የተጣራ መረጃ

በኢትዮጵያ የወንዴ የዘር ፍሬ መለገስ እንደማይቻል ተገለጸ

በኢትዮጵያ የወንዴ የዘር ፍሬ መለገስ እንደማይቻል ተገለጸ

ከሰሞኑ በትግራይ ክልል ወንዶች የዘር ፍሬያቸውን ሴቶች ደግሞ እንቁላላቸውን መለገስ እንደሚቻል የሚያሳይ ዘገባ መሰራቱ ይታወሳል፡፡ ቢቢሲ አማርኛ እንደዘገበው ከሆነ መሰረቱን በትግራይ ክልል መዲና መቀሌ ከተማ ያደረገ አንድ የህክምና ተቋም የወንድ ዘር ፍሬያቸውን ለሚለግሱ 10 ሺህ ብር እንዲሁም እንቁላላቸውን ለሚለግሱ ሴቶች ደግሞ 30 ሺህ ብር እንደሚከፍል አስታውቋል፡፡ ይህ የህክምና ተቋም ልጅ መውለድ ያልቻሉ ሰዎችን ጥያቄ መመለስ የሚያስችል ህክምና መጀመሩን እና ለዚህም የተለያዩ መስፈርቶችን አስቀምቷል፡፡ የጤና ሚኒስቴርን በጉዳዩ ዙሪያ እንዳለው ኢትዮጵያ ከበጎ ፈቃደኞች በተለገሱ የዘር ፍሬዎች አልያም እንቁላል ልጅ እንዲወለዱ የሚፈቅድ ህግ እንደሌላት አስታውቋል፡፡ በሚኒስቴሩ የጤና እና ጤና ነክ ተቋማት እና ባለሙያዎች ቁጥጥር ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ እንዳልካቸው ጸዳል ለአልዐይን እንዳሉት ኢትዮጵያ…
Read More
የአፍሪካ ልማት ባንክ ከኢትዮጵያ ያስወጣቸውን ሰራተኞች እንደሚመልስ ገለጸ

የአፍሪካ ልማት ባንክ ከኢትዮጵያ ያስወጣቸውን ሰራተኞች እንደሚመልስ ገለጸ

የአፍሪካ ልማት ባንክ ከሁለት ወር በፊት በአዲስ አበባ ያሉ ሁለት የባንኩ ሰራተኞች በኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ድብደባ፣ እስር እና እንግልት እንደደረሰባቸው አስታውቆ ነበር። ባንኩ እንዳለው ሁለት ሰራተኞቹ የቬና የዲልሎማሲ ጥበቃ ስምምነትን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሮ አስተናጋጅ ሀገራት ስምምነትን የጣሰ ክስተት በኢትዮጵያ መፈጸሙንም ገልጿል። የተፈጠረውን ክስተት ለኢትዮጵያ መንግሥት በይፋ ማመልከቱን የሚገልጸው የአፍሪካ ልማት ባንክ ጉዳዩ መፈጸም እንደሌለበት፣ ህግ መጣሱን እና ጉዳዩ ተመርምሮ እርምጃ እንደሚወሰድ በኢትዮጵያ በኩል ቃል ተገብቶልኛል ሲልም በወቅቱ አስታውቆ ነበር፡፡ ባንኩ አሁን ላይ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል በገባው መሰረት በአጥፊዎች ላይ እርምጃ እንዳልወሰደ እና ጉዳዩ ስለመመርመሩ መረጃ እንዳልሰጠው ገልጿል፡፡ ይህን ተከትሎም ባንኩ የኢትዮጵያ ቢሮውን ሊዘጋ እና…
Read More
በኢትዮጵያ ከ20 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች በሐሰተኛ ሰነዶች እንደሚኖሩ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከ20 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች በሐሰተኛ ሰነዶች እንደሚኖሩ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት እንዳስታወቀው የውጭ ሀገር ዜጎች ሀሰተኛ ሰነዶችን ተጠቅመው ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸውን ደርሼበታለሁ ብሏል፡፡ የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በሰጡት መግለጫ በርካታ የውጭ ሀገር ዜጎች ሀሰተኛ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ሀሰተኛ ጊዚያዊ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ሀሰተኛ ፓስፖርት፣ ሀሰተኛ ቪዛ እና ሀሰተኛ ሰነድ አዘጋጅተው በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እየኖሩ ይገኛል ብለዋል። በተደረገው የማጣራት ስራ ከ18 ሺህ በላይ ሀሰተኛ ጊዚያዊ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ከ1 ሺህ 500 በላይ ሀሰተኛ ቪዛ እና ከአንድ ሺህ 800 በላይ የትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያን ያሰሩ ዜጎች በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች መገኘታቸውንም ዳይሬክተሯ ተናግረዋል። በመሆኑም ህገወጥ ሰነድ ያለቸው ዜጎች ከጥር አንድ ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ጥር 30 ቀን 2016 ዓ.ም…
Read More
ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ወደብ በሊዝ መግዛቷን ገለጸች

ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ወደብ በሊዝ መግዛቷን ገለጸች

በቀይ ባህር ላይ ወደብ እንደሚያስፈልጋት ስትገልጽ የቆየችው ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ወደብ በሊዝ መግዛቷን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ እንደ ጽህፈት ቤቱ መግለጫ ከሆነ የባህር በር የምታገኝበትን የመግባቢያ ስምምነት ከሶማሌ ላንድ ጋር ተፈራርማለች፡፡ የባህር በር ሊዝ ስምምነቱን ጠቅላይ ሚኒስትር  ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሌ ላንድ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ እንደተፈራረሙ ተገልጿል። የኢትዮጵያ እና ራስ ገዟ ሶማሊላንድ ስምምነት ኢትዮጵያ የቀይ ባህር በር እንዲኖራት ለያዘችው ጥረት ጥሩ መደላደል ሊፈጥር ይችላልም ተብሏል፡፡ ይሁንና የባህር በር ሊዝ ስምምነቱ ለምን ያህል ጊዜ፣ በምን ያህል ገንዘብ እና የስምምነቱ ዝርዝር መረጃ እስካሁን በማንኛውም ወገን ይፋ አልተደረገም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከወራት በፊት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት…
Read More
መንግስት ብርን የማዳከም ፍላጎት እንደሌለው ገለጸ

መንግስት ብርን የማዳከም ፍላጎት እንደሌለው ገለጸ

ብሔራዊ ባንክ ሪፖርተር ጋዜጣ በሕዳር 23 እትሙ በውጭ ምንዛሬ ተመን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ለማድረግ መታቀዱን በማስመልከት ያወጣው ዘገባ ሃሰተኛ መሆኑን ገልጿል፡፡ የሪፖርተር የአማርኛ ጋዜጣ ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ ተመን ላይ በቅርብ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ ለውጥ ለማድረግ ማቀዱን በማስመልከት ያወጣው ዘገባ ፈጽሞ ሐሰተኛና አሳሳች፣ ከጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ያፈነገጠ ድርጊት መሆኑን ባንኩ አስታውቋል፡፡ ባንኩ ይህን አስመልክቶ  ባወጣው መግለጫ የሪፖርተር የአማርኛ ጋዜጣ በህዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም እትሙ ብሔራዊ ባንክ ባለፈው ሳምንት የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለፓርላማ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ከአንድ የፓርላማ አባል ቀረበ ከተባለ አስተያየት ላይ ተነሥቶ ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ ተመን ላይ…
Read More
የፈረንሳዩ ኩባንያ የኢትዮ ቴሌኮምን ድርሻ ለመግዛት የጀመረውን ጥረት እቅድ ሰረዘ

