መነሻ ገፅ

ኢትዮጵያ የ6 መርከቦች ግዥ መፈፅሟ ተገለ

ኢትዮጵያ የ6 መርከቦች ግዥ መፈፅሟ ተገለ

የመርከቦቹ መገዛት በባህር ትራንስፖርት ላይ ያላትን አቅም የበለጠ ያሳድጋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የሚያስተዳድራቸው 10 መርከቦች ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ የማዳበሪያ ምርትን ጨምሮ የሚበዛውን ምርት የምታጓጉዘው እነዚህኑ መርከቦች ተጠቅማ ነው። አሁን ደግሞ የተጨማሪ ስድስት ትላልቅ መርከቦች ግዢ ተፈፅሞ ኢትዮጵያ መርከቦቹን ዘንድሮ እንደምትረከብ ተነግሯል። ይህም ኢትዮጵያ በውሃ ትራንስፖርት ላይ ያላትን አቅም የሚያሳድግ ነው ተብሏል። ከስድስቱ መርከቦች ሁለቱ እስከ 62,000 ቶን የመጫን አቅም ያላቸው እንደሆኑም ተነግሯል። ኢትዮጵያ አሁን ካሏት አስር መርከቦች አባይ ሁለት በመባል የምትጠራው እስከ 63,000 ቶን የመጫን አቅም እንዳላት ይነገራል። ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያ ወደ ሀገር ውስጥ ካስገባችው 1.9 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የማዳበሪያ ምርት አብዛኛው ተጓጉዞ ጅቡቲ ወደብ የደረሰው በራሷ መርከቦች…
Read More
የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ የብድር እዳ ክምችት 2.5 ትሪሊዮን ብር ደረሰ

የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ የብድር እዳ ክምችት 2.5 ትሪሊዮን ብር ደረሰ

የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ የብድር ክምችት 2.5 ትሪሊዮን ብር መድረሱን፣ ከዚህም ውስጥ የግምጃ ቤት ቦንድ ግዥ ከፍተኛ ድርሻ ይይዛል ተብሏል፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴር በዕዳ አስተዳደር ክፍል በኩል ያዘጋጀውን ወርኃዊ የዕዳ ማስታወቂያ የነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም. ሪፖርት፣ የመንግሥት አገራዊ ብድር ዝርዝር መረጃ ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህም መንግሥት እ.ኤ.አ. ከጁን 30 ቀን 2025 ጀምሮ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ብድር 2.5 ትሪሊዮን ብር መድረሱን እንዳስታወቀ የሪፖርተር ዘገባ ያሳያል፡፡ ከአገር ውስጥ ብድር ድርሻ 80 በመቶ የሚይዘው በረዥም ጊዜ የሚከፈል የግምጃ ቤት ሰነድ እ.ኤ.አ. በኦገስት 2025 የግምጃ ቤት ሰነድ ግዥ ከፍተኛ እንደነበርና ከአጠቃላይ ክምችት አንፃርም 39 በመቶ እንደሚሸፍን ገልጿል፡፡ እስከ ኦገስት 2025 ድረስ ባለው የመንግሥት አጠቃላይ የአገር ውስጥ…
Read More
ጊቭ ዋተር ከ200 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሀ ማቅረቡን ገለጸ

