ዜና

ማስተርካርድ ፋውንዴሽን ለ12 የኢትዮጵያ ጀማሪ ተቋማት 720 ሺህ ዶላር ድጋፍ አደረገ

ማስተርካርድ ፋውንዴሽን ለ12 የኢትዮጵያ ጀማሪ ተቋማት 720 ሺህ ዶላር ድጋፍ አደረገ

ለስምንት ሳምንታት ያህል ማመልከቻዎችን ሲቀበል ከቆየ በኋላ፣ ሪች ፎር ቼንጅ ኢትዮጵያ (Reach for Change Ethiopia) በዛሬው ዕለት የማስተርካርድን ኤድቴክ ፕሮግራም የመጀመሪያውን ዙር የተቀላቀሉትን 12 የኤድቴክ ሥራ ፈጣሪዎች ይፋ አድርጓል። “ኤድቴክ” (EdTech) በእንግሊዝኛው ትምህርት እና ቴክኖሎጂን አጣምሮ የያዘ ቃል ሲሆን፣ ትምህርትን አሳታፊ በሆነና ምቹ መንገድ ለማቅረብ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀምን የሚገልጽ ሐሳብ ነው። ፕሮግራሙ የሪች ፎር ቼንጅ እና የማስተርካርድ ፋውንዴሽን አጋርነት አንድ አካል ሲሆን፣ የአጋርነቱ ዓላማም ለተመረጡ የኤድቴክ ድርጅቶች ቁልፍ የሆነ የቢዝነስና የፋይናንስ ድጋፍ መስጠት ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ ፕሮግራሙ ለድርጅቶቹ አዲስን ነገር ስለ መማር ሳይንስ፣ ስለ እድገትና መስፋፋት፣ ስለ ዘላቂነት እንዲሁም ተጽዕኖ ስለ መፍጠር ምልከታን የሚያስጨብጥ ይሆናል። “እነዚህ ፕሮግራሙን የተቀላቀሉ 12 የኤድቴክ…
Read More
ሳፋሪኮም እና ገበያ ኩባንያ የኢትዮጵያን የሥራ ፈጠራ ሥነ ምህዳር የሚያሳድግ “ታለንት ክላውድ” ጀመሩ

ሳፋሪኮም እና ገበያ ኩባንያ የኢትዮጵያን የሥራ ፈጠራ ሥነ ምህዳር የሚያሳድግ “ታለንት ክላውድ” ጀመሩ

ሳፋሪኮም ከገበያ ኩባንያ ጋር በአጋርነት፣ እንዲሁም የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (JICA) ድጋፍ ታክሎበት “ሳፋሪኮም ታለንት ክላውድ” የተሰኘ ፕሮግራም ይፋ አድርገዋል። ፕሮግራሙ የመረጃ መረብን በመጠቀም የሥራ ዕድልን የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል። ፕሮግራሙ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነና ቀጣዩን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎች እንዲሁም የዲጅታሉ ዓለም መሪዎችን አቅም ለማሳደግ ያለመ ነው። ይህ የተለየ አሠራርን ይዞ የመጣው ፕላትፎርም እስከ 2024 እ.ኤ.አ ማብቂያ ድረስ፣ ለ10 ሺሕ ልዩ ልዩ ክህሎት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች አጠቃላይ የአቅም ግንባታ እንዲሁም የሥራ ጉዟቸውን ማሳደጊያ ዕድሎችን የሚያቀርብ ነው። ይህንን በማድረግ፣ በአገሪቱ ውስጥ የሚስተዋለውን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂውን ኢንዱስትሪ ዕድገት የገታውን የቴክኖሎጂ ክህሎት እጥረት ለመቅረፍ ፕሮግራሙ ዒላማ ያደርጋል። "የሳፋሪኮም ታለንት ክላውድ “ለመጪው ዲጂታል ዘመን የኢትዮጵያንን…
Read More
ዳሸን ባንክ ለሶስተኛ ጊዜ የዳሸን ከፍታ የስራ ፈጠራ ውድድርን ሊጀምር ነው                                                                                 

