Ukraine

ኢትዮጵያዊው ቅጥረኛ ወታደር ከዩክሬን ጎን ሆኖ እየተዋጋ እንደሆነ ተገለጸ

ኢትዮጵያዊው ቅጥረኛ ወታደር ከዩክሬን ጎን ሆኖ እየተዋጋ እንደሆነ ተገለጸ

ለአንድ ሳምንት በሚል የተጀመረው የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ሁለት ዓመት ያለፈው ሲሆን ጦርነቱ አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል። ሩሲያ ከዩክሬን ጎን ቆመው እየተዋጉ ያሉ ቅጥረኛ ወታደሮችን ማንነት ይፋ አድርጋለች። እንደ ሩሲያ መከላከያ ሚንስቴር መረጃ ከሆነ አንድ ኢትዮጵያዊ ከዩክሬን ጎን ሆኖ ሩሲያን እየወጋ ይገኛል ተብሏል። ይህ ኢትዮጵያዊ እስካሁን በህይወት እንዳለ የተገለጸ ሲሆን ወታደሩ ኢትዮጵያዊ ከመሆኑ ውጪ ማንነቱ ይፋ አልተደረገም። በአጠቃላይ ይህ ጦርነት ከተጀመረበት የካቲት 2014 ዓ.ም ጀምሮ ከ89 ሀገራት የተውጣጡ 13 ሺህ 387 ቅጥረኛ ወታደሮች ከዩክሬን ጎን ተሰልፈዋል። ከጠቅላላው ቅጥረኛ ወታደሮች ውስጥም 5 ሺህ 962 ያህሉ በሩሲያ ጦር መገደላቸው ተገልጿል። ፖላንድ ቅጥረኛ ወታደሮችን በማዋጣት ቀዳሚዋ ሀገር ስትሆን 2 ሺህ 960 ዎቹ ተገድለዋል ተብሏል። ከፖላንድ በመቀጠል…
Read More
በፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ የግድያ ሙከራ ተፈጸመ

በፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ የግድያ ሙከራ ተፈጸመ

በሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን መኖሪያ በሆነው የክሪምሊን ቤተ መንግስት ላይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን አርቲ ዘግቧል፡፡ የድሮን ጥቃቱ ያነጣጠረው በሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ ሲሆን ጥቃቱ ሲፈጸም ፕሬዝዳንቱ በቦታው አልነበሩም ተብሏል፡፡ የቤተ መንግስቱ ቃል አቀባይ ድሚትሪ ፔስኮቭ እንዳሉት አደጋው በሁለት ድሮኖች የታገዘ ሲሆን የየት ሀገር ስሪት እንደሆነ እስካሁን አልታወቀም፡፡ በድሮኖቹ ጥቃት የተጎዳ ሰው አለመኖሩን የተናገሩት ቃል አቀባዩ ሞስኮ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ መጀመሯንም አክለዋል፡፡ የሞስኮ ከተማ ከንቲባ በበኩላቸው በከተማዋ ከተፈቀደላቸው የደህንነት ተቋማት ውጪ የድሮን እንቅስቃሴ መታገዱን ገልጸዋል፡፡ ፊንላድን እየጎበኙ ያሉት የዩክሬን ፕሬዝዳንት ከሄልስንኪ እንዳሉት በክሪምሊን ቤተ መንግስት ላይ ተፈጸመ ስለተባለው የድሮን ጥቃት መረጃ የለኝም ብለዋል፡፡
Read More