Blog

የትግራይ እና አማራ ክልል አመራሮች ከሁለት ዓመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ ተገናኙ

የትግራይ እና አማራ ክልል አመራሮች ከሁለት ዓመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ ተገናኙ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ ባህርዳር ያቀኑ ሲሆን ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ይልቃል ከፋለ ጋር ተወያይተዋል፡፡ አቶ ጌታቸው ረዳ እና ልዑካቸው ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ጋር እንዲሁም ከህብረተሰቡ ከተውጣጡ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል። በዚህ ውይይት ላይ አቶ ጌታቸው ረዳ " ዋጋ የማይጠይቅ የሠላም አማራጭ ሳለ በፖለቲከኞች የጠብ ርሃብ ምክንያት በርካታ ጉዳቶች ተከስተዋል " ብለዋል፡፡ "ልዩነቶች ቢኖሩ እንኳን ልዩነቶቹ ከአማራ እና ትግራይ ሕዝብ በታች ናቸው " ያሉ ሲሆን " አሁን የጦርነትን ምዕራፍ ዘግተን የሠላም አማራጮችን የምናይበት ጊዜ ነው " ሲሉም አክለዋል፡፡ "የሁከት እና ግርግር አጀንዳዎች የሚታያቸው ይኖራሉ፤ ነገር ግን ለሕዝብ ካሰብን እና ከሠራን ከሠላም ውጭ የተሻለ…
Read More
ማንችስተር ሲቲ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አነሳ

ማንችስተር ሲቲ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አነሳ

ማንችስተር ሲቲ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አነሳ የጣልያኑ ኢንተርሚላንን እና የእንግሊዙ ማንችስተር ሲቲን ያገናኘው የዘንድሮው የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ በሲቲ አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡ ትናንት ምሽት በቱርክ ኢስታምቡል በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ሮድሪጎ በሁለተኛው አጋማሽ ባስቆጠራት ጎል ማንችስተር ሲቲ ዋንጫውን ማሸነፍ ችሏል፡፡ ማንችስተር ሲቲ በስፔናዊው አሰልጣኝ ፔፔ ጋረዲዮላ አሰልጣኝነት ታግዞ በታሪክ የመጀመሪያውን የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ማንሳት ችሏል፡፡ ማንችሰተር ሲቲ በ2022/23 የውድድር ዓመት ከቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ በተጨማሪ የእንግሊዝን ፕሪሚየር ሊግ እና ኤፍኤካፕ ዋንጫን በማንሳት የሶትዮሽ ዋንጫ መውሰድ ችሏል፡፡ አሰልጣኝ ፔፔ ጋርዲዮላ የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ከባርሴሎና፣ ባየርንሙኒክ እና ማንችስተር ሲቲ ጋር አሸንፏል፡፡ ከቦርሲያ ዶርትሙንድ ማንችስተር ሲቲን ከአንድ ዓመት በፊት የተቀላቀለው ኖረዌያዊው አርሊንግ ሀላንድ በ12 ጎሎች…
Read More
ኢትዮጵያዊያን እና ኬንያዊያን አትሌቶች በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ደምቀው አምሽተዋል

ኢትዮጵያዊያን እና ኬንያዊያን አትሌቶች በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ደምቀው አምሽተዋል

የፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ትናንት ምሽት የተካሄደ ሲሆን ኢትዮጵያዊያን እና ኬንያዊያን አትሌቶች ድል ቀንያቸዋል። ኢትዮጵያዊው ለሜቻ  ግርማ ለ19 አመት ተይዞ የነበረውን የ3 ሺህ መሰናክል ክብረወሰን በመስበር አሸንፏል። ከውድድሩ አስቀድሞ ሪከርዱን እንደሚሰብር ሲናገር የነበረው ለሜቻ በአንድ ወር ውስጥ ሁለተኛ ክብረወሰኑ ሁኖ ተመዝግቧል ። አትሌቱ 7:51:11 በመግባት ሲያሸንፍ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አብርሃም ስሜ8:10:73 የግሉን ምርጥ  ሰዓት በማስመዝገብ 4ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል ። ከቀናት በፊት የ1500 ሜትር የአለም ክብረ ወሰን የሰበረችው ኬኒያዊቷ ፌዝ ኪፕዮገን ለመጀመሪያ ጊዜ በተዋዳደረችበት የ5 ሺህ ሜትር ውድድር ለ8 ዓመት ተይዞ የቆየውን ክብረ ወሰን አሻሽላለች። የዚሁ ርቀት ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው እና በውድድሩ ላይ የተሳተፈችው ለተሰንበት ግደይ ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች። የ5 ኪሎ…
Read More
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዘጠኝ የአውሮፓ ህብረት ፕሮጀክቶችን አሸነፈ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዘጠኝ የአውሮፓ ህብረት ፕሮጀክቶችን አሸነፈ

