መነሻ ገፅ

መቐለ ዩኒቨርሲቲ በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ይጀምራል መባሉን አስተባበለ

መቐለ ዩኒቨርሲቲ በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ይጀምራል መባሉን አስተባበለ

መቐለ ዩኒቨርሲቲ በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ይጀምራል በሚል የተሰራጨው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀበሰሜን ኢትዮጵያ ሲካሄድ በነበረው ጦርነት ምክንያት የመማር ማስተማር ሥራው የተቋረጠው የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ሥራውን እንደሚጀምር በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘገብ ቆይቷል። በዚህም ዩኒቨርሲቲው በሚቀጥሉት አራት ወራት 24 ሺሕ የሚጠጉ የቀድሞ ተማሪዎችን እንደሚያስመርቅ እና ከመስከረም ወር 2016 ጀምሮ አዲስ ተማሪዎችን እንደሚቀበል የተገለጸ ሲሆን፤ ዩኒቨርሲቲው በመንግሥት በኩል የሚያስፈልግ በጀት ሁሉ እንደተለቀቀለትም ተነግሯል። ነገር ግን ይህ መረጃ የተሳሳተ መሆኑን የዩኒቨርስቲው ሰራተኞች እና አመራሮች አረጋግጠዋል። መቐለ ዩኒቨርሲቲም ይህንን ዜና የሚመለት መረጃ በይፋዊ የፌስቡክ እና የትዊተር አካውንቱ ላይ አላወጣም። የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋና ሓጎስ ዩኒቨርሲቲው ሥራ ለመጀመር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር…
Read More
መንግሥት ለአዲስ አበባ አመራሮቹ ለሞባይል ስልክ 140 ሺህ ብር ፈቀደ

መንግሥት ለአዲስ አበባ አመራሮቹ ለሞባይል ስልክ 140 ሺህ ብር ፈቀደ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለአመራሮች የእጅ ስልክ መግዣ 140 ሺህ ብር ድረስ ፈቀደ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በጥር ወር ላይ በወሰነዉ ዉሳኔ መሰረት፣ ለከተማዋ አመራሮች የሞባይል ስልክ ቀፎ ግዢ መፍቀዱ ተገልጿል። በዚህም መሰረት ለከንቲባ እና ለከተማ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ 140 ሺህ ብር ተመድቧል። ለምክትል ከንቲባ፣በምክትል ከንቲባ ማዕረግ ደረጃ ለተሿሙ አመራሮች እና ለምክትል አፈ-ጉባኤ ስልክ መግዣ 120 ሺህ ብር መወሰኑንም ሰምተናል ሲል ኢትዮ ኤፍ ዘግባል። ለክፍለ ከተማ 50 ሺህ ፣ለወረዳ ዋና ስራ አስፈፃሚ የ40 ሺህ እንዲሁም ለወረዳ ቀሪ አመራሮች 30 ሺህ ብር የሚያወጣ የሞባይል ስልክ እንዲገዛላቸዉ ተፈቅዷል። ይህንን የሚያስፈፅም ደብዳቤም በየክፍለ ከተማዎችና ወረዳዎች ጭምር እንደተበተነ ተገልጿል።
Read More
<strong>ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመቋረጧ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተገለጸ</strong>

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመቋረጧ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተገለጸ

በሳሙኤል አባተ ኢትዮጵያ በኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተገልጻል። ቶፕ 10 ቪፒኤን የቴክኖሎጂ ኩባንያ እንዳስታወቀው፣ በትግራይ ክልል የነበረውን ጦርነት ተከትሎ ለአንድ አመት ሙሉ የኢንተርኔት አገልግሎት በመዘጋቱ ሃገሪቱ 146 ሚሊዮን ዶላር ማጣቷን አስታውቋል። አሁንም ቢሆንም በመላው ሀገሪቱ ኢንተርኔት በመቋረጡ ሚሊዮን ዶላሮችን እያጣች ትገኛለች ብሏል። ኢንተርኔት ከተዘጋ አንድ ወር ያለፈ ሲሆን መንግሥት እስካሁን ስለጉዳዩ ያለው ነገር የለም። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ሚዲያ ምክር ቤት እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት የኢትዮጵያ መንግሥት ኢንተርኔት እንዲከፍት ጠይቀዋል። በአሁኑ ወቅት የኢንተርኔት ገደብ የተደረገባቸው ፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ቲክቶክ እና ዩቲዩብ  ገደብ የተደረገባቸው የትስስር ገጾች ናቸው። ኢትዮጵያ ከዚህ በፊትም የኢንተርኔት ገደብ በመጣል የምትታወቅ ሲሆን በተለይም…
Read More
ሩሲያ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፖለቲካዊ ቅርጽ ማስያዝ ተገቢ አለመሆኑን ገለጸች

ሩሲያ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፖለቲካዊ ቅርጽ ማስያዝ ተገቢ አለመሆኑን ገለጸች