የፈረንሳዩ ኩባንያ የኢትዮ ቴሌኮምን ድርሻ ለመግዛት የጀመረውን ጥረት እቅድ ሰረዘ

ኦሬንጅ የተሰኘው የፈረንሳይ የቴሌኮም ኩባንያ ከኢትዮቴሌኮም 45 በመቶ አካባቢ ድርሻ ለመግዛት ዕቅድ የነበረው ቢሆንም ኃሳባችንን በፍጥነት ለመተግበር እና ውጤት ለማግኘት የሚያስችል ሁኔታ ባለመኖሩ ራሴን አግልያለሁ ብሏል። ኢትዮጵያ ከመንግስታዊው ኢትዮቴሌኮም እና በቅርቡ ገበያውን ከተቀላቀለው ከሳፋሪኮም በተጨማሪ ሦስተኛ የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ስራ እንዲጀምር ፈቃድ ለመስጠት ገበያውን እየገመገመ የቆየች ሲሆን በቅርቡ የገበያው ሁኔታ የታሰበውን ያህል አመርቂ ባለመሆኑ ሐደቱ ተቋርጧል ማለቷ ይታወሳል። ከዚህ ጎን ለጎን ከኢትዮቴሌኮም ከግማሽ ያነሰ ድርሻ ለመሸጥም እየጣረች ሲሆን ኦሬንጅ ድርሻ ለመግዛት ፍላጎት ካሳዩት ዓለምአቀፍ ግዙፍ ኩባንያዎች መካከል አንዱ ነበር። ኩባንያው ሞባይል ለዎርልድ ላይቭ እንደገለፀው ከ2021 ጀምሮ የነበረውን ፍላጎት አሁን መግታቱን ይፋ አድርጓል። ኦሬንጅ ግሩፕ በጉዳዩ ላይ ትንተና ከሠራ በኋላ “ስትራቴጂያችንን…
Read More
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር ግጭት ውስጥ መግባቷን አመነች

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር ግጭት ውስጥ መግባቷን አመነች

የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥታል። የሚንስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በተለያዩ የዲፕሎማሲ እና ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ ማብራሪያ ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል ከሰሞኑ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ልማት ባንክ መክፈል ያለባትን ብድር ከመክፈል ጋር በተያያዘ አለመግባባት ተፈጥሯል የሚለው ጉዳይ ነው። አለመግባባቱ በኢትዮጵያ ገንዘብ ሚንስቴር እና በአዲስ አበባ ካለው የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮ ጋር መካከል ነው የተባለ ሲሆን በተፈጠረው አለመግባባት ምክንያትም ባንኩ ቢሮውን ዘግቶ ሆዷል የሚል ነበር። በሁለቱ አካላት መካከል የተፈጠረው ግጭት ምንድን ነው? ባንኩስ የኢትዮጵያ ቢሮውን ዘግቶ ወጥቷል? በሚል ለአምባሳደር መለስ ዓለም ጥያቄ ከጋዜጠኞች ቀርቦላቸው ነበር። አምባሳደር መለስ በምላሻቸውም "ከአፍሪካ ልማት ባንክ ኢትዮጵያ…
Read More
ኢትዮጵያ ከእስራኤል ጎን እንድትቆም ተጠየቀች

