መነሻ ገፅ

አዲስ ስታንዳርድ ሚዲያ ፈቃድ መሰረዙ ተገለጸ

አዲስ ስታንዳርድ ሚዲያ ፈቃድ መሰረዙ ተገለጸ

የኢትዮጵያ  መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን እንዳስታወቀው የአዲስ ስታንዳርድ የበየነ-መረብ መገናኛ ብዙኃን ምዝገባ ምስክር ወረቀት ከየካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ  ተሰርዟል ብሏል፡፡ እንደ ባለስልጣኑ መግለጫ ከሆነ አዲስ ስታንዳርድ የበየነ-መረብ መገናኛ ብዙኃን የሚዲያ ስነ ምግባርን፣ የኢትዮጵያ ሕጎች እና የሀገርንና የሕዝብን ብሔራዊ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥሉ ዘገባዎችን በተደጋጋሚ በማሰራጨት ላይ ይገኛል ሲል አስታውቋል፡፡ በመሆኑም ባለሥልጣኑ ይህንኑ ድርጊት በመመርመር አዲስ ስታንዳርድ የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን እንዲታረም እና ከአጥፊ አካሄዱ እንዲቆጠብ በተደጋጋሚ ምክር ሲሰጥ ቢቆይም ለመታረም ፈቃደኛ ሳይሆን በመቅረቱ ፈቃዲ እንደተሰረዘ ባለስልጣኑ ገልጿል። በተጨማሪም በሚዲያ ዘርፉ ላይ የሙያ ስነምግባር እና የሀገርና የህዝብ ብሔራዊ ጥቅም አክብሮ እንዲሰራ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ እና ማስጠንቀቂያ ቢሰጠውም ለመታረም ፈቃደኛ አልሆነም ያለው…
Read More
ራያ እና ወልቃይት አካባቢ ከትግራይ ክልል ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ተወሰነ

ራያ እና ወልቃይት አካባቢ ከትግራይ ክልል ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ተወሰነ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በአማራ እና ትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ በሚያነሱባቸው አካባቢዎች ምርጫ እንዲካሄው ውስኗል ተብሏል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ የካቲት 16፣ 2018 ባወጣው መግለጫ ከዚህ በፊት በትግራይ ክልል ስር ሆነው ምርጫ ሲካሄድባቸው የነበሩ ምርጫ ክልሎች ከክልሉ መንግስት ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድባቸው መወሰኑን የሚገልጽ ደብዳቤ እንደደረሰው ገልጿል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቻ ይካሄድባቸዋል ተብለው በቦርዱ መግለጫ ላይ የተጠቀሱት ምርጫ ክልሎች ሁመራ፣ አዲረመጽ፣ ኮረምኦፍላ ፣ ጠለምት እና ራያ አላማጣ ምርጫ ክልሎች እንደሆኑም ቦርዱ አስታውቋል፡፡ ቦርዱ አክሎም የክልል ምክር ቤት ምርጫ በአካባቢዎቹ ላይ የተነሳባው የይገባኛል ውዝግብ ጥያቄ በህገ መንግስት ውሳኔ መሰረት ሲፈታ እንደሚካሄድ ቦርዱ አስታውቋል።የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር በበኩሉ…
Read More
ፖሊስ ከሶስት ባንኮች 89 ሚሊዮን ብር ያጭበረበረውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለጸ

ፖሊስ ከሶስት ባንኮች 89 ሚሊዮን ብር ያጭበረበረውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለጸ

በሶስት ባንኮች ላይ የ89 ሚሊዮን ብር ምዝበራ የፈጸመው ቡድን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል። ፖሊስ ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ በሐሰተኛ የባንክ ዋስትና ሰነድ በመጠቀም በገዳ ባንክ፣ በኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል የፈጸሙ ተጠርጣሪዎችን ከነግብረ-አበሮቻቸው በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታውቋል። ተጠርጣሪዎቹ በተቀነባበረ ሴራ በአጠቃላይ ከ89 ሚሊዮን 296 ሺህ ብር በላይ በሀገር ኢኮኖሚ እና በባንኮች ላይ ጉዳት አድርሰዋል ተብሏል። ተጠርጣሪው የጎደር ዋይን ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ ጌታሁን መለስ ሲሆን፣ ከገዳ ባንክ አገምሳ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አብዲሳ ቶሎሳ ጋር በጥቅም በመመሳጠር የቅርንጫፉን ፊርማና ማህተም ለወንጀል ተግባራቸው ሲጠቀሙበት መቆየታቸው ተገልጿል። ዋነኛው ተጠርጣሪ…
Read More
የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስራ አስፈጻሚ የኡጋንዳ አየር መንገድን እንዲመሩ ተሾሙ

የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስራ አስፈጻሚ የኡጋንዳ አየር መንገድን እንዲመሩ ተሾሙ

አቶ ግርማ ዋቄ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬታማ እንዲሆን የአመራርነት ሚናቸውን ካሳረፉ ሰዎች መካከል ዋነኛው ናቸው። የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከለቀቁ በኋላ ወደ ኪጋሊ አምርተው የሩዋንዳ አየር መንገድን በማቋቋም አሁን ላይ በማደግ ላይ ካሉ የአፍሪካ አየር መንገዶች መካከል አንዱ ሆኗል። ሌላኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ኡጋንዳ ኢትዮጵያዊውን የአቪዬሽን መሪ የሆኑት አቶ ግርማ ዋቄን ቀጥራለች። አቶ ግርማ የኡጋንዳ አየር መንገድን በጊዜያዊነት ስራ አስፈጻሚ ሆነው የተሾሙ ሲሆን በተጨማሪም የሀገሪቱን አቪዬሽን አማካሪ ሆነውም እንደሚያገለግሉ የትራንስፖርት ሚንስቴር ገልጿል። የኡጋንዳ አየር መንገድ በ1985 ዓ .ም የተቋቋመ ቢሆንም በኪሳራ ምክንያት በ2009 ተዘግቶ ነበር። ከስድስት ዓመታት በፊት ዳግም የተቋቋመው የኡጋንዳ አየር መንገድ በኪሳራ ላይ ካሉ የአፍሪካ አየር መንገዶች መካከል አንዱ ነበር።…
Read More
የአፍሪካ-ጣሊያን መሪዎች ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

የአፍሪካ-ጣሊያን መሪዎች ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

ሁለተኛው የአፍሪካ-ጣሊያን መሪዎች ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ ከጣሊያን ዋና ከተማ ሮም ውጭ በአፍሪካ ምድር በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። ይህ ጉባኤ የጣሊያንና አፍሪካ ግንኙነት በአህጉራዊና በዓለም አቀፋዊ ትብብሮች ይበልጥ እንዲጠናከር የሚያደርግ ሲሆን፣ ኢትዮጵያም አህጉሪቱን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማስተሳሰር ያላትን የዲፕሎማሲ አቅም በተግባር ያሳየችበት መድረክ ሆኗል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች እና የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን ጨምሮ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ታሪካዊው ስብሰባ በፈረንጆቹ 2024 በሮም የቀረበውን የጣሊያን "የማቲ ዕቅድ" (Mattei Plan) አፈጻጸም የሚገመግም ሲሆን፣ በተለይም በሀይል ልማት፣ በግብርና፣ በትምህርት እና በጤና ዘርፎች ላይ ያተኮረ ሰፊ ምክክር ያደርጋል። የመንግሥት ኮምኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ደኤታ አቶ ተስፋሁን…
Read More
ዶክተር ዮሀንስ አያሌው የጸደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

