26
Jan
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረው የማርበርግ ቫይረስ (Marburg Viral Disease) ወረርሽኝ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር መቻሉን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመሆን ፣ ወረርሽኙ ለመጀመሪያ ጊዜ መከሰቱ በይፋ ከተነገረበት ከሕዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ሰፊ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል። በወረርሽኙ ወቅት በአጠቃላይ ለ3 ሺህ 800 ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ ቫይረሱ የተገኘባቸው 14 ሰዎች ነበሩ። ከታካሚዎቹ መካከል ዘጠኙ በበሽታው ምክንያት ሕይወታቸው ሲያልፍ፣ አምስቱ ደግሞ ተገቢውን ሕክምና አግኝተው ማገገም መቻላቸው ይታወቃል። ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ ለመቆጣጠር እንዲቻል የክትትልና ምላሽ ስርዓት ተዘርግቶ ሲሰራ መቆየቱን የገለጸው ሚኒስቴሩ በተለይም ከ4 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ተጓዦች በመውጫና…