Berberaport

ኢትዮጵያ የበርበራ ወደብን መጠቀም ጀመረች

ኢትዮጵያ የበርበራ ወደብን መጠቀም ጀመረች

የሶማሌላንድ የገንዘብ እና ልማት ሚኒስቴር ዛሬ በሶማሌላንድ በርበራ ወደብ የኢትዮጵያ ትራንዚት ማሳለጫ ቢሮዎች ስራ መጀመራቸውን ገልጿል። የሶማሌላንድ የንግድና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አብዲረሺድ ኢብራሂም ደግሞ  "የሶማሌላንድ መንግሥት በበርበራ ወደብ የኢትዮጵያ ትራንዚት ማሳለጫ ቢሮዎችን ስራ አስጀምሯል " ሲል ይፋ አድርገዋል። "ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲሉ ገልጸዋል። ይህ ውጥን ቀጠናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ለማጠናከር ሶማሌላንድ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ሲሉ አክለዋል። ቢሮው በወደቡ የሚራገፉ ጭነቶችን ወደ ኢትዮጵያ የተለያዩ መዳረሻዎች እንዲጓጓዙ የሚያሳልጥ ነውም ተብሏል። በርበራ ወደብ በተባበሩት አረብ ኤሜሬትሱ DP World ይተዳደራል የተባለ ሲሆን የበርበራ ወብ ዋና ስራ አስፈፃሚ ስፓቺ ዋታንቫራቺ ተገኝተው…
Read More
በርበራ ወደብ በዓለም ባንክ የጥራት መመዘኛ ከአፍሪካ በቀዳሚነት ተመረጠ

በርበራ ወደብ በዓለም ባንክ የጥራት መመዘኛ ከአፍሪካ በቀዳሚነት ተመረጠ

የዓለም ባንክ በመላው ዓለም ያሉ ወደቦች እቃ የመጫን አቅማቸውን የተመለከተ አሁናዊ ያሉበትን ሁኔታ አስመልክቶ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የእቃ ጫኝ ኮንቴይነር የመያዝ አቅማቸውን መሰረት በማድረግ የወደቦችን ደረጃ ያወጣው ባንኩ ኢትዮጵያ የባህር ሀይሏን ልታቋቁምበት ያሰበችበት በርበራ የተሻለ ደረጃን አግኝቷል፡፡ በባንኩ ሪፖርት መሰረት የራስ ገዟ ሶማሊላንድ ንብረት የሆነው በርበራ ወደብ ከሰሃራ በረሃ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ የመጀመሪያው ወደብ ተብሏል፡፡ በርበራ ወደብ በዓለም ካሉ ወደቦች በ103ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ከሰሀራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ ቀዳሚው ሆኗል፡፡ ሞቃዲሾ ወደብ ከበርበራ ወደብ በመቀጠል በሁለተኝነት ሲጠቀስ የጊኒው ኮናክሪ በሶስተኝነት ሲቀመጥ  የኢኳቶሪያል ጊኒው ማለቡ ወደብ ደግሞ በአራተኝነት ተቀምጧል፡፡ ከመላው ዓለም ደግሞ የቻይናው ያንግሻህ ወደብ በአንደኝነት ሲቀመጥ…
Read More