መነሻ ገፅ

ኢትዮጵያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት ጠየቀች

ኢትዮጵያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት ጠየቀች

የኢትዮጵያ መንግስት ለሁለተኛው አገር በቀል የኢኮኖሚ ፕሮግራም ማስፈጸሚያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር ጠይቋል፡፡ ብድሩ እና እርዳታው የተጠየቀው የዓለም የገንዘብ ድርጅት አይኤምኤፍ፣ ዓለም ባንክና ኢትዮጵያ ያለባትን የውጭ ዕዳ መልሶ ከማሸጋሸግ ለማግኘት እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ተክለ ወልድ አጥናፉ ለሪፖርተር እንዳሉት ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከአሜሪካ፣ ፈረንሣይና ሌሎች ሀገራት ጋር ያላት ግንኙነት መልካም መሆኑ ብድሩ ሊገኝ ይችላል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የብድር መክፈያ ጊዜ እንዲስተካከል ጠይቃለች ያሉት አማካሪው ብድሩ ድርድር ከተደረገበት በኋላ ይለቀቃል የሚል ተስፋ መኖሩንም ጠቅሰዋል፡፡ የአሜሪካ ኮንግረስ ኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን ገደብ እ.ኤ.አ. በጁላይ ወር መጨረሻ ላይ ያነሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ፣ ይህም ገንዘቡን ለማግኘት ጥሩ እርምጃ ይሆናልም ተብሏል፡፡ 12 ቢሊዮን…
Read More
ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር ጠየቀች

ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር ጠየቀች

ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ገለጸች የቀድሞው ተዋጊዎችን የተሃድሶ ስልጠና ሰጥቶ ወደ ህብረተሰቡ ለመቀላቀል ከ554 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ እንደሚያስፈልግ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽነሩ ይህን የተናገሩት ኮሚሽኑ የቀድሞው ተዋጊዎችን መልሶ በዘላቂነት በማቋቋም ረገድ የመገናኛ ብዙሃን ሚናና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ባካሄደው ውይይት ላይ ነው፡፡ የኮሚሽኑ ጽ/ቤት ሃላፊ ገመዳ አለሚ በበኩላቸው ይህ  የገንዘብ መጠን በመነሻነት የታቀደ እንደነበረ የጠቀሱት ኮሚሽነሩ አሁን ላይ ግን ከተጠቀሰው ከፍ ማለቱን ተናግረዋል ። በኢትዮጵያ 372 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎች እንዳሉ የተሀድሶ ማዕከል እና የሀገር መከላከያ ሚንስቴር በጋራ ያጠኑት ጥናት ያስረዳል። የተመዘገበው አሐዝ ይህ ቢሆንም ቁጥር ሊያሻቅብ…
Read More
በሽብር ወንጀል የተከሰሱ ጋዜጠኞች የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቆ ሆኖ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ተወሰነ

በሽብር ወንጀል የተከሰሱ ጋዜጠኞች የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቆ ሆኖ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ተወሰነ

አራት የመገናኛ ብዙሃን ጋዜጠኞች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ በፍርድ ቤት ውድቅ ተደረጓል። በሽብር ወንጀል የተከሰሱ አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ፤ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውድቅ ተደረገ። የተከሳሾችን በቁጥጥር ስር መዋል በተመለከተ የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ያወጣውን መግለጫ በድረ ገጻቸው የጫኑ መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎቻቸውን እንዲያወርዱም ፍርድ ቤቱ አዝዟል። ይህን ትዕዛዝ የሰጠው ሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም የዋለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ችሎት ነው። ችሎቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጎ ትዕዛዞችን በሰጠበት ቅጽበት ተከሳሾች በጭብጨባ የታጀበ መፈክር አሰምተዋል። የተከሳሾቹ መፈክር እና ጭብጨባ፤ የችሎት ውሎ…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም 76 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ

ኢትዮ ቴሌኮም 76 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ

ቴሌብር የ680 ቢሊዮን ብር ግብይት መፈጸሙን ኢትዮ ቴሌኮም ገልጿል። የኢትዮ ቴሌሎም ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸምን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። ስራ አስፈጻሚዋ በመግለጫቸው እንዳሉት ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 76 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ገቢ ማግኘቱን ተናግረዋል። ከተገኘው አጠቃላይ ገቢ ውስጥም 44 በመቶው ከድምጽ ጥቅል ሲገኝ 23 በመቶው ከኢንተርኔት አገልግሎት መገኘቱን ስራ አስፈጻሚዋ አክለዋል። ተቋሙ ከውጭ ምንዛሬ አገልግሎቶች 164 ሚሊዮን ዶላር አግኝቷል ያሉት ፍሬህይወት የ4G ቴሌሎም አገልግሎት ያገኙ ከተሞች ቁጥርም ወደ 164 ከፍ ማለቱን ገልጸዋል። በአጠቃላይ የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር 72 ሚሊዮን ደርሷል የተባለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 34 ነጥብ 3 ሚሊዮን ያህሉ የቴሌብር ደንበኞች ናቸውም ብለዋል። በ2015 ዓ. ም…
Read More
የሴቶች ዓለም ዋንጫ ነገ ይጀመራል

