መነሻ ገፅ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች ላይ የተጣለውን እገዳ ተቃወመ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች ላይ የተጣለውን እገዳ ተቃወመ

የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መከልከል ባለሃብቶችንና የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ይጎዳል በማለት ተቃውሟል፡፡ ኮሚሽኑ ለትራንስፖርት ሚንስቴር በጻፈው ደብዳቤ፣ የሕግ ድንጋጌ ሳይኖርና ግልጽ ሕግ ሳይወጣለት ከበላይ አካል በተሰጠ ትዕዛዝ ብቻ ነዳጅ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ ማገድ አግባብነት የለውም በማለት ቅሬታውን እንደገለጠ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የተላለፈው ውሳኔ በግብርና፣ በግብርና ምርት ማቀነባበር፣ በአበባ እርሻ ልማት፣ በቱሪዝም፣ በማኑፋክቸሪንግና ግንባታ እና ሌሎች ስራዎች በተሠማሩ ባለሃብቶች እና ኩባንያዎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ መፍጠሩን ኮሚሽኑ አስታውቋል። ኮሚሽኑ አክሎም ለአንዳንድ ኢንቨስትመንት ስራዎች ከባሕሪያቸው አንጻር በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች እንዲያስገቡ እንዲፈቀድላቸው ሲል እንደጠየቀም ተገልጿል። ኢትዮጵያ ካሳለፍነው መጋቢት ወር ጀምሮ በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች…
Read More
ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሶስት ሀገራት የተውጣጡ የጠፈር ሳይንስ ተማሪዎች ተመረቁ

ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሶስት ሀገራት የተውጣጡ የጠፈር ሳይንስ ተማሪዎች ተመረቁ

ቦይንግ እና የወደፊቶቹ የአፍሪካ ጠፈር ተመራማሪዎች የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ አካዳሚ ወይም ፋሲሳ ከሶስት የአፍሪካ ሀገራ የተውጣጡ 300 ታዳጊዎችን በጠፈር ሳይንስ አሰልጥነው አስመርቀዋል፡፡ ለአምስት ወራት የተካሄደው ይህ ስልጠና ከኢትዮጵያ፣ ናይጀሪያ  እና ታንዛኒያ ከሚገኙ 63 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ናቸው ተብሏል፡፡ በወደፊቶቹ የአፍሪካ ጠፈር ተመራማሪዎች የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ አካዳሚ (Future African Space Explorers STEM Academy፣ FASESA) እና Boeing [NYSE:BA] የተዘጋጀ አዲስ የትምህርት ንቅናቄ የሆነው የመጀመሪያው ወደ ጠፈር የሚወስዱ መንገዶች ፕሮግራም ስብስብ ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ተመርቀዋል፡፡ ከአምስት ወራት መማር በኋላ በመላው ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ታንዛኒያ ከሚገኙ 63 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 50% ሴት ልጆችን ጨምሮ 312 ተማሪዎች ለጠፈር…
Read More
ኢትዮጵያዊያኑ በሞሮኮ በተካሄደ የቴክኖሎጂ ውድድርን በአንደኝነት አጠናቀቁ

ኢትዮጵያዊያኑ በሞሮኮ በተካሄደ የቴክኖሎጂ ውድድርን በአንደኝነት አጠናቀቁ

የኢትዮጵያ ቡድን በሞሮኮ በተካሄደው የሁዋዌ ቴክ ፎር ጉድ ክፍለ አህጉራዊ ውድድርን በአንደኝነት አጠናቋል፡፡ የሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር “Huawie Seeds for the Future 2024” የቴክኖሎጂ ስልጠና መርሃ ግብር በሞሮኮ (ኢሳዉራ) ከሰኔ 26 እስከ ሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ተካሂዷል። ይህ ስልጠና ከምስራቅ፣ ሰሜን፣ ምዕራብ እና መካከለኛው አፍሪካ የተውጣጡ 17 አገራትን አሳትፏል። ኢትዮጵያም ከስምንት ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ 10 ተማሪዎችን በስልጠናው ያሳተፈች ሲሆን ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል 5 ተማሪዎችን የያዘው የኢትዮጵያ አንድ ቡድን በሁዋዌ ቴክፎርጉድ ክፍለ አህጉራዊ ውድድር አንደኛ በመሆን አሸንፏል፡፡ ተማሪዎቹ በቴክ ፎር ጉድ ክፍለ አህጉራዊ (ግሎባል) ፕሮጀክት ከመወዳደራቸው በፊት የተለያዩ የቴክኖሎጂ ስልጠናዎችን ወስደዋል። ተሳታፊ ተማሪዎቹ በ28 ቡድኖች ተከፋፍለው ለውድድር የሚሆኑ ፕሮጀክቶችን ያዘጋጁ…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም 94 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ

ኢትዮ ቴሌኮም 94 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ የበጀት ዓመቱን የሥራ አፈጻጸም በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል። ኢትዮ ቴሌኮም በ2016 በጀት ዓመት 93 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል። ከተገኘው ገቢ 39.9 በመቶ የድምጽ ፣ 21.7 የኢንተርኔት ፣10.2 የዓለም አቀፍ አገልግሎቶች ፣ 2.5 ከቴሌብር እና 1.5 ከኢንፍራስትራክቸር እንዲሁም 5 በመቶ የሚሆነው  ደግሞ ከዲቫይስ የተገኘ ገቢ መሆነም ተገልጿል ። በበጀት ዓመቱ የኩባንያው የደንበኞች ቁጥር 78 ነጥብ 3 ሚሊየን መድረሱን ገልጸው፤ በበጀት ዓመቱ 21 ነጥብ 79 ቢሊየን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱንም ተናግረዋል። ኩባንያው በውጭ ምንዛሬ ገቢ ከሚያገኝባቸው ምንጮች 198 ሚሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቱን ገልጸዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለውም በ2016 በጀት ዓመት ኢትዮ ቴሌኮም 30…
Read More
ኢትዮጵያ ከቡና ንግድ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከቡና ንግድ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት ከተላከ የቡና ንግድ በታሪክ ከፍተኛ የተባለዉን ገቢ ማግኘቷን አስታውቃለች፡፡ ኢትዮጵያ ከቡና ወጪ ንግድ በዘንድሮው በጀት አመት ከአንድ ነጥብ 4 ቢሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ እንደገለፁት ኢትዮጵያ በ2016 በጀት አመት ከቡና ሽያጭ በመጠንም ሆነ በገቢ ከፍተኛ የሆነ ውጤት አስመዝግባለች ብለዋል። ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት 298 ሺህ 500  ቶን ቡና ለውጪ ገበያ አቅርባ 1 ነጥብ 43 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች። ይህም ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በመጠንም ሆነ በገቢ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበበት እንደሆነ ዋና ዳይሬክተሩ  ጨምረው ገልፀዋል። የተላከው የቡና መጠን በ20 በመቶ እንዲሁም በዋጋ ደረጃም…
Read More
አሜሪካ በአማራ እና ኦሮሚያ ተማሪዎችን እና ንጹሃን ዜጎችን ማገት እንዲቆም ጠየቀች

አሜሪካ በአማራ እና ኦሮሚያ ተማሪዎችን እና ንጹሃን ዜጎችን ማገት እንዲቆም ጠየቀች

ባሳለፍነው ሳምንት ከደባርቅ ዩንቨርሲቲ ተነስተው ወደ ቤተሰቦቻቸው በመጓዝ ላይ የነበሩ ተማሪዎች መታገታቸው ይታወሳል፡፡ እገታው የተፈጸመው ለአዲስ አበባ ከተማ ትንሽ ሲቀራቸው በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ በታጣቂዎች እንደሆነ በወቅቱ ተገልጾም ነበር፡፡ የፌደራል መንግስትም ሆነ የኦሮሚያ ክልል መንግስት እስካሁን ስለ ጉዳዩ በይፋ እስካሁን ያሉት ነገር ባይኖርም የታጋች ተማሪዎች ቤተሰቦች ግን ልጆቻቸው በታጣቂዎች እንደታገቱባቸው ለተለያዩ ብዙሃን መገናኛዎች ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኢምባሲ በጉዳዩ ዙሪያ በወጣው መግለጫ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የተራዘሙ ግጭቶች የህግ የበላይነት እንዳይከበር ምክንያት ሆነዋል ሲል በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ላይ ገልጿል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት እና ከዚህ በፊት የተፈጸሙ ተከታታይ እገታዎች ወንጀለኞችን እንዳይጠየቁ ማድረጉን በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር አረቪን ማሲንጋ መናገራቸውን…
Read More
በኢትዮጵያ ማየት አቁመው ለነበሩ 217 ሰዎች የአይን ንቅለ ተከላ ተደረገላቸው

በኢትዮጵያ ማየት አቁመው ለነበሩ 217 ሰዎች የአይን ንቅለ ተከላ ተደረገላቸው

በኢትዮጵያ በ2016 በጀት ዓመት ለ217 ሰዎች የዓይን ብሌን ንቅለ ተከላ ተደርጎ የአይን ብርሃናቸው ተመለሰ በኢትዮጰያ ባለፉት አስራ አንድ ወራት ለ217 ሰዎች የዓይን ብሌን ንቅለ ተከላ ህክምና በማድረግ የአይን ብርሃናቸው እንደተመለሰ የኢትዮጰያ ደም እና ህብረ- ህዋስ ባንክ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሀብታሙ ታዬ ተናግረዋል፡፡ የተለገሰው የአይን ብሌን ንቅለ ተከላውን ለሚያከናውኑት የተለያዩ የህክምና ተቋማት በመሰራጨት በአይን ብሌን ምክንያት ሊተላለፉ የሚችሉ በሽታዎች ላይ ቅድመ ምርመራ በማድረግ  ልገሳው  እንደተከናወነ  ተገልጿል፡፡ በቀጣይ 445 የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸው ካለፈ በኋላ የአይን ብሌናቸውን ለመለገስ ቃል የገቡ ቢሆንም ከፈላጊዎች አንጻር በጣም ዝቅተኛ ነው ተብሏል። ከሞት በኃላ ሰዎች የአይን ብሌናቸውን እንዲለግሱ በአዲስ አበባ ብቻ የማሰባሰብ ስራ የሚከናወን ሲሆን…
Read More
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት “ኢትዮጵያ ለዲፕሎማሲ ዝግጁ አይደለችም” ሲሉ ከሰሱ

