መነሻ ገፅ

በአማራ ክልል የተጀመረው “ህግ የማስከበር ዘመቻ” ለሰብዓዊ መብት ስጋት መሆኑ ተገለጸ

በአማራ ክልል የተጀመረው “ህግ የማስከበር ዘመቻ” ለሰብዓዊ መብት ስጋት መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የ2015 ዓ.ም. በጀት ዓመት የ9 ወር የሥራ ክንውን ሪፖርቱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አቅርቧል፡፡ ኮሚሽኑ ባቀረበው የሥራ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ባደራጃቸው ዘጠኝ የትኩረት መስኮች የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፣ የተገኙ ውጤቶች እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በዝርዝር ተካትተዋል፡፡  በቀረበው ሪፖርት የሰብአዊ መብቶች ክትትልና ምርመራን በተመለከተ ኮሚሽኑ በዋናው መሥሪያ ቤቱና በከተማ ጽሕፈት ቤቶቹ በ1491 ሰዎች 1680 ጉዳዮች ላይ አቤቱታ የቀረቡለት ሲሆን ከነዚህም መካከል በኮሚሽኑ ሥልጣን ሥር የሚወድቁ 1084 አቤቱታዎችን ተቀብሎ ማስተናገዱ ተገልጿል፡፡ አቤቱታ ከቀረበባቸው ጉዳዮች መካከል አብዛኞቹ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶችን የተቀሩትደግሞ የኢኮኖሚያዊናየማኅበራዊ መብቶችንየተመለከቱ ናቸው።  ኮሚሽኑ በ48 ማረሚያ ቤቶች እና በ323 ፖሊስ ጣቢያዎች አካሄድኩት ባለው…
Read More
ኢትዮጵያ ለአምስት የውጭ ባለሀብቶች የባንክ ፈቃድ ልትሰጥ መሆኑ ገለጸች

ኢትዮጵያ ለአምስት የውጭ ባለሀብቶች የባንክ ፈቃድ ልትሰጥ መሆኑ ገለጸች

። ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በባንክ ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት ላላቸው የውጭ ባለሀብቶች አምስት የሚደርሱ የባንክ ፈቃድ ለመስጠት ማቀዷ ተገለጸ፡፡ የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከሦስት እስከ አምስት ለሚደርሱ በኢትዮጵያ በባንክ ዘርፉ መሰማራት ለሚፈልጉ የውጭ ባለሀብቶች የባንክ ፈቃድ እንደሚሰጥ መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ ይህም የአገሪቱን የፋይናንስ ዘርፍ አገልግሎት ለውጭ ተፎካካሪዎች ክፍት ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡ እስካሁን የባንኩ ዘርፍ ለውጭ አገራት መዋዕለ ነዋይ አፍሳሾች ዝግ ሆኖ የቆየ ሲሆን፤ በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ ግን ለውጭ አገራት ተፎካካሪዎች ክፍት እንደሚደረግ ነው የተገለጸው፡፡ በተጨማሪም የውጭ ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ዘርፉም ከአገር ውስጥ ባለሀብቶች ጋር በጋራ የሚሰሩበት አማራጭ ሊኖር እንደሚችል በምክትል ገዥው በኩል ተጠቅሷል፡፡ የውጭ…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም እና ሰዋሰው መተግበሪያ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

