ethiopianews

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የነፍሰጡሮች ቁንጅና ውድድር አዘጋጀች

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የነፍሰጡሮች ቁንጅና ውድድር አዘጋጀች

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የነፍሰጡሮች የቁንጅና ውድድር በመስከረም ወር በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለፀ ። ታዋቂ ኢቪንትስ ከጤና ሚኒስቴር እና ከብሄራዊ ደም ባንክ አገልግሎት ጋር በጋራ ያዘጋጀውን ውድድር በተመለከተ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የውድድሩ አላማ በሀገሪቱን በስፋት እየተስተዋለ ስለሚገኘው የእናቶችን በእርግዝና እና በወሊድ ወቅት ህይወት ማለፍን አስመልክቶ ግንዛቤ ለመፍጠር መሆኑ ተገልጿል። ነፍሰ ጡርነት ውበት መሆኑን ለሌሎች በማስገንዘብ እና የጤና ክትትል የማያደርጉ ነፍሰ ጡር እናቶችን ክትትላቸውን እንዲያደርጉ የአመለካከት ለውጥ እንዲመጣ ለማሳየት መሆኑም ተመላክቷል። በዚህ የቁንጅና ውድድር 15 ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ከአንድ እስከ ሶስት ለሚወጡ አሸናፊዎች እንደየደረጃቸው ሽልማት ይበረከትላቸዋል ተብሏል። በውድድሩ ለመውለድ የተዘጋጁ ነፍሰ ጡሮች በዲዛይነሮች በተዘጋጁ ቅንጡ የነፍሰጡር አልባሳት ተውበው ይታያሉ ተብሏል። በቁንጅና…
Read More
በአዲስ አበባ ያለው ከባድ አየር ንብረት የአውሮፕላን በረራዎችን አስተጓጎለ

በአዲስ አበባ ያለው ከባድ አየር ንብረት የአውሮፕላን በረራዎችን አስተጓጎለ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲስ አበባ በተከሰተው ከፍተኛ ጭጋጋማ አየር ምንክንያት ወደ ሌላ አየር ማረፊያዎች እያዘዋወረ መሆኑን አስታወቀ በአዲስ አበባ በተከሰተዉ ከፍተኛ ጭጋጋማ አየር አብዛኛው በረራዎች ቦሌ አዉሮፕላን ማረፊያ ሊያርፍ ባለመቻሉ ምክንያት ወደ ሌላ አየር ማረፊያዎች እንዲቀየሩ መደረጉን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል ። አየር መንገዱ እንደገለፀው ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ባለዉ ከፍተኛ ጭጋግ ( ጉም) ምክንያት የአየር ማረፊያዎችን ወደ ሌላ ቦታ እያዘዋወረ መሆኑን እና ይህም በሀገር ዉስጥ እና በአለም አቀፍ በረራዎች ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል ብሏል። በተጓዦች ላይ ለደረሰዉ መጉላላት ይቅርታ የጠየቀው አየር መንገዱ በተጓዦች ላይ ሊደርሱ የሚችሉ መጉላላቶችን ለመቀነስ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አውሮፕላን ጣቢያ…
Read More
ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ያሉ የዲፕሎማሲ ተቋማት በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖችን እንዳያስገቡ ከለከለች

ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ያሉ የዲፕሎማሲ ተቋማት በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖችን እንዳያስገቡ ከለከለች