ሩሲያ የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፖለቲካዊ ቅርፅ ማስያዝ ተገቢ አለመሆኑን አስታወቀች፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ  ግድብ  የልማት  ጉዳይ ሆኖ ሳለ  ፖለቲካዊ ይዘት  እንዲኖረዉ የሚደረግ ጥረትን እንደምትቃወም ነው ሩሲያ ያስታወቀችው፡፡ በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር የቭግኒ  ትረኪን  ከኢትዮ ኤፍ ኤም ጋር በነበራቸው ቀይታ፤በግድቡ ላይ መንግስታቸዉ  ነፃና ገለልተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሞስኮ ከኢትዮጵያ፤ከሱዳንና ከግብጽ ጋር መልካም ግንኙነት እንዳላት የገለፁት  አምባሳደሩ፤ግድቡን የፖለቲካ ጉዳይ ለማድረግ  የሚደረገዉን ጥረት  እንደማትቀበል አስታዉቀዋል፡፡ በዚህም ሩሲያ  የግድቡ የድርድር ሂደት ወደ ፀጥታዉ ምክር ቤት  ባመራበት ወቅት መቃወሟን አስታዉሰዋል፡፡የሩሲያ መንግስት  የኢትዮጵያን  የልማት እቅድ እንደሚደግፍም ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም ሶስቱ ሀገራት በግዱቡ ዙሪያ ያላቸዉን አለመግባባት በሰላማዊ መንገድ  እንዲፈቱ  በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር  የቭገኒ ትረኪን ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ የግድቡ ግንባታ 88…
Read More
በወላይታ እናት ከጎረቤቷ ጋር ያላትን የፍቅር ግንኙነት ያወቀ ህጻን በመርዝ ተገደለ

በወላይታ እናት ከጎረቤቷ ጋር ያላትን የፍቅር ግንኙነት ያወቀ ህጻን በመርዝ ተገደለ

በወላይታ እናት ከጎረቤቷ ጋር ያላትን የፍቅር ግንኙነት ያወቀ ህጻን በመርዝ ተገደለ በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ሶዶ ዙሪያ ወረዳ በአይጥ መርዝ የተመረዘ በሶ ለልጇ አጠጥታለች የተባለችዉ የ32 ዓመቷ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋሏን ፖሊስ አስታወቀ። በዞኑ ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ቶሚ ገረራ ቀበሌ ነዋሪ የሆነችዉ ይህች ሴት ጎረቤቷ ከሆነ አባወራ ጋር በድብቅ የፍቅር ግንኙነት ጀምራለች በሚል የሚወራዉ ወሬ ከ16 አመቱ ታዳጊ ልጇ ጆሮ ይደርሳል። ልጅም እናቱ ከጎረቤታቸው ጋር የድብቅ ፍቅር ግንኙነት መመስረቷን ተከታትሎ ካረጋገጠ በኋላ በትህትና ሲያዋራት ጥፋቷን አምና ነበር ተብሏል። ይሁንና የድብቅ ፍቅር ግንኙነቷን ለባሏ እንዳይነግርባት ስጋት የገባት ይህች እናት ልጇን መርዝ አብልታ እንደገደለች ፖሊስ ገልጿል። እንደ ደቡብ ፖሊስ ምርመራ ከሆነ ይህች…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የጣለችውን የእርዳታ እቀባ እንደምታነሳ ገለጸች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የጣለችውን የእርዳታ እቀባ እንደምታነሳ ገለጸች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የጣለችውን የፋይናንስ ድጋፍ እቀባ ልታነሳ መሆኑ ተዘገበ ለሁለት ዓመታት ሲካሄድ ቆይቶ በተያዘው ዓመት ጥቅምት ወር መቋጫ ባገኘው የፌዴራል መንግሥት እና ሕወሓት ጦርነት ከመንግሥት ጋር ቅራኔ ውስጥ ገብቶ የቆየው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የቆየውን የእርዳታ እና የፋይናንስ ድጋፍ እቀባ ሊያነሳ መሆኑን መስማቱን የዘገበው ፎሬን ፖሊሲ ነው፡፡ መጽሔቱ ከባለሥልጣናት ሰምቼዋለሁ ባለው መረጃ መሠረት የባይደን አስተዳደር እቀባውን ማንሳቱን በቅርቡ አዲስ አበባ ያቀናሉ በተባሉት የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኃላፊ አንቶንዮ ብሊንክን በኩል ይፋ ያደርጋል፡፡ በሰሜኑ ጦርነት ተደጋጋሚ መግለጫዎችን ስታወጣ የቆየችውና በመንግሥት እና ሕወሓት የሠላም ስምምነት ሒደት ከፍተኛ ሚና የነበራት አሜሪካ፤ ጦርነቱ በተጀመረበት 2013 ግንቦት ወር ላይ ነበር…
Read More
ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች

ሶማሊላንድ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ልዩ ኃይሎች ድንበር አልፈው በሶሎ ግዛት ላስአኖድ ከተማ ጦርነት ውስጥ እየተሳተፉ ነው ስትል ክስ አቅርባ ነበር። በፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ የሚመራው የሶማሌላንድ ካቢኔ ባወጣው መግለጫ ግጭት ባለባት ላስአኖድ ከኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ኃይሎች በተጨማሪ የሶማሊያ እና የፑንትላንድ ወታደሮች ይገኛሉ ብሏል፡፡ ካቢኔው የሶማሌ ላንድን ዓለም አቀፋዊ ድንበር አልፈው ገብተዋል ያላቸው እነዚህ ኃይሎች ከአካባቢው እንዲወጡም አሳስቧል።  ለሶማሊላንድ ክስ ምላሽ የሰጠው የሶማሌ ክልል መንግስት በላሳኖድ ከተማ በሚካሄደው ጦርነት አንድም የሶማሌ ክልል ኃይል አባል የለም ያለ ሲሆን፣ መግለጫውንም ኃላፊነት የጎደለው ውንጀላ እንደሆነ ገልጿል፡፡ በጉዳዩ ላይ የተናገሩት የሶማሌ ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ዐብዱልቃድር ረሺድ ‹‹እኛ የሌላ ሀገር ፖለቲካ ውስጥ እጅ…
Read More
በአዲስ አበባ ባለፉት 6 ወራት ከ1ሺህ 300 በላይ ትዳር መፍረሱ ተገለጸ።

በአዲስ አበባ ባለፉት 6 ወራት ከ1ሺህ 300 በላይ ትዳር መፍረሱ ተገለጸ።

ባለፉት 6 ወራት በአዲስ አበባ ከተማ ከ1ሺህ 300 በላይ ትዳር በፍቺ መጠናቀቃቸው ተገለጸ። በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ወራት 1ሺህ342 ፍቺዎች እና 14ሺህ 136 ጋብቻዎች መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አስታውቋል። ዘንድሮ በ6 ወራት ብቻ የተመዘገበው የፍቺ ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር ተቀራራቢ ሲሆን፤ በ2014 በጀት ዓመት 1 ሺህ 623 የፍቺ ምዝገባዎች መደረጋቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ። በአዲስ አበባ ከ2012 እስከ 2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ 16 ሺህ 35 ፍቺዎች እንደተካሄዱ የወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ መረጃ ያሳያል። የወሳኝ ኩነት ምዝገባና ማስረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ቤቴልሔም እንደሚገልጹት መረጃዎቹ የሚያመላክቱት በመስሪያ ቤቱ በህጋዊ መንገድ የተመዘገቡትን ብቻ ነው።…
Read More
መንግሥት በማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ በድጋሚ ተጠየቀ

መንግሥት በማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ በድጋሚ ተጠየቀ

የኢትዮጵየ መንግሥት ፌስቡክ እና ዩቲዩብን ጨምሮ በማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ የጠየቀው ዓለም አቀፉ መብቶች ተሟጋች አምነስቲ ኢንተርናሽናል ነው፡፡  አምነስቲ የማኅበራዊ መገናኛ መድረኮቹ ከተገደቡ አንድ ወር እንደሞላቸው ዛሬ ሐሙስ የካቲት 30፣ 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ላይ አስታውቋል፡፡  በጉዳዩ ላይ የተናገሩት የአምነስቲ የምሥራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር ፍላቪያ ምዋንጎቪ፤ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ቲክቶክ እና ዩቲዩብን ማኅበረሰቡ እንዳይጠቀም ገደብ ከጣሉ አንድ ወር እንደሞላቸው አስታውሰው፤ ይህም ‹‹የዜጎችን ሃሳብን በነጻነት የመግለጽና መረጃን የማግኘት መብቶችን በግልጽ የሚጥስ ነው›› ብለዋል፡፡  በኢትዮጵያ አምነስቲ የጠቀሳቸው የማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ገደበ የተጣለባቸው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ የተፈጠረ ክስተት ተከትሎ ውጥረት በመስፈኑ ነበር፡፡  የመብቶች ተሟጋቹ በመግለጫው…
Read More
በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ ፖሊሶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ ፖሊሶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ የፖሊስ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ። በዘንድሮው የአድዋ በኣል በአዲስ አበባ ምኒልክ አደባባይ የጸጥታ ሀይሎች በዜጎች ላይ ያልተገባ ድርጊት መፈጸማቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ እና ሌሎችም ተቋማት መናገራቸው ይታቀሳል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በጉዳዪ ዙሪያ ዛሬ በሰጠው መግለጫ በዕለቱ የህግ ጥሰት በፈጸሙ የፖሊስ አባላት ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል። ኮሚሽኑ አክሎም በዓሉ በተከበረበት እለት የከተማዋን ሰላም አውከዋል በሚል 878 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር አውያለሁ ብሏል። በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉት ውስጥም 557ቱ ከሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ መሆናቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን…
Read More