መነሻ ገፅ

ኢትዮጵያ ከ18 ሺህ በላይ የውጭ ሀገራት ዜጎችን አባረረች

ኢትዮጵያ ከ18 ሺህ በላይ የውጭ ሀገራት ዜጎችን አባረረች

የተባረሩት የውጭ ሀገራት ዜጎች ህጋዊ የነዋሪነት ፈቃድ የሌላቸው እንደሆኑ የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡ የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የበጀት ዓመቱን የዘጠኝ ወራት ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበዋል፡፡ ዳይሬክተሯ በዚህ ጊዜ እንዳሉት በሐሰተኛ የመኖሪያ ፍቃድ በአገር ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ከ18 ሺህ በላይ የውጭ አገር ዜጎችን ከአገር እንዲባረሩ ተደርጓል፡፡ ከአገር ከተባረሩት የውጭ ሀገራት ዜጎች መካከል የተወሰኑት ሐሰተኛ የመኖሪያ ፍቃድ አዘጋጅተው በገንዘብ ሲሸጡ የነበሩ እንደሚገኙበት ተቋሙ አስታውቋል፡፡ በኢንቨስትመንት ፍቃድ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የውጭ ዜጎች ለበርካታ ዓመታት በሕገወጥ ሥራዎች ላይ ተሳታፊ ኾነው እንደተገኙም ዳይሬክተሯ በሪፖርታቸው ላይ ጠቅሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ከዚህ በፊት በርካታ የውጭ ሀገር ዜጎች ሀሰተኛ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ፣…
Read More
ኢትዮጵያ የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጀት እቅድ እንዳላት ገለጸች

ኢትዮጵያ የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጀት እቅድ እንዳላት ገለጸች

ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አመታት የአፍሪካ ዋንጫ ውድድርን እንድታዘጋጅ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጄላ መርዳሳ ተናግረዋል። የአፍሪካ ዋንጫን እ.ኤ.አ በ2029 ወይም በ2031 ለማዘጋጀት እየሰራን ነው ያሉት ሚኒስትሩ ለእቅዱ መሳካትም ቢያንስ ስድስት ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ካፍ ከዚህ በፊት ያልነበሩ አዳዲስ መስፈርቶችን በማስቀመጡ ኢትዮጵያ አንድም ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም እንዳይኖራት አድርጓል ሲሉም አቶ ቀጀላ መርዳሳ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የካፍን ደረጃ የሚመጥኑ ስታዲየሞች የሌላት በመሆኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ረዘም ላሉ ጊዜያት ከሀገሩ ዉጪ ለመጫወት ተገድዶ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። የዉድድሩ አዘጋጅ ሀገራት ቢያንስ ስድስት ስታዲየሞችን እንዲያዘጋጁ ካፍ ቢያዝም ኢትዮጵያ እስካሁን የካፍን ደረጃ ያሟላ ስታዲየም የሌላት ሲሆን ውድድሩን ለማዘጋጀት እያደረገች ስላለው ዝግጅት የተባለ…
Read More
ከአላማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ50 ሺህ አለፈ

ከአላማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ50 ሺህ አለፈ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 50 ሺህ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡ እንደ ድርጅቱ ሪፖርት ከሆነ ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ ወልደያ እና ሰቆጣ ከተሞች በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች ላይ እንደተጠለሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የገለጸው ድርጅቱ ለተፈናቃዮች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ህይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡ አሁን ላይ ከለጋሽ ተቋማት እና ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እየተሟጠጠ በመሆኑ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ ለተፈናቃዮቹ መጠለያ፣ የሕክምና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባል…
Read More
የቢል እና ሜሊንዳ ጌት ሥራ አስኪያጅ ማርክ ሱዝማን ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው

የቢል እና ሜሊንዳ ጌት ሥራ አስኪያጅ ማርክ ሱዝማን ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው

የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ሥራ አስኪያጅ ማርክ ሱዝማን ከሚያዚያ ኢትዮጵያን ሊጎበኙ መሆኑን አስታወቁ፡፡ ስራ አስኪያጁ ለአንድ ሳምንት በሚያደርጉት ጉብኝት በጤና ነክ ተግዳሮቶች ላይ ለመምከርና ለኢትዮጵያውያን ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን የሚቀርፉ እድሎችን ለማመቻቸት ይሠራሉ ተብሏል። ጉብኝቱ የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ከመሪዎችና ከማህበረሰቡ ጋር በቅርበት ሆኖ በመሥራት በመላው አፍሪካ ያሉ ዜጎችን ኑሮ መሻሻል የሚያፋጥኑ መፍትሔዎችን ለመደገፍ እያሳየ ያለው ቆራጥነት አካል ነው። በዚህ ጉብኝት ወቅት፤ ሱዝማን የመንግሥት ባለሥልጣናትን፣ ለጋሽ ድርጅቶችን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ቡድኖችን፣ የሳይንስ ሰዎችን፣ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን፣ በቦታው ተገኝተው የሚሠሩ የጤና ባለሙያዎችንና እና የፈጠራ ባለሙያዎችን ጨምሮ የተለያየ ዘርፍ ላይ ከሚገኙ ባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል። በነዚህ ውይይቶች ወቅት ሱዝማን አጋሮቻቸው…
Read More
በአፍሪካ በየአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በየ ዓመቱ 250 ሺህ ሰዎች ሊሞቱ እንደሚችሉ ተገለጸ

በአፍሪካ በየአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በየ ዓመቱ 250 ሺህ ሰዎች ሊሞቱ እንደሚችሉ ተገለጸ

የፓን አፍሪካ አየር ንብረት ፍትህ ጥምረት ከዓለም ጤና ድርጅት ፣ አፍሪካ ጤና እና ጥናት ፋውንዴሽን፣ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና  ሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳቶች ዙሪያ በአዲስ አበባ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል፡፡ በዚህ መድረክ ላይ የአየር ንብረት ለውጥ ባለሙያዎች፣ የጤና ባለሙያዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና የተለያዩ ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል፡፡ የፓን አፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ፍትህ ጥምረት ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሚቲካ ምዌንዳ በመድረኩ ላይ እንዳሉት የአየር ንብረት ለውጥ ዜጎችን ለተደራራቢ የጤና ችግሮች እየዳረገ ነው ብለዋል፡፡ የአየር ንብረት ለውጥ የሰው ልጆች ለአየር ወለድ፣ ውሃ ወለድ፣ ለምግብ እጥረት እና ሌሎች የጤና ችግሮች እየዳረገ ነው ያሉት ስራ አስፈጻሚው ጉዳቱን ለመቀነስ የተቀናጀ ስራ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡…
Read More
ኢትዮጵያ ከዓለም ከአይኤምኤፍ ጋር ያላትን ልዩነት መፍታት እንዳልቻለች ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከዓለም ከአይኤምኤፍ ጋር ያላትን ልዩነት መፍታት እንዳልቻለች ተገለጸ

የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በዋሸንግተን በተካሄደው የዓለም የገንዘብ ድርጅት ጉባኤ ላይ እየተካፈለች ትገኛለች፡፡ በዚህ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ እና የብሔራዊ ባንክ ዋና ገዢ ማሞ ምህረቱ እንዲሁም ሌሎች ባለስልጣናትም እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ ኢትዮጵያ ከዓለም የገንዘብ ድርጅት 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት የጠየቀች ሲሆን ተቋሙ ግን ብድር ለኢትዮጵያ ከመስጠቱ በፊት የተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጧል፡፡ ከተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎች መካከል ኢትዮጵያ የብሯን የመግዛት አቅም እንድታዳክም የሚለው ሲሆን ይህ ጉዳይ እስካሁን አጨቃጫቂ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ ኢትዮጵያ እና የዓለም ገንዘብ ድርጅት ድርድር ሲያደርጉ ከአንድ ዓመት በላይ የሆናቸው ሲሆን በየጊዜው ሳይስማሙ በመለያየት ላይ ናቸው፡፡ ከአንድ ወር በፊት የዓለም ገንዘብ ድርጅት ከፍተኛ ባለሙያዎች ወደ አዲ አበባ መጥተው…
Read More
ከአላማጣ እና አካባቢው 29 ሺህ ህዝብ መፈናቀሉ ተገለጸ፡፡