ኢትዮጵያ በሀገሪቱ የሚገኙ ሁሉም የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን እንዳያስገቡ እገዳ ጥላለች፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ የሚገኙ ሁሉም ዲፕሎማቲክ እና ሚሲዮኖች የነዳጅ መኪናዎችን እንዳያስገቡ እገዳ የጣለች ሲሆን በምትኩ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ማስመጣት ብቻ እንዳለባቸው አሳስቧል። የዉጪ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በአዲስ አበባ ለሚገኙ የዲፕሎማቲክ እና የቆንስላ ሚስዮኖች፣ ለቀጠናው እና ለአለም አቀፍ ድርጅቶች በፃፈው ደብዳቤ " የተወሰደው እርምጃ ኢትዮጵያ የበካይ ጋዝ ልዕቀት ቅነሳና ወደ ታዳሽ ኃይል ለመሸጋገር ካላት ቁርጠኝነት የተነሳ መሆኑን" አስረድተዋል ። በዚህም የዲፕሎማሲ መብት ያላቸው ሁሉ ተሽከርካሪዎችን ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ የተሰጠውን አቅጣጫ አክብረዉ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን ብቻ ማስመጣት ይጠበቅባቸዋል ብሏል። ኢትዮጵያ ከመጋቢት 2016 ዓ.ም ጀምሮ በነዳጅ የሚሰሩ የግል አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ወደ…
Read More
አሚአ ኩባንያ በ620 ሚሊዮን ዶላር የንፋስ ሀይል ማመንጫ ሊገነባ ነው

አሚአ ኩባንያ በ620 ሚሊዮን ዶላር የንፋስ ሀይል ማመንጫ ሊገነባ ነው

ኢትዮጵያ በ620 ሚሊዮን ዶላር የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለመገንባት ከአለም አቀፉ አሚአ ፓወር ኩባንያ ጋር ተስማምታለች፡፡ ስምምነቱ በዱባይ ከአራት ቀናት በፊት የኢትዮጵያ ኤሌክተሪክ እና አሚአ ኩባንያ ሀላፊዎች መካከል ተካሂዷል፡፡ ኢትዮጵያ በሶማሌ ክልል ለሚገነባዉ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ ለማልማት በታዳሽ ኃይል ልማት ላይ ከተሰማራው እና መቀመጫዉን የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ኩባንያ ካደረገዉ ከአሚአ ፓወር ጋር ስምምነት አድርጓል። በታዳሽ ኃይል ልማት፣ ግንባታና አስተዳደር ዘርፍ የተሰማራው አሚአ ፓወር በአይሻ አንድ የንፋስ ኃይል 300 ሜጋ ዋት አመንጭቶ ለኢትዮጵያ ለመሸጭ ነው ሥምምነቱን የፈረመው። በኢትዮጵያ 300 ሜጋ ዋት የንፋስ ሃይል ፕሮጀክትን ለማልማት እና ለማንቀሳቀስ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ጋር የኃይል ግዢ ስምምነት እና የትግበራ ስምምነት መፈራረሙን ያስታወቀው…
Read More
የድምጻዊ ቬሮኒካ አዳነ አዲስ አልበም በ17 ሚሊዮን ብር ተሸጠ

የድምጻዊ ቬሮኒካ አዳነ አዲስ አልበም በ17 ሚሊዮን ብር ተሸጠ

መጠሪያዬ የተሰኘው የድምጻዊ ቬሮኒካ አዳነ አዲስ አልበም በኢትዮጵያ ታሪክ ውዱ አልበም ተብሏል ድምፃዊት ቬሮኒካ አዳነ አዲስ አልበሟ ነሃሴ 23  ለአድማጮች እንደሚደርስ ድምጻዊቷ በዛሬው ዕለት በሰጠችው ጋዜጣዊ  መግለጫ ላይ ተናግራለች። መጠሪያዬ የሚል ስያሜ ያለው ይህ አዲ የሙዚቃ አልበም  የድምጻዊቷ  የመጀመሪያ አልበሟ ሲሆን  አልበሙን ሰርቶ ለማጠናቅ 6 ሚሊዮን ብር እንደፈጀባት ተናግራለች፡፡ በመሆኑም የተጠናቀውን  ሙሉ አልበም በ160ሺ የአሜሪካ ዶላር ወይም ከ17 ሚሊየን ብር በላይ መሸጡን በመግለጫው ለይ ተናግራለች። ይህ ክፍያ በኢትዮጵያ  ታሪክ የመጀመሪያው መሆኑም ተጠቁሟል። አልበሙ በተለያዩ  አማራጮች ለአድማጭ የደረሰ ሲሆን ይህም በቴሌግራም ካሴት መተግበሪያ ላይ ፣ በራሷ የዩቲውብ ቻናል እና በዞጃክ  ዓለም አቀፍ  መተግበሪያዎች ላይ እንደሚለቀቅ ተናግራለች። አልበሙን የገዛው "Zojak worldwide" የተሰኘው የአሜሪካ አሳታሚ ድርጅት…
Read More
ኢትዮጵያን በፔሩ ከ20 ዓመት በታች ዓለም አቀፍ ውድድር ላይ የሚወክለው አትሌት በጥይት ተመታ