ዶክተር ዮሀንስ አያሌው የጸደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

የቀድሞው ልማት ባንክ እና አማራ ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሀንስ አያሌው በኪሳራ ላይ ላለው ጸደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ተደርገው ተሾመዋል። የአማራ ብድርና ቁጠባ ድርጅት በሚል ሲጠራ የነበረው በኋላም ጸደይ ባንክ በሚል ስያሜ የኢትዮጵያን የባንክ ቢዝነስ የተቀላቀለው ጸደይ ባንክ በኪሳራ ላይ ይገኛል። ባንኩ በ2024/25 በጀት ዓመት ብቻ የሁለት ቢሊዮን ብር ኪሳራ እንደደረሰበት ከአንድ ወር በፊት ዓመታዊ ጉባኤውን ሲያካሂድ ገልጿል። ይህን ተከትሎም ዶክተር ዮሀንስ አያሌው የባንኩ አዲስ ፕሬዝዳንት ሆነው እንደተሾሙለት ባንኩ ከደቂቃዎች በፊት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ አስታውቋል። በኪሳራ ላይ ያሉ የገንዘብ ድርጅቶችን በመታደግ የሚታወቁት ዶክተር ዮሀንስ ከዚህ በፊት ልማት ባንክን እንዲሁም የአማራ ባንክን ከኪሳራ ወደ ትርፍ መመለሳቸው ይገለጿል። ላለፉት ዓመታት ጸደይ ባንክን በፕሬዝዳንትነት…
Read More
የ”ዲጂታል ይዘት ስርቆት” እና ችላ የመባሉ አስጊ ተፅዕኖዎች

የ”ዲጂታል ይዘት ስርቆት” እና ችላ የመባሉ አስጊ ተፅዕኖዎች

በደመቀ ከበደ በኢትዮጵያ የፈጠራና የባህል ኢኮኖሚ ላይ የተጋረጠው የ"ዲጂታል ይዘት ስርቆት" እና ችላ የመባሉ አስጊ ተፅዕኖዎች በአዲስ አበባ እምብርት ውስጥ ወጣት የሙዚቃ አቀናባሪዎች የሙዚቃ ገበያውን ዓለም ሊያነቃንቁ የሚችሉ ቅኝቶችን ሲያመርቱ ይውላሉ። ፊልም ሰሪዎቻችን የኢትዮጵያን ማንነትና ነፍስ የሚዘክሩ ታሪኮችን በካሜራቸው ይስላሉ። በከተማዋ በሚገኙ የሲኒማቶግራፊ ስቱዲዮዎች እና የዲጂታል አማራጮች ውስጥም የሀገር በቀል ታሪኮችን ከዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃ ጋር ያዋሃዱ የሚዲያ ስራዎች ለመፍጠር እየታተሩ ነው። በሽሮ ሜዳ የእጅ ባለሙያዎችም የዘመናት ቅርስ የሆነውን የጋሞን ጥበብና ድንቅ ድሮችን ወደ ዘመናዊ ገበያ እያመጡ ነው። በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ የሰርከስ ተሳታፊዎችና የውዝዋዜ ቡድኖች ጥንታዊ ትውፊትን ከዘመናዊ ፈጠራ ጋር አዋህደው ልምምዳቸውን ያደርጋሉ። ከሶፍትዌር አልሚዎችና ዲዛይነሮች እስከ ጸሐፍትና የሶሻል…
Read More
የኤርትራ ጦር ከአማጺ ጋር በመተባበር ወደ ኢትዮጵያ ግዛት መግባቱ ተገለጸ