ኢትዮጵያ ከእስራኤል ጎን እንድትቆም ተጠየቀች

ኢትዮጵያ ከእስራኤል ጎን እንድትቆም በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ ጥሪ አቀረበ የኢትዮጵያ መንግሥት እና ተቋማት፣ በሐማስ የተፈጸመውን ጥቃት እንዲያወግዙ፣ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለልኝ አድማሱ በሰጡት መግለጫ ጠይቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት እስከ አሁን ስለጥቃቱም ይኹን ስለ ግጭቱ በይፋ የሰጠው መግለጫ የለም፡፡ ኾኖም፣ ኢትዮጵያ ገለልተኛ አቋም እንዳላትና ግጭቱ በሰላም እንዲፈታ እንደምትፈልግ፣ በእስራኤል የኢትዮጵያ አምባሳደር፣ ትላንት ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡ ሃማስ በእስራኤል ላይ መጠነ ሰፊ  ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ በሀገሪቱ የሚገኙ ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያዉያን ሰለባ መሆናቸዉን በኢትዮጵያ እስራኤል ኤምባሲ  አስታዉቋል፡፡ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለሊ አደማሱ እንዳሉት በወቅታዊ የጉዳቱን መጠን አሁን ላይ መግለጽ ባይቻልም ከተጎጂዎች መካከል ግን ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያዉያን እንደሚኖሩ ተናግረዋል፡፡ በጥቃቱ ከ1200 በላይ እስራኤላዉያን መሞታቸዉን አምባሳደር አለሊ…
Read More
በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ የታሰሩ ሰዎች ህይወት በተስቦ በሽታ ማለፉ ተረጋገጠ

በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ የታሰሩ ሰዎች ህይወት በተስቦ በሽታ ማለፉ ተረጋገጠ

190 እስረኞች ታመው ህክምና ሲወስዱ ሶስት ሰዎች ደግሞ በጽኑ ህክምና ክትትል ውስጥ መሆነቸውን ኢሰመኮ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ወይም ኢሰመኮ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ አስተዳድር ስር ባለ ሲዳሞ አዋሽ የታሰሩ ሰዎችን አስመልክቶ ያደረገውን ሪፖርት ይፋ አድርጓል። ኮሚሽኑ ነሐሴ 24 እንዲሁም በጳጉሜን 2 እና 3 ቀን 2015 ዓ.ም. በዚህ ማቆያ ማእከል/ቦታ ባደረገው ጉብኝት እንዲሁም፣ በማቆያ ማእከሉ የሚገኙ ሰዎችን እና የአዲስ አበባ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮን ጨምሮ የሚመለከታቸውን የመንግሥት የጸጥታ አካላት በማነጋገር ክትትል አካሂጃለሁ ብሏል። በተጨማሪም የማቆያ ማእከሉ አስተባባሪዎች እና ጥበቃ ሲያደርጉ የነበሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላትን፣ በቦታው የሕክምና አገልግሎት የሚሰጡ የሕክምና ባለሞያዎችን እና ተጨማሪ የሕክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኝ የነበረውን የጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል ኃላፊዎችን እና ባለሞያዎችን በማነጋገር…
Read More
ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን መታሰሩ ተገለጸ

ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን መታሰሩ ተገለጸ

የትርታ ኤፍ  ኤም መስራች ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን በፌደራል ፖሊሶች ተይዞ መወሰዱን ባለቤቱ ገልፃለች። ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን ዛሬ ምሳ ሰዓት ላይ ባልዳራስ ኮንዶሚኒየም ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በፌደራል ፖሊስ አባላት ተይዞ  ሜክሲኮ የቀድሞው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ወደሚገኘው ጊዜያዊ ማቆያ ቦታ መወሰዱን ባለቤቷ ገልፃለች ። ባለቤቱ የታሰረበት ቦታ ሄዳ የጠየቀች ሲሆን በምን ምክንያት እንደታሰረ እንዳላወቀና ለጥያቄም እንዳልቀረበ አሳውቋታል ። ጋዜጠኛ የኋላሸት ትኩረቱን በኪነ ጥበባዊ ጉዳዮች ላይ ያደረገው ኪነ ብስራት የተሰኘ የሬድዮ ሾው ለዓመታት በብስራት ኤፍ ኤም 101.1 በማቅረብ ይታወቃል። ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ጥበቃ ቡድን ወይም ሲፒጂ ከቀናት በፊት ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ የጋዜጠኞች እስር መቀጠሉን እና የታሰሩት እንዲፈቱ ማሳሰቡ ይታወሳል።
Read More