ኢትዮጵያን በፔሩ ከ20 ዓመት በታች ዓለም አቀፍ ውድድር ላይ የሚወክለው አትሌት በጥይት ተመታ

የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ውድድር ከአንድ ሳምንት በኋላ በላቲን አሜሪካዋ ፔሩ አዘጋጅነት ይካሄዳል፡፡ ለሶስት ቀናት በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች ተመርጠው የመጨረሻ ልምምድ በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለውድድሩ ከመረጣቸው አትሌቶች መካከል የ17 አመቱ አትሌት ሰው መሆን ታሪኩ አንዱ ነው፡፡ ይህ አትሌት ባሳለፍነው እሁድ ነሀሴ 5 ቀን 2016 ዓም የከሰዓት በኋላ ልምምድ ለመስራት ወደ ጫካ ወጣ ብሎ ልምምዱን ጨርሶ እያቀዘቀዘ ባለበት ያልታሰበ ሰው ጥቃት አድርሶበታል ተብሏል፡፡ አትሌቱን አንድ ሰው ከቀረበው በኋላ ፓሊስ ነኝ በማለት ራሱን ካስተዋወቀው በኋላ እዚህ አካባቢ ቁማር የሚጫወቱ ታውቃለህ በማለት ሲጠይቀው አላውቅም ብሎ እንደመለሰ ነገር ግን ወዲያው በፎጥነት ይህ ሰው አንገቱን ሲይዘው አትሌቱም…
Read More
በሕፃን ሔቨን ጉዳይ የተጀመረው የሚዲያ ዘመቻ እንዲቆም የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር ጠየቀ፡፡

በሕፃን ሔቨን ጉዳይ የተጀመረው የሚዲያ ዘመቻ እንዲቆም የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር ጠየቀ፡፡

ከሰሞኑ የአማራ ክልል መዲና በሆነችው ባህር ዳር ከተማ የሰባት ዓመት እድሜ ያላት ህጻን ሔቨን የአስገድዶ መደፈር ወንጀል ከተፈጸመባት በኋላ ህይወቷ እንዳለፈ የህጻኗ እናት ለተለያዩ ሚዲያዎች ተናግራለች፡፡ በርካቶችን ያስቆጣው ይህ ድርጊት ወንጀሉን ፈጽሟል የተባለው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ በተፋጠነ ምርመራ ፍርድ ቤት ከቀረበ በኋላ የ25 ዓመት እስር እንደተላለፈበትም ተገልጿል፡፡ ይህን ተከትሎ ጥፋተኛ የተባለው ግለሰብ ላይ የተላለፈበት ውሳኔ በቂ ካለመሆኑ በላይ ግለሰቡ ፍርዱ እንዲቀነስለት ይግባኝ ማለቱም ተነስቷል፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም እንደተፈጸመ የተገለጸው ይህ ወንጀል ጉዳዩ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት ከፍተኛ ትኩረት የሳበ ሲሆን ተቋማት ሳይቀር በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫዎችን በማውጣት ላይ ናቸው፡፡ የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር በጉዳዩ…
Read More
ኢትዮጵያ በሶማሊያ ብሔራዊ ጥቅሟል ለማስጠበቅ ማንኛውንም እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል ገለጸች

ኢትዮጵያ በሶማሊያ ብሔራዊ ጥቅሟል ለማስጠበቅ ማንኛውንም እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል ገለጸች

