Blog

በፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ የግድያ ሙከራ ተፈጸመ

በፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ የግድያ ሙከራ ተፈጸመ

በሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን መኖሪያ በሆነው የክሪምሊን ቤተ መንግስት ላይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን አርቲ ዘግቧል፡፡ የድሮን ጥቃቱ ያነጣጠረው በሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ ሲሆን ጥቃቱ ሲፈጸም ፕሬዝዳንቱ በቦታው አልነበሩም ተብሏል፡፡ የቤተ መንግስቱ ቃል አቀባይ ድሚትሪ ፔስኮቭ እንዳሉት አደጋው በሁለት ድሮኖች የታገዘ ሲሆን የየት ሀገር ስሪት እንደሆነ እስካሁን አልታወቀም፡፡ በድሮኖቹ ጥቃት የተጎዳ ሰው አለመኖሩን የተናገሩት ቃል አቀባዩ ሞስኮ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ መጀመሯንም አክለዋል፡፡ የሞስኮ ከተማ ከንቲባ በበኩላቸው በከተማዋ ከተፈቀደላቸው የደህንነት ተቋማት ውጪ የድሮን እንቅስቃሴ መታገዱን ገልጸዋል፡፡ ፊንላድን እየጎበኙ ያሉት የዩክሬን ፕሬዝዳንት ከሄልስንኪ እንዳሉት በክሪምሊን ቤተ መንግስት ላይ ተፈጸመ ስለተባለው የድሮን ጥቃት መረጃ የለኝም ብለዋል፡፡
Read More
የፌደራል መንግሥት እና ኦሮሚያ ነጻነት ሰራዊት ድርድር አለመሳካቱ ተገለጸ

የፌደራል መንግሥት እና ኦሮሚያ ነጻነት ሰራዊት ድርድር አለመሳካቱ ተገለጸ

የመንግስት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ በኦሮሚያ ክልል ያለውን ግጭት በማስወገድ ሰላምን ለማምጣት ያለመውና በታንዛኒያ ሲካሄድ የቆየው የሰላም ውይይት የመጀመሪያ ምዕራፍ ተጠናቋል ብሏል። ውይይቱ በአብዛኛው በአዎንታዊ መልኩ የተከናወነ ነው ያለው ሚንስቴሩ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ግን በዚህኛው የውይይት ምዕራፍ ስምምነት ላይ አልተደረሰም ብሏል። ግጭቱን በዘላቂነትና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለማስቆም እንዲቻል ሁለቱም አካላት የሰላም ውይይቱን መቀጠል አስፈላጊ መሆኑ ላይ እንደተግባቡ ተገልጿል። በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትና እስካሁን ሲመራባቸው በነበሩ መሠረታዊ መርሖች መሠረት ግጭቱን በሰላማዊ መልኩ ለመፍታት መንግስት የጸና አቋም እንዳለው በመግለጫው ላይ ተጠቅሷል። ይህንን መልካም አጋጣሚና በውይይት ችግሮችን የመፍታት በጎ ጅምር በመጠቀም ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ የኢትዮጵያ መንግሥት ፅኑ አቋም እንዳለው አስታውቋል። አሜሪካ በታንዛኒያ ራስ…
Read More
በኢትዮጵያ በኮሌራ ወረርሽኝ የ84 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ በኮሌራ ወረርሽኝ የ84 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የኮሌራ ወረርሽኝ መከሰቱ ከተገለጸ ስድስት ወራት ያስቆጠረ ሲሆን የሰዎች ህይወት ማለፉን የኢትዮያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል፡፡ በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከአምስት ሺህ 500 በላይ ሰዎች በኮሌራ ወረርሽኝ መጠቃታቸውም ተገለጿል ። የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ርዳታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ በይፋዊ የትዊተር ገጹ ባወጣው መረጃ ከነሐሴ 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጀምሮ ከ5,500 በላይ ሰዎች ኢትዮጵያ ውስጥ በኮሌራ ተጠቅተዋል ። የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ 118 ከፍተኛ ተጠቂ አካባቢዎች የለየ ሲሆን የወረርሽኙ ተጠቂዎች የሚታከሙባቸው 41 የኮሌራ ህክምና ማዕከላት ማቋቋሙን ገልጿል። በዋናነት ችግሩ የታየባቸው አካባቢዎች የሶማሌ፤ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች፤ የኦሮሚያ፤ የአፋር፤ የአማራ እና የትግራይ ክልሎች ናቸውም ብሏል ።  አጣዳፊ ተቅማጥ የሚያስከትለው የኮሌራ ወረሽኝ የሚሰራጨው…
Read More
አሜሪካ የ2024 ዲቪ ሎተሪ እድለኞችን ይፋ አደረገች