ጊቭ ዋተር ከ200 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሀ ማቅረቡን ገለጸ

ሀገር በቀሉ ጊቭ ዋተር የተሰኘው ድርጅት ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ ሃብት በማሰባሰብ ከ200 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያንን ንጹህ የመጠጥ ውሀ ተጠቃሚ ማድረጉን አስታውቋል። የድርጅቱ ሀብት ማሰባሰብ ኃላፊ አቶ ከማል አህመድ እንዳሉት ድርጅቱ ከተመሰረተበት 2010 ጀምሮ ላለፉት 15 ዓመታት በንፁህ የመጠጥ ውሃ እጦት ክፉኛ እየተፈተኑ ላሉ የገጠር ማህበረሰብ አካባቢዎች የተለያዩ እና በርካታ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ህበረተሰቡን ተጠቃሚ መደረጉን ገልፀዋል። ጊቭ ዎተር በ15 ዓመታት የልማት ጉዞው የሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎቶች መካከል አንዱ በሆነው የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ዘርፍ የገጠሩን ማህበረሰብ የትኩረት ማዕከሉ በማድረግ ሲንቀሳቀስ ቆይቷልም ብለዋል። ድርጅቱ በተጠቀሱት ዓመታት ውስጥ ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ ሃብት በማሰባሰብ በ 7 ክልሎች በተለይም በአፋር፣ ሶማሌ፣…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓመታዊ ገቢውን ወደ 25 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያሳድግ ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓመታዊ ገቢውን ወደ 25 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያሳድግ ገለጸ

አየር መንገዱ ከ10 ዓመት በኋላ ዓመታዊ ገቢውን 25 ቢሊዮን ዶላር የማድረስ እቅድ እንዳለው አስታውቋል። ከ10 ዓመት በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገቢ 25 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ገለጹ፡፡ አቶ መስፍን እንደገለጹት አየር መንገዱ እ.ኤ.አ በ2035 ላይ 209 ዓለም አቀፍ እና 31 የሀገር ውስጥ መዳረሻዎች፣ 271 አውሮፕላኖች እንደሚኖሩትም ጠቅሰዋል፡፡ አየር መንገዱ 67 ነጥበ 2 ሚሊዮን መንገደኞችንም በማጓጓዝ ከ10 ዓመት በኋላ ገቢውንም 25 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ መታቀዱን ገልጸዋል፡፡ ለዚህም አዳዲስ መዳረሻዎችን በማስፋት ትስስሩን ይበልጥ ማጠናከር እና አዳዲስ መዳረሻዎችን መክፈት የሚያስፈልግ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ለዚህም አሁን በረራ ከሚደረግባቸው አምስቱ ክፍለ አኅጉሮች ተጨማሪ አውስትራሊያንም የሚጨመር መሆኑን…
Read More
ኢትዮጲያ ከ34 አመት በኋላ ያለ ወርቅ ሻምፒወናዉን አጠናቀቀች

ኢትዮጲያ ከ34 አመት በኋላ ያለ ወርቅ ሻምፒወናዉን አጠናቀቀች

በጃፖን ቶኪዮ አስተናጋጅነት ሲካሄድ  የቆየዉ  የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጲያ በታሪክ ለሁለተኛ ጊዜ ያለ ምንም ወርቅ አጠናቃለች። ኢትዮጲያ በዚህ መድረክ በታሪክ ከ34 አመት በኅላ አንድም ወርቅ ሳታገኝ ያጠናቀቀችበት የአለም ሻምፒዮና ሆኖ ተመዝግቧል። በውድድሩ የመጨረሻ ቀናት በተደረገዉ የ5000 ሜትር የወንዶች ፍፃሜ ዉድድር ምን አልባት ወርቅ ይገኝበታል ተብሎ ቢጠበቅም ኢትዮጵያ ሜዳሊያ  ዉስጥ መግባት ሳትችል ቀርታለች። ኢትዮጲያን የወከሉት አትሌት ሀጎስ ገብረ ሂወት እና አትሌት ቢኒያም መሀሪ ዉድድራቸዉን 5ኛ እና 13ኛ  ደረጃን ይዘዉ አጠናቀዋል። ኢትዮጲያ እስካሁን ባደረገቻቸዉ ስምንት የፍፃሜ ዉድድሮች ሁለት ብር እና ሁለት ነሀስ ስታገኝ በድምሩ አራት ሜዳሊያዎችን ብቻ ሰብስባ በታሪኳ በእጅጉ ደካማ የሆነዉን የቶኪዮ አለም ሻምፒዮና ቆይታዋን ደምድማለች። አሜሪካ በውድድሩ 16 የወርቅ ሜዳሊያ…
Read More
አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ብልጽግና ፓርቲን ለማሸነፍ ህብረት ፈጠሩ

አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ብልጽግና ፓርቲን ለማሸነፍ ህብረት ፈጠሩ

ፓርቲዎቹ "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" የተሰኘ የቅንጅት ፖርቲ መመስረታቸውን ገልጸዋል። ላለፉት ሥስት ዓመታት በትብብር በጋራ ሲሠሩ የቆዩት አምስት የፖለቲካ ድርጅቶች ቅንጅት መመሥረታቸውን በዛሬው ዕለት አስታውቀዋል። የቅንጅቱ ስያሜም "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" መሆኑን በዛሬው የመስራች ጉባኤ ላይ ተገልጿል። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ እናት ፖርቲ ፣የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፖርቲ (ኢሕአፓ)፣ አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ እና አማራ ግዮናዊ ንቅናቄ ናቸው ቅንጅት መመሥረታቸውን አስታውቀዋል። ቅንጅቱንም እንዲመሩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዝዳንት አቶ አብርሀም ጌጡ ተመርጠዋል። "ለእናት ፖርቲ ትልቅ ቀን ነው" ያሉት የፖርቲው ፕሬዝዳንት ሰይፈስላሴ አያሌው (ዶ/ር)፤ "ኢትዮጵያ 50 ዓመታት የተበታተነ የፖለቲካ ጎራ መከራ እየወረደበት ላለው ፖለቲካ መፍትሄ የሚሰጥ ቅንጅት ነው" ሲሉ ተናግረዋል። በተናጥል የሚመጣ…
Read More
ከተሽከርካሪዎች የሚወጣ በካይ ጋዝ የሚቆጣጠር መመሪያ ተዘጋጀ

ከተሽከርካሪዎች የሚወጣ በካይ ጋዝ የሚቆጣጠር መመሪያ ተዘጋጀ

‎በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢኒስቲትዩት የተዘጋጀው፤ ከተሽከርካሪዎች የሚወጣን ጎጂ የካይ ጋዝ ልቀት ለመቆጣጠር የሚያገለግለው አስገዳጅ መመሪያ ከመስከረም 30 ቀን 2018 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል። ዋነኛ ዓላማው የትራንስፖርት ዘርፉ ለበካይ ጋዝ ልቀት የሁለት ሦስተኛ ድርሻ ያለው በመሆኑ በጎጂ በካይ ጋዞች ምክንያት የሚከሰትን የአየር ብክለት መቀነስ ሲሆን፤ አዲሱ መመሪያ ሙሉ ለሙሉ ሲተገበር ተሽከርካሪዎች ወደ አየር የሚለቁትን የበካይ ጋዝ መጠን የሚቆጣጠር መሳሪያ እንዲገጥሙ ይገደዳሉ ተብሏል። የተቋሙ የትራንስፖርት ዘርፍ የአየር ንብረት ክትትል እና ቁጥጥር ቡድን መሪ አቶ ግርማ ሳሙኤል፤ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ መመሪያው ከጸደቀበት መጋቢት 2017 ጀምሮ ውይይቶች ሲካሄዱበት እንደነበርም ተናግረዋል። በዚህም አስገዳጅ መመሪያው ከጸደቀ በኋላ ከታክሲ ማኅበራት፣ ከክልል ከተማ አስተዳደሮች…
Read More
ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በመዝጋት ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር ተባለች

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በመዝጋት ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር ተባለች