ኢትዮ ቴሌኮም እና ሰዋሰው መተግበሪያ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

በእለቱ አብነት አጎናፍርን ጨምሮ የሁለት አርቲስቶች የአልበም ምርቃት፣ የክብር ስጦና እና የፊርማ ስነ ስርአትም ተከናውኗል። ሀገር በቀሉ የሙዚቃ አገልግሎት ሰጪው “ሰወሰው” መተግበሪያ ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል። የስምምነት ፊርማው በሰዋሰው መተግበሪያ እና በሰዋሰው ዩትዩብ ቻናል በኩል የሚሰራጩ የኪነ-ጥበብ ሥራዎችን የቅጂ መብት ለማስከበር ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሏል ። ይህ ስምምነት የኪነ-ጥበብ ስራዎቹ ተደራሽነት ላይም ትርጉም ያለው ለውጥ እንደሚፈጥር ተገልጿል። የመዝናኛውን ኢንዱስትሪ ዲጅታላይዝ በማድረግ በኩል አሻራውን በማሳረፍ ላይ የሚገኘው ሰዋሰው ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በገባው ስምምነት ከነበሩት የክፍያ አማራጮች በተጨማሪ ወደ 9107 አጭር ቁጥር A ወይም B ብሎ በመላክ እለታዊ እና ሳምንታዊ የክፍያ የደንበኝነት ጥቅሎችን በመግዛት ደንበኞች የሚፈልጉትን ሙዚቃ እንዲያገኙ ያስችላል።…
Read More
እናት ባንክ “ለእናቴ” የተሰኘ አገር አቀፍ ጽሑፍ ውድድር  ጀመረ

እናት ባንክ “ለእናቴ” የተሰኘ አገር አቀፍ ጽሑፍ ውድድር  ጀመረ

እናት ባንክ “ለእናቴ” የተሰኘ ኹሉንም የማኅበረሰብ ክፍል የሚያሳትፍና የሚያሽልም አገራዊ የጽሑፍ ውድድር መጀመሩን አስታውቋል። የባንኩ ማርኬቲንግ እና ኮሙንኬሽን ዳይሬክተር አቶ አክሊል ግርማ እንዳሉት "ውድድሩ እናት ባንክ ከተመሠረተበት ራዕይና ተልዕኮ አንፃር የሚዛመድ ብሎም የባንኩን ማኅበራዊ እሴት ማዕከል የሚያደርግ አገር አቀፍ መርሐ ግብር ነው" ብለዋል። አቶ አክሊል አክለውም ባንኩ ለዘመናት ለአገርም ሆነ ለቤተሰብ ምሰሶ ለሆኑት የኢትዮጵያ እናቶች መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ለአንድ ወር የሚቆይ ሽልማት የሚያስገኝ፣ “ለእናቴ” የተሰኘ የጽሑፍ ውድድር በይፋ ማስጀመሩን ተናግረዋል። ውድድሩ በዋናነት ኹሉም ሰው ለእናቱ ያለውን ፍቅር፣ አክብሮት፣ ውለታና ምስጋና በዝርዝር ጽሑፍ ማለትም ግጥም ባልሆነ በወግ መልክ ወይንም በደብዳቤ ቅርፅ የሚገልጽበትና “ለእናት" የሚልበት መልካም አጋጣሚ እንደሆነም ዳይሬክተሩ ጨምረው አስረድተዋል። "ኹሉም…
Read More
የጀርመኑ መራሄ መንግሥት ኦላፍ ሹልዝ አዲስ አበባ ገቡ

የጀርመኑ መራሄ መንግሥት ኦላፍ ሹልዝ አዲስ አበባ ገቡ

የጀርመኑ መራሄ መንግሥት ኦላፍ ሹልዝ በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ገብተዋል። መራሄ መንግሥቱ የጀርመን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ፣ ባለሀብቶችን፣ የተቋማት መሪዎችን እንዲሁም በርከት ያለ የልዑካን አባላትን አስከትለው ነው ቦሌ አየር ማረፊያ የደረሱት። ሹልዝ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ብርቱካን አያኖ አቀባበል አድርገውላቸዋል። የመራሄ መንግሥቱን የሥራ ጉብኝት አስመልክቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም በሰጡት መግለጫ፤ ጉብኝቱ ታሪካዊና ጠንካራ የኹለትዮሽ ግንኙነት ላላቸው ኢትዮጵያና ጀርመን ከፍ ያለ ፋይዳ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። ትብብሮችን ለማሳደግ ፣ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማላቅ  የመራሄ መንግሥት ሹልዝ ጉብኝት ትርጉም ያለው መሆኑንም ገልጸዋል። መራኄ መንግሥት ኦላፍ ሾልዝ በኢትዮጽያ ቆይታቸው…
Read More
በአማራ ክልል ሶስት ዞኖች ጦርነት መጀመሩ ተገለጸ

