27
Apr
የተባረሩት የውጭ ሀገራት ዜጎች ህጋዊ የነዋሪነት ፈቃድ የሌላቸው እንደሆኑ የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡ የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የበጀት ዓመቱን የዘጠኝ ወራት ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበዋል፡፡ ዳይሬክተሯ በዚህ ጊዜ እንዳሉት በሐሰተኛ የመኖሪያ ፍቃድ በአገር ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ከ18 ሺህ በላይ የውጭ አገር ዜጎችን ከአገር እንዲባረሩ ተደርጓል፡፡ ከአገር ከተባረሩት የውጭ ሀገራት ዜጎች መካከል የተወሰኑት ሐሰተኛ የመኖሪያ ፍቃድ አዘጋጅተው በገንዘብ ሲሸጡ የነበሩ እንደሚገኙበት ተቋሙ አስታውቋል፡፡ በኢንቨስትመንት ፍቃድ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የውጭ ዜጎች ለበርካታ ዓመታት በሕገወጥ ሥራዎች ላይ ተሳታፊ ኾነው እንደተገኙም ዳይሬክተሯ በሪፖርታቸው ላይ ጠቅሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ከዚህ በፊት በርካታ የውጭ ሀገር ዜጎች ሀሰተኛ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ፣…