ከአላማጣ እና አካባቢው 29 ሺህ ህዝብ መፈናቀሉ ተገለጸ፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 29 ሺህ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡ እንደ ድርጅቱ ሪፖርት ከሆነ ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ ሰሜን ወሎ እና ሰቆጣ ከተማ በሚገኙ መጠለያዎች ላይ እንደተጠለሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የገለጸው ድርጅቱ ለተፈናቃዮች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ህይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡ አሁን ላይ ከለጋሽ ተቋማት እና ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እየተሟጠጠ በመሆኑ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ ለተፈናቃዮቹ መጠለያ፣ የሕክምና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባል…
Read More
በኢትዮጵያ 9 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ 9 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ በፀጥታ ችግር ምክንያት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች 8.8 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። በኢትዮጵያ በግጭት ምክንያት 8,977 ትምህርት ቤቶች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 6,483 ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆናቸውን በሚኒስቴሩ 'ትምህርትን በአደጋ ማስቀጠል' ባለሙያ ንጋቱ አበበ ተናግረዋል፡፡ ሚኒስቴሩ እና የክልል ትምህርት ቢሮዎች በጋራ በመሆን የመማር ማስተማር ሒደቱን ለማስቀጠል ጥረት ቢያደርጉም፤ አሁንም በተለያዩ ቦታዎች በቀጠሉት ግጭቶች ምክንያት ችግሩን ለመፍታት አስቸጋሪ እንደሆነ ባለሙያው ጠቁመዋል፡፡ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የመማር ማስተማር ሒደቱን ለማስቀጠል የሚጠበቅባቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉም ባለሙያው ጥሪ አቅርበዋል። ከሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ጦርነት እየተካሄደ ባለበት የአማራ ክልል ውስጥ 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን…
Read More
የባህር ሀይል ወታደሮች በአማራ ክልል ውጊያ እየተሳተፉ መሆኑን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ገለጸ

የባህር ሀይል ወታደሮች በአማራ ክልል ውጊያ እየተሳተፉ መሆኑን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ገለጸ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ እንዳለው "የኢትዮጵያ ባህር ሀይል ማሪን ኮማንዶ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ተሰማርቷል" ብሏል። ተቋሙ የባህር ሀይል ዋና አዛዥ ተወካይ ሬር አድሚራል ናስር አባዲጋን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው "ጽንፈኛ" ባላቸው ቡድን አባላት ላይ እርምጃ እንደወሰደ ገልጿል። የኢትዮጵያ ባህር ሀይል ማሪን ኮማንዶዎች በሰሜን ሸዋ ዞን ባሉ ወረዳዎች እንደተሰማሩ እና ግዳጃቸውን እየተወጡ እንደሆነም አዛዡ መናገራቸው ተገልጿል። እንዲሁም ማሪን ኮማንዶ በመርከብ ላይ በባህር ከሚሰጠው ተልዕኮ በተጨማሪ በማንኛውም ጊዜ ግዳጁን የሚወጣ ሀይል እንደሆነም ሬር አድሚራል ናስር አባድጋ ተናግረዋል ተብሏል። ማሪን ኮማንዶ ከአማራ ክልል የጸጥታ ሀይሎች ጋር በመሆን በወሰዳቸው እርምጃዎች የክልሉ ሰላም እየተሻሻለ መምጣቱንም በዚሁ ዘገባ ላይ ተጠቅሷል። የፌደራል መንግሥት…
Read More
ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር በተፈራረመችው የወደብ ስምምነት ዙሪያ የአቋም ለውጥ እንዳላደረገች አስታወቀች

ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር በተፈራረመችው የወደብ ስምምነት ዙሪያ የአቋም ለውጥ እንዳላደረገች አስታወቀች

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ነብዩ ተድላ በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው ካነሷቸው ጉዳዮች መካከል የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ጉዳይ፣ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ስለተደረገው የወደብ መግባቢያ ስምምነት እና ሌሎቹም ተጠቃሽ ናቸው። አቶ ነብዩ እንዳሉት የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ጉዳይ በድንበር አካባቢ ያሉ ማህበረሰብ ክፍሎችን ባሳተፈ መንገድ በሁለቱ ሀገራት በሚዋቀር ኮሚቴ ይፈታል ብለዋል። የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ በኤርትራ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው ድንበር ሊቀየር በማይችል ኹኔታ ለመጨረሻ ጊዜ ተሠምሯል ማለቱ አይዘነጋም። የኤርትራ ጦር በርካታ የኢትዮጵያ አካባቢዎችን እንደተቆጣጠር እና አካባቢዎቹን ወደ ኤርትራ ማካለሉን እንዴት ኢትዮጵያ እንዴት ታየዋለች? በሚል ለቃል አቀባዩ ለቀረበላቸው ጥያቄም "ጥያቄው…
Read More