ዳሸን ባንክ ለሶስተኛ ጊዜ የዳሸን ከፍታ የስራ ፈጠራ ውድድርን ሊጀምር ነው                                                                                 

ዳሸን ባንክ በስራ ፈጠራ ዘርፍ የበኩሉን አስተዋፅኦ ለማበርከት እየተገበረ ያለው ዳሸን ከፍታ የስራ ፈጠራ ውድድር ለሶስተኛ ጊዜ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ይካሄዳል፡፡ ባንኩ ውድድሩን ስኬታማ በሆነ መልኩ ለማካሄድ በአማካሪነት ከቀጠረው ዊቬንቸር ሆልዲንግስ ከተሰኘ ሃላፊነቱ የተወሰነ ድርጅት እንዲሁም የሚዲያ አጋር ከሆነው የአፍሪካ ሬኔሳንስ ቴሌቪዥን (አርትስ ቲቪ) ጋር ዛሬ በዋናው መስሪያ ቤት ስምምነት መፈራረሙን ለኢትዮ ነጋሪ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ የዘንድሮው ውድድር በባህር ዳር፣ ደሴ፣ መቀሌ፣አዳማ፣ድሬዳዋ፣ወላይታ፣ ሃዋሳ፣ጅማ እና አዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን በነዚህ ከተሞች በባንኩ ቅርንጫፎች የሰልጣኞች ምዝገባ ከሰኔ 18 እስከ ሰኔ 29-2016 ዓ.ም ይከናወናል፡፡ ለተመዘገቡ ሰልጣኞች በስራ ፈጠራ ዙሪያ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የሚያስችል ስልጠና በነዚህ ከተሞች ከተሰጠ በኋላ ሰልጣኞቹ የፈጠራ መነሻ ሃሳባቸውን በፅሁፍ በባንኩ…
Read More
ካሳሁን ፎሎ የዓለም ሥራ ድርጅት አስተዳድር አባል ሆነው ተመረጡ

ካሳሁን ፎሎ የዓለም ሥራ ድርጅት አስተዳድር አባል ሆነው ተመረጡ

የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለቀጣዮቹ 3 ዓመታት የዓለም ሥራ ድርጅት አስተዳድር አባል ሆነው ተመርጠዋል፡፡ በጀኔቫ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ባለው የዓለም ሥራ ድርጅት (ILO) 112ኛ ጉባኤ ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓ.ም በተካሄደው ስብሰባ ለቀጣይ 3 ዓመታት በበላይነት የሚቆጣጠሩና የሚያስተዳድሩ አካላትን ከሠራተኞች ፣ከመንግሥታትና ከአሠሪዎች መካከል ለመምረጥ ባደረገው እንቅስቃሴ  ካሳሁን ፎሎ  የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ባገኙት ከፍተኛ ድምፅ የዓለም ሥራ ድርጅት የሚያስተዳድረው አካል አባል በመሆን መመረጣቸው ተገልጿል፡፡ በተመሳሳይ 112ኛ ጉባኤ ቅዳሜ ግንቦት 30 ቀን 2016 ባካሄደው ስብሰባው የዓለም ሥራ ድርጅትን በበላይነት የሚያስተዳድር (Governing Body)  ምክትል አባል ሀገራት መካከል ኢትዮጵያን አንዷ አድርጎ መርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ከተወዳደሩት ሰባት ሀገራት…
Read More
በርበራ ወደብ በዓለም ባንክ የጥራት መመዘኛ ከአፍሪካ በቀዳሚነት ተመረጠ

