ጵጵስና የሰጡና የተቀበሉ 26 የቀድሞ አባቶችን ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ማውገዟ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የሦስት ጳጳሳትንና የ20 መነኮሳትን ውግዘት አንስቷል። ውግዘቱ የተነሳው ከዛሬ መጋቢት 21፤ 2015 ዓ.ም. ጀምሮ እንደሆነ ምልዓተ ጉባኤው አሳውቋል። ቅዱስ ሲኖዶስ በመግለጫው "ሦስቱም የቀድሞ ሊቃነ ጳጳሳት ማለትም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ እና ብፁዕ አቡነ ዜናማርቆስ ላይ የተላለፈው ውግዘት ከዛሬ መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ተነስቷል" ብሏል፡፡ በቀድሞ የሊቀ ጳጳስነት ማዕረጋቸው እንዲጠሩና ተመድበው ይሰሩበት በነበረው የስራ ኃላፊነታቸው እንዲቀጥሉም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ የየካቲት ስምንቱን ባለ10 ነጥብ ስምምነት እንቀበላለን ብለው ለቅዱስ ሲኖዶስ ደብዳቤ ያስገቡ 20 የቀድሞ አባቶች ውግዘትም…
Read More