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በተደጋጋሚ በመዝጋትና የኢንተርኔትን ነጸነት በመገደብ ከአፍሪካ በአንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን በብሉምስበሪ አሳታሚ ላይ የታተመ አንድ የጥናት መጽሐፍ አመላከተ። “የኢንተርኔት መዘጋት በአፍሪካ” በሚል ርእስ በፊሊሽያ አንቶኒዮ እና ቶኒ ሮበርትስ የተጠናውና መቀመጫውን በብሪታንያ ባደረገው ብሉምስበሪ አሳታሚ ድርጅት ላይ በመጸሐፍ መልክ ታትሞ የወጣው ጥናት በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2016 እስከ 2024 በአህጉረ አፍሪካ በሀገራት የተፈጸመውን የኢንተርኔት መዘጋት ገምግሟል። በዚህም በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2016 እስከ 2024 ባሉት በለፉት ዘጠኝ ዓመታት 193 የኢንተርኔት መዘጋት በአፍሪካ አህጉር መመዝገቡን ገልጿል። በተጠቀሱት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ በተፈጸሙ የኢንተርኔት መዘጋት ድግግሞሽ መጠኖች ሀገራትን በደረጃ ያስቀመጠው ጥናቱ ኢትዮጵያን በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ሰላሳ ጊዜ ኢንትርኔት የዘጋች በሚል ከ55ቱ የአፍሪካ ሀገራት በአንደኛ ደረጃ አስቀምጧታል።…
Read More
ጣልያን በኢትዮጵያ የባቡር መስመር ግንባታ ለማድረግ ተስማማች

ጣልያን በኢትዮጵያ የባቡር መስመር ግንባታ ለማድረግ ተስማማች

የጣልያን ባቡር ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል። መንግሥት በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ምክንያት የተቋረጠውን የአዋሽ- ኮምቦልቻ እና ሐራ ገበያ የባቡር መስመርን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ቁርጠኝነት አለኝ ብሏል። የአዋሽ- ኮምቦልቻ እና ሐራ ገበያ  የባቡር መስመርን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ የመንግስት ቁርጠኝነት ምኖሩን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታወቀ። የኮርፖሬሽኑ የህግ አገልግሎት ሃላፊ አቶ ካሳሁን ሙላቱ እንደገልፁት ኮርፖሬሽኑ የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎትን ለማጠናከር ከኮይፓ ኢጣሊያ ጋር ስምምነት አድርጓል። ስምምነቱ አዳዲስ የባቡር መስመሮችን መዘርጋትን እንዲሁም እየተገነቡ ያሉ የባቡር መስመሮችን በፍጥነት አጠናቆ ወደ ስራ ማስገባትን የሚያካትት ነው ብለዋል። ከዛም ባለፈ በጋራ ድርጅቶችን ማቋቋም እንዲሁም ትላልቅ ዎርክ ሾፖሽን ማሻሻል ጨምሮ በርካታ ስትራቴጂካዊ ስራዎች የሚሰራበት የጋራ ስምምነት መሆኑን…
Read More
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቹ ከነዓን ማርክነህ የኦማን ክለብን ተቀላቀለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቹ ከነዓን ማርክነህ የኦማን ክለብን ተቀላቀለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወይም (ዋልያዎቹ) የፊት መስመር እና የመሐል ሜዳ ተጫዋች ከንአን ማርክነህ ወደ አዲስ ክለብ ለማምራት መስማማቱ ተገልጿ። ከንአን ማርከነ በአዲሱ የውድድር ዘመን ወደ ኦማን ሊግ በማቅናት አል ሸባብ ክለብ ለመጫወት ከስምምነት መድረሱ ታውቋል። ከብሔራዊ ቡድን ጨዋታ መልስ ወደ ኦማን ያቀናው ከንአን ማርክነህ በትላንትናው ዕለት የህክምና ምርመራውን በተሳካ ሁኔታ አልፏል። ከንአን ከህክምና ምርመራ በኃላ በክለቡ የሚያቆየውን የአንድ አመት ኮንትራት ሲፈራረም ክለቡ በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጎታል። ከንአን ያለፈውን የውድድር ዓመት በሊቢያ ሊግ ስኬታማ ጊዜን ሲያሳልፍ ለአል መዲና እና ሸባብ አል ጋሂር እግር ኳስ ክለቦች መጫወቱ ይታወሳል። ከንአን ማርከነ በሊቢያ ቆይታው በ14 ጨዋታዎች ስድስት ጎሎችን አስቆጥሯል። የከንአን አዲሱ ክለብ አል ሸባብ…
Read More