በአማራ ክልል ሶስት ዞኖች ጦርነት መጀመሩ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል የተወሰኑ አካባቢዎች እየተካሄደ ያለው “የሕግ ማስከበር ዘመቻ”ን አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል። ኮሚሽኑ ይህ ድርጊት በሰብአዊ መብቶች ላይ ያለውን አንድምታና ተጽእኖ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑ አስታውቋል። ኮሚሽኑ አደረኩት ባለው ክትትል በሰሜን ጎንደር፣ ሰሜን ወሎ እና ሰሜን ሸዋ ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች ግጭት አለ ብሏል። በተለይም ሸዋ ሮቢት፣ አርማኒያ፣ አንጾኪያ፣ ገምዛ እና ማጀቴ በመከላከያ ሰራዊት እና በአካባቢው ታጣቂዎች መካከል የተኩስ ልውውጥና በከባድ መሣሪያ ጭምር የታገዘ ጥቃት መኖሩን ደርሼበታለሁም ብሏል። በዚህ የተኩስ ልውውጥ ምክንያትም በሲቪል ሰዎች ላይ የሞት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት ከመድረሱ ባለፈ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ የሚወስደው መንገድ በተለያዩ ጊዜያት መዘጋቱን እንዳረጋገጠ ኮሚሽኑ አስታውቋል። በተጨማሪም በክልሉ ያሉ የተወሰኑ…
Read More
በፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ የግድያ ሙከራ ተፈጸመ

በፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ የግድያ ሙከራ ተፈጸመ

በሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን መኖሪያ በሆነው የክሪምሊን ቤተ መንግስት ላይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን አርቲ ዘግቧል፡፡ የድሮን ጥቃቱ ያነጣጠረው በሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ ሲሆን ጥቃቱ ሲፈጸም ፕሬዝዳንቱ በቦታው አልነበሩም ተብሏል፡፡ የቤተ መንግስቱ ቃል አቀባይ ድሚትሪ ፔስኮቭ እንዳሉት አደጋው በሁለት ድሮኖች የታገዘ ሲሆን የየት ሀገር ስሪት እንደሆነ እስካሁን አልታወቀም፡፡ በድሮኖቹ ጥቃት የተጎዳ ሰው አለመኖሩን የተናገሩት ቃል አቀባዩ ሞስኮ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ መጀመሯንም አክለዋል፡፡ የሞስኮ ከተማ ከንቲባ በበኩላቸው በከተማዋ ከተፈቀደላቸው የደህንነት ተቋማት ውጪ የድሮን እንቅስቃሴ መታገዱን ገልጸዋል፡፡ ፊንላድን እየጎበኙ ያሉት የዩክሬን ፕሬዝዳንት ከሄልስንኪ እንዳሉት በክሪምሊን ቤተ መንግስት ላይ ተፈጸመ ስለተባለው የድሮን ጥቃት መረጃ የለኝም ብለዋል፡፡
Read More
የፌደራል መንግሥት እና ኦሮሚያ ነጻነት ሰራዊት ድርድር አለመሳካቱ ተገለጸ