የአውሮፓ ህብረት ከሚደግፋቸው አስራ ሰባት (17) የምርምር እና የትምህርት ልህቀት ማዕከላት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዘጠኙ አሸናፊ ሆነ። ከዚህም በተጨማሪ ሁለት የፕሮጀክት ፕሮፖዛሎች ውጤት በመጪው ጥቂት ወራት የሚታወቅ ይሆናል ተብሏል። በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን በ2022 November የARUA እና Guild የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች በነበራቸው ስብሰባ በአውሮፓ ህብረት የሚደገፉ የምርምር እና የ ትምህርት ልህቀት ማእከላት ለማቋቋም ወስነው መለያየታቸው ይታወሳል። በዚሁ መሰረት በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በርካታ ፕሮፖዛሎች የቀረቡ ሲሆን ባለፉት ሁለት ተከታታይ ቀናት በቤልጂየም ብራስልስ በተካሄደው ግምገማ መሰረት 17 የልህቀት ማእከል ተመስርተዋል። ከነዚህ የልህቀት ማዕከል ፕሮጀክቶች ውስጥም በዘጠኙ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊ ሆኗል። በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው ፕሮጀክቶቹን በማሸነፉ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዩሮ የሚያገኝ ይሆናል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት…
Read More
በአዲስ አበባ ዙሪያ ባለችው ሱሉልታ ከተማ በርካታ ሰዎች በሸኔ ታጣቂዎች ታገቱ

በአዲስ አበባ ዙሪያ ባለችው ሱሉልታ ከተማ በርካታ ሰዎች በሸኔ ታጣቂዎች ታገቱ

በቅርቡ በተዋቀረው የሸገር ከተማ አስተዳደር ሥር በሚገኘው የሱሉልታ ክፍለ ከተማ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ታፍነው መወሰዳቸው ተገልጿል። ነዋሪዎቹ እንደገለጹት፤ በሱሉልታ ክፍለ ከተማ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በማለት በሚጠራው እና በመንግሥት “ኦነግ ሸኔ” በመባል በአሸባሪነት በተፈረጀው ታጣቂ ቡድን የሚፈጸሙ መሰል ድርጊቶች እየተበራከቱ መምጣታቸውን አስረድተዋል፡፡ በዚህም “ከአንድ ሳምንት በፊት በአንድ ምሽት ብቻ ከሱሉልታ ክፍለ ከተማ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን አካባቢ ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ቁጥራቸው ከ20 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በሸኔ ታጣቂዎች ታፍነው ተወስደዋል” ሲል አዲስ ማለዳ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡ ሰዎቹ በተወሰዱበት ዕለትም ምንም አይነት የመሳሪያ ድምጽ ባለመሰማቱ የጸጥታ አካላት ደርሰው ሊያስጥሏቸው እንዳልዳቻሉ ጠቅሰዋል። ረቡዕ ግንቦት 30 ቀን…
Read More
ኢትዮጵያ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት 50 ቢሊዮን ብር በጀተች

ኢትዮጵያ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት 50 ቢሊዮን ብር በጀተች

በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት የሀገር መከላከያ በጀት ወጪ ከ120 ቢሊዮን ብር በላይ የደረሰ ሲሆን ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛው ሆኖ በታሪክ ተመዝግቧል። ለ2016 በጀት ዓመት ከቀረበው 801 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ የፌዴራል መንግሥት በጀት ውስጥ ለመከላከያ ሚኒስቴር 50 ቢሊዮን ብር ሲመደብ ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የወደሙ ተቋማትና አገልግሎቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ ደግሞ 20 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙ ተገልጿል። በ2015 በጀት ዓመት ውስጥ አጠቃላይ ከተበጀተው የመከላከያ ሚኒስቴር በጀት ድርሻ ከ12 ቢሊዮን በላይ ብር ደርሷል ተብሏል። የሰሜኑ ጦርነት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መፍትሔ ማግኘቱን ተከትሎ መከላከያ ሚኒስቴር ለ2016 በጀት ዓመት 50 ቢሊዮን ብር እንደተያዘለት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረበው የቀጣዩ ዓመት ረቂቅ በጀት ለመረዳት ተችሏል።…
Read More
የመንግሥት ዓመታዊ በጀት ጉድለት የ281 ቢሊዮን ብር ጭማሪ አሳየ

የመንግሥት ዓመታዊ በጀት ጉድለት የ281 ቢሊዮን ብር ጭማሪ አሳየ

ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የ2016 በጀት ዓመት አጠቃላይ የመንግሥት በጀት የ281 ቢሊዮን ብር ጉድለት እንደገጠመው የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሺዴ አስታውቀዋል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2016 በጀት ዓመት የመንግሥት በጀት 801.65 ቢሊዮን ብር እንዲሆን፤ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መምራቱ የሚታወስ ነው፡፡ ይህንኑ ተከትሎ ምክር ቤቱ የቀረበውን የበጀት ረቂቅ እየገመገመ ነው፡፡ የገንዘብ ሚኒስትሩ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት፤ መንግሥት ለ2016 ካረቀቀው አጠቃላይ በጀት ውስጥ የ281 ቢሊዮን ብር ጉድለት ማጋጠሙን ጠቁመዋል፡፡ የዓመቱ የበጀት ጉድለት በመጠናቀቅ ላይ ከሚገኘው የ2015 በጀት ዓመት የበጀት ጉድለት 50 ቢሊዮን ብር ገደማ ሆኗል፡፡ የ2015 በጀት ዓመት አጠቃላይ በጀት 786 ቢሊዮን ብር የነበረ ሲሆን፤ የበጀት ጉድለቱ 231 ቢሊዮን ብር መሆኑን ሚኒስትሩ…
Read More
የቲንክ ያንግ ኮዲንግ ስኩል ስልጠና በድጋሜ ሊጀምር እንደሆነ ተገለጸ