የሴቶች ዓለም ዋንጫ ነገ ይጀመራል

እንደ ወንዶች የዓለም ዋንጫ ሁሉ በየ አራት አመቱ የሚካሄደው የሴቶች እግር ኳስ ዓለም ዋንጫ ነገ ይጀመራል። አውስትራሊያ እና ኒውዝላንድ በጋራ የሚያስተናገዱት የ2023 የፊፋ ሴቶች ዓለም ዋንጫ አዘጋጆቹ አውስትራልያ እና ኒውዝላንድ የመክፈቻ ውድድር ጨዋታን ያደርጋሉ። ውድድሩ ከፈረንጆቹ ሀምሌ 20 እስከ ነሀሴ 20 ቀን 2023 ውስጥ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ይካሄዳል ተብሏብ። ከዚህ በፊት የሴቶች ዓለም ዋንጫ በ24 ብሔራዊ ቡድኖች አማካኝነት ይካሄድ የነበረ ሲሆን በዘንድሮው ግን ፊፋ የተሳታፊ ሀገራትን ቁጥር ወደ 32 ከፍ አድርጎታል። አፍሪካ በዚህ ውድድር ላይ በአራት ሀገራት የሚወከሉ ሲሆን ናይጀሪያ ፣ ዛምቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ሞሮኮ ተሳታፊ ሀገራት ናቸው። የናይጀሪያዋ አሲሳት ኦሾላ በውድድሩ ትደምቃለች ተብሎ ከወዲሁ ትኩረት የተሰጣት ተጫዋች…
Read More
ኢትዮጵያ ለቤተሰብ እቅድ አገልግሎት የ36 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

ኢትዮጵያ ለቤተሰብ እቅድ አገልግሎት የ36 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

በጀቱ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነ ተገልጿል። የ36 ሚሊዮን በጀት ስምምነቱ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት በኢትዮጵያ የቤተሰብ ዕቅድን ተደራሽ ለማድረግ ይውላል ተብላል። በኢትዮጵያ 22 በመቶ ሴቶች የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ተደራሽ ያልሆነላቸው ሲሆን በጀቱ ከዚህ አንጻር ተጨማሪ ሴቶችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል። በበጀት ስምምነቱ ላይ የተገኙት የጤና ጥበቃ ሚንስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳሉት የቤተሰብ እቅድ አገልግሎቱን ተደራሽነት ለማጠናከር እንቅፋት ከሆኑ ችግሮች መካከል አገልግሎቱ በነፃ የሚሰጥና ወጭው በአብዛኛው  በለጋሽ አካላት የሚሸፈን በመሆኑና ከለጋሽ አካላት የሚገኘው ድጋፍ እየቀነሰ መምጣቱ ነው ብለዋል። እንዲሁም በአለም አቀፍ ደረጃ የዋጋ ንረት በመኖሩ ለግብዓት የሚያስፈልግ የበጀት ዕጥረት ማጋጠሙን የጠቆሙት ሚንስትሯ ችግሩን በመቅረፍ አቅርቦቱን እንዳይቆራረጥ ለማድረግ  በመደበኛነት ከሚመደበው በጀት…
Read More
በኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ስራዎችን የሰሩ ሰዎች ተሸለሙ

በኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ስራዎችን የሰሩ ሰዎች ተሸለሙ

በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በርካታ የበጎ አድራጎት ስራ የሰሩ ሰዎችን ማመስገን እና ለስራቸው እውቅና መስጠት አላማው ያደረገ ፕሮግራም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ማስተር አብነት ፣ ወንድም ካሊድ ፣ሚኪያስ ለገሰ እና ዘካሪያስ ኪሮስ በኢትዮጵያ ዘር፣ ቀለም እና ሀይማኖት ሳይገድባቸው የተቸገሩ ወገኖችን ለዓመታት እየረዱ መሆናቸው በመድረኩ ላይ ተጠቅሷል። ግለሰቦቹ ለሰሩት በጎ ስራ በሽማግሌዎች ምርቃት ታጅበው የምስጋና እና የእውቅና መርሀግብር ተካሂዷል። በአዲስ አበባ ስቴይ ኢዚ ሆቴል በተካሄደው በዚህ ፕሮግራም ላይ የመንግስት አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል። ምስጋና እና እውቅና ከተሰጣቸው ሰዎች መካከልም በአዲስ አበባ በበጎ ስራቸው  የተቸገሩ ሰዎች እንዲረዱ እና ህክምና  እንዲያገኙ በማድረግ የሚታወቁት ሚኪያስ ለገሰ ( የሰሊሆም የአዕምሮ መርጃ ማዕከል)…
Read More
ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ "በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞች ተተክሏል" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በዛሬው እለት 567 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል። በአንድ ቀን 500ሺ ችግኝ የመትከል ዘመቻ አማካኝነት በሀገሪቱ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ችግኝ ሲተክሉ የሚያሳዩ ፎቶዎች እና ቪዲዮዎች ተለቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የችግኝ ተከላው" ለኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት" ነው ሲሉ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዚህ አመት ብቻ ከካርቦን ሽያጭ 52 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቷን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የችግኝ ተከላው ስራ በዚሁ ከቀጠለ ከካርቦን ሽያጭ የምታገኘው ገቢ በእጥፍ እንደሚጨምር ገልጸዋል። ይሁንና በአንድ ጀምበር ተተከለ የተባለው የችግኝ መጠን በትክክል ስለመተከሉ በገለልታኛ አካል አልተረጋገጠም።
Read More
ቦይንግ ኩባንያ ከቲንክ ያንግ ጋር በመተባበር ለ60 ኢትዮጵያዊያን ስልጠና ሰጠ

ቦይንግ ኩባንያ ከቲንክ ያንግ ጋር በመተባበር ለ60 ኢትዮጵያዊያን ስልጠና ሰጠ

ለአራት ቀናት የተሰጠው ይህ ስልጠና ከቲንክ ያንግ እና ከአሜሪካው የአቪዬሽን ቦይንግ ኩባንያ ጋር በመተባበር ነው። ስልጠናው ከ20 ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ ለ60 ተማሪዎች በአዲስ አበባ ተሰጥቷል። ከሰባት ዓመት በላይ ጀምሮ እድሜ ላላቸው የተሰጠው ይህ ስልጠና ታዳጊዎች ከቴክኖሎጂ ጋር እየተዋወቁ እንዲያድጉ በማሰብ የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል። ለታዳጊዎቹ የተሰጠው የስልጠና አይነት ዌብሳይት ማበልጸግ፣ ሮቦቲንግ፣ ኮዲንግ እና አርቲፊሻል እንተለጀንስ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። ዓለም አቀፉ የአቪዬሽን ተቋም ቦይንግ የስልጠናው አካል ሲሆን የበጀት ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል። በቦይንግ ኩባንያ የመካከለኛው ምስራቅ፣ አፍሪካ እና ተርኪየ ፕሬዝዳንት የሆኑት ኩልጅት ጋታ ስልጠናው የቦይንግ ማህበራዊ ሀላፊነት አንዱ አካል ነው ብለዋል። "የኢትዮጵያ መንግሥት ድጅታል ኢኮኖሚ ለመገንባት የያዘውን እቅድ ለመደገፍ ወደ ኢትዮጵያ መጥተናል ያሉት"…
Read More
ኢትዮጵያ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የጣለችውን ገደብ አነሳች

ኢትዮጵያ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የጣለችውን ገደብ አነሳች

በኢትዮጽያ ለወራት ያህል በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ ተነስቷል። በኢትዮጵያ ከየካቲት ወር መጀመሪያ አንስቶ በኢንተርኔት አገልግሎቶች ማለትም በፌስቡክ፣ ሜሴንጀር፣ ቴሌግራም እና ቲክቶክ ላይ ገደብ መጣሉ ይታወሳል። በኢትዮጵያ የኢንተርኔት ገደብ መጣሉን ተከትሎ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንን ጨምሮ በርካታ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች መንግሥት ገደቡን እንዲያነሳ ሲጠየቅ ቆይቷል። በኢንተርኔት እገዳው ምክንያትም ኢትዮጵያ 7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ማጣቷን የመብቶችና ዴሞክራሲ እድገት ማዕከል ገልጿል፡፡ “ፖለቲካዊ አለመረጋጋቶችን ተከትሎ፤ ከ2008 ወዲህ የበይነመረብ ግንኙነትን ማቋረጥ በኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣ ችግር ነው” ያለው ማዕከሉ፤ የበይነመረብ ግንኙነት መቋረጡ የዴሞክራሲና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕድገት ጸር መሆኑን አመላክቷል፡፡ መንግሥት ዋና ዋና የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች በኢትዮጵያ እንዳይጎበኙ እገዳ መጣሉ ሕጋዊ መሰረት…
Read More