በርበራ ወደብ በዓለም ባንክ የጥራት መመዘኛ ከአፍሪካ በቀዳሚነት ተመረጠ

የዓለም ባንክ በመላው ዓለም ያሉ ወደቦች እቃ የመጫን አቅማቸውን የተመለከተ አሁናዊ ያሉበትን ሁኔታ አስመልክቶ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የእቃ ጫኝ ኮንቴይነር የመያዝ አቅማቸውን መሰረት በማድረግ የወደቦችን ደረጃ ያወጣው ባንኩ ኢትዮጵያ የባህር ሀይሏን ልታቋቁምበት ያሰበችበት በርበራ የተሻለ ደረጃን አግኝቷል፡፡ በባንኩ ሪፖርት መሰረት የራስ ገዟ ሶማሊላንድ ንብረት የሆነው በርበራ ወደብ ከሰሃራ በረሃ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ የመጀመሪያው ወደብ ተብሏል፡፡ በርበራ ወደብ በዓለም ካሉ ወደቦች በ103ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ከሰሀራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ ቀዳሚው ሆኗል፡፡ ሞቃዲሾ ወደብ ከበርበራ ወደብ በመቀጠል በሁለተኝነት ሲጠቀስ የጊኒው ኮናክሪ በሶስተኝነት ሲቀመጥ  የኢኳቶሪያል ጊኒው ማለቡ ወደብ ደግሞ በአራተኝነት ተቀምጧል፡፡ ከመላው ዓለም ደግሞ የቻይናው ያንግሻህ ወደብ በአንደኝነት ሲቀመጥ…
Read More
ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ዓመት 1 ትሪሊየን ብር አመታዊ በጀት መደበች

ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ዓመት 1 ትሪሊየን ብር አመታዊ በጀት መደበች

የሚንስትሮች ምክር ቤት በ34ኛ መደበኛ ስብሰባው የ2017 በጀት አመት የፌዴራል መንግስት ረቂቅ በጀት አዘጋጅቷል። የ2017 ዓ.ም የፌደራል መንግስት በጀት የአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነውን የ2016-2018 የልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችን እና የ2017-2021 የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚና የፊስካል ማዕቀፍን ማስፈጸም እንዲቻል በሚያደርግ መልኩ መዘጋጀቱን አስታውቋል። እንዲሁም የ2016 የፌደራል መንግስትን የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም መነሻ በማድረግ፤ የመንግስት የፋይናንስ አቅም እና ተጠባቂ ገቢዎችን ታሳቢ በማድረግ እንዲሁም አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የተሰጣቸውን ተልኮና ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስፈልጋቸውን ወጪ በመገምገም እንዲዘጋጅ መደረጉንም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በዚሁ መሰረት ለፌዴራል መንግስት መደበኛ ወጪዎች ፣ ለካፒታል ወጪዎች ፣ ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ…
Read More
በኢትዮጵያ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የታሰሩ ሁሉ ከእስር እንዲለቀቁ ኢሰመኮ አሳሰበ

በኢትዮጵያ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የታሰሩ ሁሉ ከእስር እንዲለቀቁ ኢሰመኮ አሳሰበ

በአማራ ክልል ታውጆ የነበረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዛሬ አብቅቷል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ምክንያቱን በአማራ ክልል የተከሰተውን ግጭት ያደረገው እና ለ10 ወራት የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ አዋጅ የጊዜ ገደብ በማለቁ በእስር የቆዩ ሰዎች እንዲለቀቁ አሳስቧል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው በአማራ ክልል በመንግሥት እና በታጣቂ ኃይሎች (በተለምዶ “ፋኖ”) መካከል ከሚካሄደው የትጥቅ ግጭት ጋር ተያይዞ የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ አዋጅ የጊዜ ገደብ በማለቁ በእስር የቆዩ ሰዎች የመልቀቅ ሂደት እንዲቀጥልም አሳስቧል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የነበረው እና ጥር 24 ቀን 2016 ዓ.ም. ለተጨማሪ 4 ወራት የተራዘመው የአስቸኳይ ጊዜ…
Read More
ኢትዮጵያ የዳሌና ጉልበት መገጣጠሚያ ንቅለ ተከላ ሕክምና መስጠት ጀመረች

ኢትዮጵያ የዳሌና ጉልበት መገጣጠሚያ ንቅለ ተከላ ሕክምና መስጠት ጀመረች

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሙሉ ዳሌና ጉልበት መገጣጠሚያ ቅየራ ህክምና በየካቲት 12 ሆስፒታል መሰጠት ተጀመረ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የአጥንት ቀዶ ህክምና እና የመገጣጠሚያ ቅየራ ከፍተኛ ቀዶ ህክምና አገልግሎትን በይፋ መሰጠት መጀመሩን አስታውቋል። የአጥንት ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት እና የመገጣጠሚያ ቅየራ እንዲሁም የአርትሮስኮፒ  ህክምና ሠብ ስፔሻሊስት ሃኪም የሆኑት ዶ/ር ሰኢድ መሐመድ እንደተናገሩት  በአሁኑ ወቅት የሙሉ ዳሌ እና ጉልበት መገጣጠሚያዎች ቅየራ ከፍተኛ የቀዶ ህክምና አገልግሎትን ሆስፒታሉ በይፋ መስጠት ተጀምሯል። በከፍተኛ ሁኔታ የተጎዳን የዳሌ መገጣጠሚያ ሙሉ ለሙሉ በማስወገድ በሌላ  ሰው ሰራሽ በሆነ አካል በመተካት ይህ አይነቱ ህክምና እንደሚሰጥ ተገልጿል። ይህ አገልግሎት በኢትዮጵያ ህክምና ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሠጥ ሲሆን በዳሌና…
Read More
ኢሕአፓ ከሀገራዊ ምክክሩ ራሱን አገለለ