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው ወቅት ከጋዜጠኞች ከተነሱላቸው ጥያቄዎች መካከል የግብጽ እና ሶማሊያ ወታደራዊ ስምምነቶች በኢትዮጵያ ላይ ምን አይነት አንድምታ ይኖረዋል? የሚለው ዋነኛው ነበር። እንዲሁም የሶማሊያን ጸጥታ እና ደህንነት ለማስጠበቅ በሚል በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር የተሰማራው ሰላም አስከባሪ ጦር (አትሚስ) ተልዕኮ የፊታችን ታህሳስ ያልቃል። የሶማሊያ ጸጥታ እና ደህንነት ተቋማት አሁንም የሚፈለገውን አቅም አለመገንባታቸውን ተከትሎ አትሚስን ተክቶ እንደ አዲስ በሚዋቀረው ሰላም አስከባሪ ስር ግብጽ ጦር ለማዋጣት ፍላጎት ማሳየቷ እና የሶማሊያ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ ጦር በአዲሱ ተልዕኮ ስር እንዳይካተት መፈለጋቸውስ በኢትዮጵያ ላይ ምን አይነት አስተዋጽኦ ይኖረዋል? የሚለው ጥያቄም ለአምባሳደር ነብዩ ተነስቶላቸዋል።…
Read More
የማራቶን አትሌቶች አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ኢትዮጵያ የሸለመቻቸውን 2 ሚሊዮን ብር አልቀበልም አሉ

የማራቶን አትሌቶች አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ኢትዮጵያ የሸለመቻቸውን 2 ሚሊዮን ብር አልቀበልም አሉ

በፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ልዑክ ቡድን በብሄራዊ ቤተ መንግስት አቀባበል እና የእራት ግብዣ ተደርጎለታል። ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት በተካሄደው የአቀባበል እና የአውቅና ስነ ስርዓት ላይም ለአትሌቶች፣ አሰልጣኞች እና ለታሳታፊዎችዎች እንደየ ተሳትፏቸው እና አብርክቷቸው ከ50 ሺህ ብር እስከ 7 ሚሊየን ብር የገንዘብ ሽልማት ተሰጥቷል። በዚህ ስነ ስርዓት ላይ በማራቶን ለኢትዮጵያ ብቸኛውን ወርቅ ሜዳሊያ ላስገኘው አትሌት ታምራት ቶላ 7 ሚሊየን ብር እና ወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል። የብር ሜዳልያ ላመጡት አትሌት ትግስት አሰፋ፣ አትሌት በሪሁን አረጋዊ እና አትሌት ፅጌ ዱጉማ ለእያንዳንዳቸው የ 4 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የታምራት ቶላ እና ትግስት አሰፋ አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ በስነ ስርዓቶ ላይ የ2 ሚልዮን ብር…
Read More
በፓሪስ ኦሎምፒክ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ 

በፓሪስ ኦሎምፒክ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ 

ለ17 ቀናት በፓሪስ የተካሄደው 33ኛው ኦሎምፒክ ትናንት ማምሻውን ተጠናቋል። በፓሪስ ኦሎምፒክ ድል ያስመዘገቡ እና የተሳተፉ የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን ዛሬ ማለዳ ነሀሴ 7 ቀን 2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ገብተዋል። የልኡካን ቡድኑ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በዛሬው እለት ከሰዓት በኋላ በብሔራዊ ቤተ-መንግስት ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ በተገኙበት ለልዑካን ቡድኑ የክብር ሽልማት፣ የማበረታቻ እና የእራት ግብዣ መርኃ-ግብር የሚካሄድ መሆኑንም ተገልጿል። ኢትዮጵያ በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ 1 የወርቅ እና 3 የብር በአጠቃላይ 4 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ከዓለም 47ኛ ከአፍሪካ ደግሞ 4ኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ ይታወቃል። ታምራት ቶላ በማራቶን ወርቅ፣ ጽጌ ድጉማ በሴቶች 800 ሜትር ብር፣ በሪሁ አረጋዊ በወንዶች 10 ሺህ…
Read More