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት “ኢትዮጵያ ለዲፕሎማሲ ዝግጁ አይደለችም” ሲሉ ከሰሱ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከሰሞኑ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባደረጉት ንግግር ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር ከመነጋገር ይልቅ ወደ ሌሎች ሀገራት ሽምግልና ይልካሉ ሲሉ መክሰሳቸው ይታወሳል፡፡ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ የገቡበትን ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት በንግግር ለመፍታት ኢትዮጵያ ዝግጁ አይደለችም ሲሉ ተናገሩ። የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ቅዳሜ ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ.ም በአገሪቱ ምክር ቤት የመክፈቻ ንግግራቸው ላይ መንግሥታቸው ዲፕሎማሲያዊ ውጥረቱን ለማርገብ ፍላጎት ቢኖረውም፤ ኢትዮጵያ ግን ለውይይት ዝግጁ አይደለችም ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ ይህን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከጥቂት ቀናት በፊት “የሶማሊያ መንግሥት እኛን ከማናገር፣ በየሰፈሩ እየዞረ እኛን መክሰስ መርጧል” ብለው ከተናገሩ በኋላ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ባሳለፍነው ሳምንት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር…
Read More
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ከወደብ ስምምነት ውጪ በሌሎች ጉዳዮችም እየተደራደሩ መሆኑን ገለጹ

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ከወደብ ስምምነት ውጪ በሌሎች ጉዳዮችም እየተደራደሩ መሆኑን ገለጹ

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው ላይ ካነሷቸው ጉዳዮች መካከል የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ጉዳይ ዋነኛው ነው። በቱርክ አደራዳሪነት በአንካራ የተጀመረው የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ድርድር ሁለተኛው ዙር የፊታችን ነሀሴ 27 ቀን 2016 ዓ.ም ይቀጥላል የተባለ ሲሆን ይህ ድርድር ምን ያህል ከውጭ ጣልቃ ገብነት የተጠበቀ ነው?  የሚል ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ተከታዩን ብለዋል። "ኢትዮጵያ በታሪኳ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ ስትደራደር ቆይታለች፣ አንድም ጊዜ በውጭ ጣልቃ ገብነቶች ጥቅሟን አሳልፋ ሰጥታ አታውቅም" ብለዋል። "በአንካራ እየተካሄደ ያለው የሁለትዮሽ ድርድርም ብሔራዊ ጥቅማችንን ባስጠበቀ መንገድ ይቀጥላል" ያሉት አምባሳደር ነብዩ በድርድሩ ላይ ምንም አይነት ጣልቃ ገብነት እንደሌለ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ…
Read More
የጸጥታ ሀይሎች የአማራ ክልል ህዝብ የጤና አገልግሎት እንዳያገኝ እያደረጉ ነው -ሂዩማን ራይትስ ዋች

የጸጥታ ሀይሎች የአማራ ክልል ህዝብ የጤና አገልግሎት እንዳያገኝ እያደረጉ ነው -ሂዩማን ራይትስ ዋች

የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ አጋሮች በአማራ ክልል እየተፈጸመ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳላየ መሆናቸውን እንዲያቆሙ ሂዩማን ራይትስ ዋች አሳሰበ፡፡ ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተቋም ሂዩማን ራይትስ ዋች በኢትዮጵያ አማራ ክልል የሰብዓዊ መብት ጥሰት ዙሪያ አዲስ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የተቋሙ ሪፖርት ካሳለፍነው ነሀሴ 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 2016 ዓ.ም ባሉት 10 ወራት ውስጥ ተፈጽመዋል ባለቸው ጉዳዮች ዙሪያ አተኩሯል፡፡ በአማራ ክልል ከጤና እና ተያያዥ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ዙሪያ ያተኮረው ይህ ሪፖርት የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች የጤና ተቋማትን ኢላማ አድርገዋል ብሏል፡፡ ተቋሙ 58 ተጎጂዎችን እና የአይን ምስክሮችን ቃለ መጠይቅ አድርጌ አወጣሁት ባለው ሪፖርቱ ላይ እንዳለው ወታደሮች ለህክምና ወደ ሆስፒታል ሲገቡ ቢሞቱ ሐኪሞቹ ተጠያቂ እንደሚሆኑ…
Read More