የኤርትራ ጦር ከአማጺ ጋር በመተባበር ወደ ኢትዮጵያ ግዛት መግባቱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር እንዳስታወቀው ኤርትራ ባለፉት ቀናት አዲስ ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን አስታውቋልል። ሚንስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ለኤርትራ አቻቸው ኦስማን ሳሌህ በጻፉት ደብዳቤ የኤርትራ ጦር ከአማጺያን ጋር በመተባበር በሰሜን ምስራቅ በኩል ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን አስታውቋል። ወደ ኢትዮጵያ የገቡት የኤርትራ ወታደሮችም ከአማጺያን ጋር በመቀናጀት ወታደራዊ እንቅስቃሴ እያደረጉ እንደሆኑም ተገልጿል። በመሆኑም እነዚህ የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ባስቸኳይ እንዲወጡም ጠይቋል። የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ በደብዳቤው ላይ ከኤርትራ ጋር የገቡበትን አለመግባባት በዲፕሎማሲ ለመፍታት ዝግጁ እንደሆነም ገልጿል። ሚንስትሩ አክለውም በተለይ ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት እና የአሰብ ወደብን ለማግኘት ያቀረበቻቸውን ጥያቄዎች ጨምሮ ሌሎች ፍላጎቶችን ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ ለመወያየት ዝግጁ እንደሆነችም ተጠቅሷል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ባሳለፍነው…
Read More
የፕሪቶሪያ ስምምነት አፈጻጸምን የሚከታተለው የባለሙያዎች ቡድን መቐለ ገባ

የፕሪቶሪያ ስምምነት አፈጻጸምን የሚከታተለው የባለሙያዎች ቡድን መቐለ ገባ

ለሁለት ዓመት የዘለቀውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት እንዲቆም ምክንያት የሆነው የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት አፈጻጸም የሚከታተል የባለሙያዎች ቡድን ትግራይ ክልል መቐለ መግባቱ ተገልጿል። ስምምነቱ እንዲፈረም ያደራደረው የአፍሪካ ህብረት የባለሙያዎችን ቡድን ያቋቋመው ከኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ናይጀሪያ እና አልጀሪያ የተውጣጡ ናቸው። ይህ የባለሙያዎች ቡድን በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ታጣቂዎች ትጥቅ መፍታታቸውን፣ መሰረታዊ አገልግሎቶች መቀጠላቸውን፣ በጦርነቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀድሞ ቀዬአቸው መመለሳቸውን የመከታተል ሀላፊነት ተሰጥቶታል። ዛሬ መቐለ መድረሱ የተገለጸው ይህ የባለሙያዎች ቡድን መቀመጫውን መቐለ በማድረግ የስምምነቱን አፈጻጸም ሲከታተል የቆየ ሲሆን ላለፉት ወራት በዕረፍት ላይ መቆየቱን የትግራይ ሰላምና ደህንነት ቢሮ አስታውቋል። ይህ የባለሙያዎች ቡድን ከአስተዳድራዊ ዕረፍት በኋላ ወደ መቐለ የተመለሰው በአማራ እና ትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ…
Read More
በኒጀር የሚገኙ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖች የሽብር ጥቃት ደረሰባቸው

በኒጀር የሚገኙ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖች የሽብር ጥቃት ደረሰባቸው

አየር መንገዱ እንደገለጸው ባለፈው ሃሙስ ጥር 21 ቀን 2018 ዓ.ም ለሊት በኒጀር ዋና ከተማ ኒያሚ አውሮፕላን ማረፊያ በደረሰው ጥቃት ሁለት የአስካይ አየር መንገድ ቦይንግ 737 አውሮፕላኖች ላይ መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ብሏል። ሁለቱ አውሮፕላኖች የኢትዮጵያ አየር መንገድ አጋር የሆነው የአስካይ  አየር መንገድ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አማካኝነት ከአውሮፕላን አከራዮች የተከራያቸው እና በኢትዮጵያ ሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን የተመዘገቡ ናቸው ተብሏል። በአውሮፕላኖቹ ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመገምገም የተላከው የቴክኒክ ቡድን ጉዳቱ መጠነኛ መሆኑን እንዳረጋገጠ የገለጸው አየር መንገዱ አውሮፕላኖቹ ተጠግነው በቅርቡ ወደ አገልግሎት እንደሚገቡ አስታውቋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሎሜ (ቶጎ) መቀመጫውን ካደረገው አስካይ አየር መንገድ ጋር የ40% የባለቤትነት ድርሻና የቴክኒክ አጋርነት አለው። የአስካይ አውሮፕላኖች የሽብር ጥቃት ኢላማ…
Read More