አሜሪካ የ2024 ዲቪ ሎተሪ እድለኞችን ይፋ አደረገች

አሜሪካ በዓለም ላይ በየዓመቱ 50 ሺህ ሰዎችን በዳይቨርሲቲ ቪዛ ወይም ዲቪ ሎተሪ አማካኝነት ወደ ሀገሯ ታስገባለች። ባሳለፍነው ጥቅምት እና ህዳር ወራት ላይ በበይነ መረብ አማካኝነት የተሞላው የ2024 ድቪ ሎተሪ አሸናፊዎች መታወቃቸው ተገልጿል። የዲቪ 2024 ማመልከቻ የሞሉ ዜጎችም መመረጣቸውን እና አለመመረጣቸውን የፊታችን ቅዳሜ ማለትም ከሚያዚያ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ማወቅ እንደሚችሉ በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲ በትዊተር ገጹ ጽፏል። ኢምባሲው አክሎም በዲቪ ሎተሪ ድረገጽ ላይ በመግባት አመልካቾች ያመለከቱበትን ልዩ ቁጥር ወይም ኮድ በማስገባት ማወቅ ይችላሉም ብሏል። ይህ በዚህ እንዳለም የዲቪ ሎተሪ አሸንፋችኋል፣ ከአሜሪካ ኢምባሲ ነው እምንደውለው በሚል የሚያጭበረብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች እንዲጠነቀቁም አሳስቧል። ለዲቪ ሎተሪ ስለማሸነፋቸው እና አለመድረሱን አመልካቾች በራሳቸው…
Read More
የኢትዮጵያ ሚዲያዎች በጥቃት ውስጥ እንደሚገኙ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሚዲያዎች በጥቃት ውስጥ እንደሚገኙ ተገለጸ

ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ብቻ 29 ጋዜጠኞች በታሰሩባት ኢትዮጵያ፤ የፕሬስ ነጻነት “ጉልህ ጥቃት” እንዳጋጠመው ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና የደቡባዊ አፍሪካ ሚዲያ ኢንስቲትዩት አስታወቁ። ባለስልጣናት የፕሬስ ነጻነትን ማፈን በሚፈልጉባቸው በምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ሀገራት፤ በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰው ጥቃት እየጨመረ መምጣቱንም ተቋማቱ ገልጸዋል። ሁለቱ ተቋማት ይህን ያሉት ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 25፤ 2015 ታስቦ የሚውለውን የዓለም የፕሬስ ነጻነትን በማስመልከት በጋራ ባወጡት ዳሰሳ ነው። ዳሰሳው ኢትዮጵያን ጨምሮ በ10 የአፍሪካ ሀገራት ያለውን የመገናኛ ብዙሃን ነጻነትን እና በጋዜጠኞች ላይ እየደረሱ ያሉ ጥቃቶችን በማሳያነት በማንሳት ዳሰሳ አድርጓል። በዚሁ ዳሰሳ፤ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት በርካታ ጋዜጠኞችን በማሰር ከኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በመለጠቅ ስሟ የተጠቀሰው ኢትዮጵያ ነች።…
Read More
ሻሸመኔ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ወደ ፕሪሜር ሊግ አደገ

ሻሸመኔ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ወደ ፕሪሜር ሊግ አደገ

በሳሙኤል አባተ በምድብ ለ ሀዋሳ ላይ እየተከናወነ በሚገኜው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር ሻሸመኔ ከነማ ቀሪ 4 ጨዋታ እያለው ወደ ቤቲኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሜር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል ። በዕለተ ማክሰኞ ሚያዚያ 24 አዲስ አበባ ከነማ በቦዲቲ ከነማ 2ለ1 መሸነፉን ተከትሎ ሻሸመኔ ቀሪ 4 ጨዋታዎች እያሉት በ 47 ነጥብ ፕሪሜር ሊጉን ተቀላቅሏል ። አዲስ አበባ ከነማ በ35 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በቀጣይ ቀሪ 2 ክለቦች ሊጉን ይቀላቀላሉ ። በምድብ ሐ  ሀምበርቾ ዱራሜ በ 42 ነጥብ ገላን ከተማ በ 40 ነጥብ የምድቡ አንደኛ ሁኖ ለማለፍ የሚያደርጉት ፉክክር ይጠበቃል ። በተመሳሳይ በምድብ ሀ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ 50 ነጥብ ምድቡን ሲመራ ቤንቺ ማጅ በ…
Read More
መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር እየተደረገ ስላለው ድርድር መረጃ እንዲሰጥ ተጠየቀ

መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር እየተደረገ ስላለው ድርድር መረጃ እንዲሰጥ ተጠየቀ