ኢሕአፓ ከሀገራዊ ምክክሩ ራሱን አገለለ

ኢሕአፓ ያስቀመጣቸው ቅድመሁኔታዎች እስከሚሟሉ ድረስ ከዛሬ ከግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ. ም ጀምሮ እራሱን ከሀገራዊ ምክክሩ ያገለለ መሆኑን አስታወቋል። ኢሕአፓ ኮሚሽኑ ሲመሠረት ከነበረው እውነታ ባሻገር የተፈጠሩ ግጭቶችን ለሀገራችን ቀውስም ወሳኝ ቦታ ያላቸው ሁኔታዎችን ለማካታት የሚያስችል ተልዕኮም ይሁን ህጋዊ ማዕቀፍ አለመኖሩ አሁን እየተካሄደ ባለበት መልኩ የኮሚሽኑ የሥራ ውጤት በአገራችን ውስጥ ዘላቂ ሰላምን ያመጣል ብሎ እንደማያምን ገልጿል። ኢሕአፓ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተስፋፉ የመጡትን ቀውሶች በአገራዊ በቅንነት ምናልባት በድርድርና ምክክር ሊፈቱ ይችሉ ይሆናል በሚል ተስፋ ለተወሰኑ ዐመቶች ሲሳተፍባቸው የቆየ መሆኑን በመግለጽ ''ገዥዎቻችን ችግሮችን በቅንነትና በከፍተኛ የሃላፊነት ስሜት ለመፍታት ከመሞከር ይልቅ አገራዊ ምክክርና መግባባትን የራሳቸውን ሥልጣን ማጠናከሪያና የዓለምአቀፉን ማኅበረሰብ ማደናገሪያ'' አድርገው ሲጠቀሙበት ቆይተዋል ብሏል። አሁን…
Read More
ኢትዮጵያ በሶማሊያ ያለው ሰላም አስከባሪ ጦሯን ልታስወጣ ነው

ኢትዮጵያ በሶማሊያ ያለው ሰላም አስከባሪ ጦሯን ልታስወጣ ነው

በሶማሊያ የሰፈረው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሰራዊት በቀጣይ ታህሳስ ወር ሀገሪቱን ለቆ ይወጣል ብሎ እንደሚጠብቅ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር ሰላም አስከባሪ ጦር ወደ ሶማሊ ከላኩ ሀገራት መካከል አንዷ ናት፡፡ ከኢትዮጵያ በተጨማሪም ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ኡጋንዳ እና ቡሩንዲ ጦራቸውን ወደ ሶማሊያ የላኩ ሀገራት ናቸው፡፡ ሶማሊያ በሀገሯ በሰላም ማስከበር ተልእኮ ላይ የሚገኙ ሁሉም የኢትዮጵያ ወታደሮች በመጪው ታህሳስ ወር ላይ ሙሉ ለሙሉ ጠቅልለው ይወጣሉ ብላ እንደምትጠብቅ አስታውቃለች። የሶማሊያ ፕሬዝዳንት የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሁሴን ሼክ አሊ ለቪኦኤ እንዳሉት የአፍሪካ ህብረት በሶማሊያ የሽግግር ተልዕኮ (ATMIS) በቀጣይ አመት ታህሳስ ወር ተልዕኮው ካበቃ በኋላ “የኢትዮጵያ ወታደሮች በአፍሪካ ህብረት የሚመራው ሃይል አባል አይሆኑም” ብሏል። የፕሬዚዳንቱ የደህንነት አማካሪው አክለውም…
Read More