የፌደራል መንግሥት እና ኦሮሚያ ነጻነት ሰራዊት ድርድር አለመሳካቱ ተገለጸ

የመንግስት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ በኦሮሚያ ክልል ያለውን ግጭት በማስወገድ ሰላምን ለማምጣት ያለመውና በታንዛኒያ ሲካሄድ የቆየው የሰላም ውይይት የመጀመሪያ ምዕራፍ ተጠናቋል ብሏል። ውይይቱ በአብዛኛው በአዎንታዊ መልኩ የተከናወነ ነው ያለው ሚንስቴሩ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ግን በዚህኛው የውይይት ምዕራፍ ስምምነት ላይ አልተደረሰም ብሏል። ግጭቱን በዘላቂነትና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለማስቆም እንዲቻል ሁለቱም አካላት የሰላም ውይይቱን መቀጠል አስፈላጊ መሆኑ ላይ እንደተግባቡ ተገልጿል። በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትና እስካሁን ሲመራባቸው በነበሩ መሠረታዊ መርሖች መሠረት ግጭቱን በሰላማዊ መልኩ ለመፍታት መንግስት የጸና አቋም እንዳለው በመግለጫው ላይ ተጠቅሷል። ይህንን መልካም አጋጣሚና በውይይት ችግሮችን የመፍታት በጎ ጅምር በመጠቀም ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ የኢትዮጵያ መንግሥት ፅኑ አቋም እንዳለው አስታውቋል። አሜሪካ በታንዛኒያ ራስ…
Read More
በኢትዮጵያ በኮሌራ ወረርሽኝ የ84 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ በኮሌራ ወረርሽኝ የ84 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የኮሌራ ወረርሽኝ መከሰቱ ከተገለጸ ስድስት ወራት ያስቆጠረ ሲሆን የሰዎች ህይወት ማለፉን የኢትዮያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል፡፡ በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከአምስት ሺህ 500 በላይ ሰዎች በኮሌራ ወረርሽኝ መጠቃታቸውም ተገለጿል ። የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ርዳታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ በይፋዊ የትዊተር ገጹ ባወጣው መረጃ ከነሐሴ 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጀምሮ ከ5,500 በላይ ሰዎች ኢትዮጵያ ውስጥ በኮሌራ ተጠቅተዋል ። የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ 118 ከፍተኛ ተጠቂ አካባቢዎች የለየ ሲሆን የወረርሽኙ ተጠቂዎች የሚታከሙባቸው 41 የኮሌራ ህክምና ማዕከላት ማቋቋሙን ገልጿል። በዋናነት ችግሩ የታየባቸው አካባቢዎች የሶማሌ፤ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች፤ የኦሮሚያ፤ የአፋር፤ የአማራ እና የትግራይ ክልሎች ናቸውም ብሏል ።  አጣዳፊ ተቅማጥ የሚያስከትለው የኮሌራ ወረሽኝ የሚሰራጨው…
Read More
አሜሪካ የ2024 ዲቪ ሎተሪ እድለኞችን ይፋ አደረገች

አሜሪካ የ2024 ዲቪ ሎተሪ እድለኞችን ይፋ አደረገች

አሜሪካ በዓለም ላይ በየዓመቱ 50 ሺህ ሰዎችን በዳይቨርሲቲ ቪዛ ወይም ዲቪ ሎተሪ አማካኝነት ወደ ሀገሯ ታስገባለች። ባሳለፍነው ጥቅምት እና ህዳር ወራት ላይ በበይነ መረብ አማካኝነት የተሞላው የ2024 ድቪ ሎተሪ አሸናፊዎች መታወቃቸው ተገልጿል። የዲቪ 2024 ማመልከቻ የሞሉ ዜጎችም መመረጣቸውን እና አለመመረጣቸውን የፊታችን ቅዳሜ ማለትም ከሚያዚያ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ማወቅ እንደሚችሉ በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲ በትዊተር ገጹ ጽፏል። ኢምባሲው አክሎም በዲቪ ሎተሪ ድረገጽ ላይ በመግባት አመልካቾች ያመለከቱበትን ልዩ ቁጥር ወይም ኮድ በማስገባት ማወቅ ይችላሉም ብሏል። ይህ በዚህ እንዳለም የዲቪ ሎተሪ አሸንፋችኋል፣ ከአሜሪካ ኢምባሲ ነው እምንደውለው በሚል የሚያጭበረብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች እንዲጠነቀቁም አሳስቧል። ለዲቪ ሎተሪ ስለማሸነፋቸው እና አለመድረሱን አመልካቾች በራሳቸው…
Read More