መንግሥት ‹‹ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት›› ጋር ስለሚያደርገው ድርድር በቂ መረጃ ይስጥ ሲል ኢዜማ አሳስቧል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) መንግሥት ራሱን ‹‹የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት›› ከሚለው ታጣቂ ቡድን ጋር ስለሚያደርገው ድርድር በቂ መረጃ ይስጥ ሲል ጠይቋል፡፡  ፓርቲው በተለይ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኦሮሚያ ክልል በተደጋጋሚ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት ሲገደሉ ንብረታቸውም ሲወድምና ከቀያቸው ሲፈናቀሉ በግልጽ ተመልክተናል ብሏል፡፡ መንግስትም በተደጋጋሚ የተፈፀሙትን በደሎች ይህ ታጣቂ ቡድን ሲፈፅማቸው እንደነበር ከማሳወቁ አንፃር ይህን መሰል የዜጎች ሰቆቃ የሚያስቆም ድርድር ውስጥ መግባቱን ፓርቲው እንደሚደግፈው ገልጿል፡፡  ይሁንና ብልጽግና ኢትዮጵያን መምራት ከጀመረበትን ጊዜ ጨምሮ ባለፉት አምስት ዓመታት በተለያየ ጊዜ የሚፈጸሙ ድርድሮች ግልጽነት የጎድላቸው እና አፈፃፀማቸው ደካማ መሆናቸውን ፓርቲው በመግለጫው አስታውቋል፡፡ ለአብነትም ከሕወሓት…
Read More
አቶ ግርማ የሺጥላ በምስራቅ አማራ ፋኖ መገደላቸውን የአማራ ክልል ገለጸ

አቶ ግርማ የሺጥላ በምስራቅ አማራ ፋኖ መገደላቸውን የአማራ ክልል ገለጸ

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ባለፈው ሳምንት ለተገደሉት የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ ግድያ በምሥራቅ አማራ ፋኖ የሚመራው ‹‹ቡድን›› ነው ሲል የገለጸው ዛሬ ማክሰኞ ባወጣው መግለጫ ነው፡፡  የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ ባልታወቁ ግለሰቦች ግድያ እንደተፈጸመባቸው የተገለጸው ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ሚያዝያ 19፣ 2015 ነበር፡፡ በወቅቱ ግድያውን ይፋ ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለግድያው ‹‹ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ ያቃታቸው›› ያሏቸው ነገር ግን በሥም ያልጠቀሷቸውን አካላት ተጠያቂ አድርገው ነበር፡፡ አክለውም ‹‹ልዩነትን በሠለጠነ መንገድ መፍታት ባህል በሆነበት ክፍለ…
Read More
የአውሮፓ ህብረት በአማራ እና ኦሮሚያ ያለው ውጥረት እንደሚያሳስበው ገለጸ

የአውሮፓ ህብረት በአማራ እና ኦሮሚያ ያለው ውጥረት እንደሚያሳስበው ገለጸ

የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮ ነጋሪ በላከው መግለጫ እንደገለጸው ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ግንኙነት ሙሉ ለሙሉ ወደ ነበረበት እንዲመለስ መወሰኑን ገልጿል፡፡ የህብረቱ አባል ሀገራት ውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ባደረጉት ስብሰባ ህብረቱ በሰሜን ኢትዮጵያ ባጋጠመው ጦርነት ምክንያት ሻክሮ የነበረው ግንኙነት መሻሻሉን አስታውቋል፡፡ በተለይም የፌደራል መንግስት እና ህወሃት በአፍሪካ ህብረት አደራዳረነት የሰላም ስምምነት መፈራረማቸውን እንደተቀበለው ህብረቱ ገልጿል፡፡ በዚህም ምክንያት የአውሮፓ ህብረት እና የኢትዮጵያ ግንኙነት ወደ ነበረበት እንዲመለስ መወሰኑን አስታወቋል፡፡ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ ድጋፍ እንደሚያደርግ የገለጸው ህብረቱ የተጀመረው የሽግግር ፍትህ እና ብሄራዊ ምክክር እቅድ ውጤታማ እንዲሆን ድጋፍ አደርጋለሁም ብሏል፡፡ ይሁንና በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለው የፖለቲካ መካረር የጸጥታ ችግሮች መባባስ እንዲሁም የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እንዳሳሰበው ጠቅሷል፡፡…
Read More
ኢትዮጵያ ብሔራዊ የውትድርና ፖሊሲ አጸደቀች

ኢትዮጵያ ብሔራዊ የውትድርና ፖሊሲ አጸደቀች

ዕድሜያቸው 18 ዓመት የሞላቸውና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ወታደራዊ ስልጠና ወስደው ለሁለት ዓመት ብሔራዊ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል አዲስ አዋጅ ፀድቋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የብሔራዊ ውትድርና አገልግሎት አዋጅን አጽድቋል። ምክር ቤቱ ከትናንት በስቲያ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፣ መንግስት አዘጋጅቶ ያቀረበውን የተሻሻለ የመከላከያ ሰራዊት ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል፡፡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጪ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ዲማ ነገዎ እንደተናገሩት፤ ተማሪዎች በፈቃዳቸው በመደበኛ መከላከያ ሰራዊት ወይም የብሔራዊ ተጠባባቂ ሃይል አባል የሚሆኑ ከሆነ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ተያያዥ መብቶችንና ጥቅሞች እንዲጠብቁላቸው ያደርጋል ብለዋል፡፡ በመንግስት ተዘጋጅቶ የቀረበው የተሻሻለ የመከላከያ ሰራዊት ረቂቅ አዋጅ፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ ሆኖ የተጣለበትን ሀገርን…
Read More