የቲንክ ያንግ ኮዲንግ ስኩል ስልጠና በድጋሜ ሊጀምር እንደሆነ ተገለጸ

ቲንክ ያንግ (ThinkYoung) እና ቦይንግ (Boeing) ለሁለተኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው 20ኛው የThinYoung Codeing School ምዝገባ መጀመሩን አስታውቀዋል። መርሃ ግብሩ ከሀምሌ 7 እስከ 10 ቀን 2015 ዓ. ም የሚካሄድ ሲሆን እድሜያቸው ከ9-18 ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ነፃ የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ ትምህርት ይሰጣል ተብሏል። የቲንክ ያንግ ኮዲንግ ትምህርት ቤት ሥርዓተ ትምህርት በባለሙያዎች የተመቻቹ ሮቦቲክስ እና ሮቦቲከስን  ጨምሮ የተለያዩ ተግባራትን የሚሽፍን ይሆናል። በተጨማሪም የቦይንግ ተወካዮች በአቪዬሽን እና በሌሎች የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ መስኮች ተነሳሽነትን ለመፍጠር ልምዳቸውን ለተሳታፊዎች እንደሚያካፍሉ ተገልጿል። እንዲህ ባለው የቲንክ ያንግ እና በቦይንግ አጋርነት በመሰል ኮዲንግ ትምህርት ላይ በተሳተፉ ከ1,300 በላይ ወጣቶች ህይወት ላይ በጎ ተጽዕኖ ያሳድረ ሲሆን በቀደሙት ዙሮች ውስጥ…
Read More
ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

በኮንስትራክሽን ሥራ የሚሰማሩ 50 ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ወደ ጀርመን ከማቅናታቸው በፊት አዲስ አበባ ባለው የጀርመን ኢንስቲትዩት ተጨማሪ ስልጠናዎችን በመውሰድ ላይ ናቸው፡፡ በኮንስትራክሽን ሥራ ለመሠማራት የሚያበቃቸውን ሥልጠና ያጠናቀቁ የመጀመሪያው ዙር ባለሙያዎች ወደ ጀርመን እንደሚሄዱ ተገልጿል፡፡ ሥልጠናቸውንና ፈተናቸውን አጠናቀው ጀርመን ከሚገኙ አሠሪዎቻቸው ጋር የሥራ ውል የተፈራረሙት የመጀመሪያዎቹ ተጓዦች በመጪው አንድ ወር ውስጥ  ጉዞ እንደሚያደርጉ ተሰምቷል።  ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በሲቭል ኢንጂነሪንግ፣ በኮንስትራክሽን ማናጅሜንት ቴክኖሎጂ፣ በአርክቴክቸርና መሰል ሙያዎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ምሩቃን ወጣቶች ጎኤቴ በመባል በሚታወቀው የጀርመን ባህልና ቋንቋ ኢንስቲትዩት ሥልጠናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሥምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ንጉሡ ጥላሁን እንዳሉት ሥልጠናው ከሦሥት ዓመት በፊት በቀድሞው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር…
Read More
ኢትዮጵያ የሂዩማን ራይትስ ዋች ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የሂዩማን ራይትስ ዋች ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ ሂዩማን ራይትስ ዋች በትግራይ ክልል ተፈጸመ በሚል ያወጣውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርት እንደማትቀበለው አስታውቃለች። በፌደራል መንግስቱ እና በትግራይ ሀይሎች መካከል የሰላም ስምምነት ቢፈረምም አሁንም በትግራይ ምዕራባዊ አካባቢዎች የሚካሄደው የዘር ማጽዳት ወንጀል መቀጠሉንና የሰብአዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ አካላትም ለፈጸሙት ግፍ ተጠያቂ አልተደረጉም በማለት ሂዩማን ራይት ወች ከሰሞኑ ያወጣውን ሪፖርት አስመልክቶ መንግስት ምላሽ ሰጥቷል፡፡ መንግስት በምላሹም ሪፖርቱ በአንዳንድ አካባቢዎች ጉልህ የሆኑ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መፈጸማቸውን የሚገልጽ መሰረተ ቢስ ሪፖርት ነው ሲል ተችቷል። አክሎም በሰሜኑ ኢትዮጵያ ክፍል የነበረው ግጭት በርካታ አካባቢዎችን ለጉዳት ያጋለጠ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ የተወሰነ አካባቢን መርጦ ደጋግሞ ሪፖርት በማዘጋጀት በሰብዓዊ መብት አጀንዳ ሽፋን የተለየ የፖለቲካ ተልዕኮዉን ለማሳካት ዓላማ ያደረገ…
Read More