Blog

የአሜሪካ የልማት ተራድዖ ድርጅት በኢትዮጵያ ያቋረጠውን የምግብ እርዳታ ዳግም አስጀመረ

የአሜሪካ የልማት ተራድዖ ድርጅት በኢትዮጵያ ያቋረጠውን የምግብ እርዳታ ዳግም አስጀመረ

እርዳታው የተጀመረው የኢትዮጵያ መንግስት ከእርዳታው ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ስምምነት እንደማይኖረው ከተስማማ በኋላ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የአሜሪካ መንግሥት ዓለም አቀፍ የልማት ተራድዖ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) በኢትዮጵያ ያቋረጠውን የምግብ እርዳታ ለስደተኞች ብቻ መልሶ ለማስጀመር መወሰኑን አስታውቋል። ድርጅቱ የእርዳታ እህል አቅርቦቱን የሚጀምረው በኢትዮጵያ ለሚገኙ ለኹሉም የእርዳታ ፈላጊዎች ሳይሆን፤ በአገሪቱ ተጠልለው ለሚገኙ የጎረቤት አገራት ስደተኞች ብቻ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የረድኤት ድርጅቱ የኢትዮጵያ መንግሥት እና አጋሮቹ የስደተኞች የምግብ እርዳታ አቅርቦት መዋቅር ላይ ለውጦችን በማድረጋቸው እዚህ ውሳኔ ላይ መድረሱን የገለጸ ሲሆን፤ “የኢትዮጵያ መንግሥት በአገሪቱ ለሚገኙ ስደተኞች የምግብ እርዳታን በማጓጓዝ፣ በማከማቸት እና በማከፋፈል ዙሪያ ምንም አይነት ተሳትፎ እንደማይኖረው ስምምነት ላይ በመደረሱ የእርዳታ እህል አቅርቦቱን ለመስጀመር መወሰኑን ተገልጿል፡፡ በዚህም በኢትዮጵያ…
Read More
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወጣት አፍሪካውያን መሪዎች ሽልማትን አሸነፉ

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወጣት አፍሪካውያን መሪዎች ሽልማትን አሸነፉ

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ በChoiseul100Africa በአፍሪካ የኢኮኖሚ እድገት ውስጥ ትልቅ ሚና ከሚጫወቱ 100 ወጣት አፍሪካዊ መሪዎች መካከል በአንደኛ ደረጃ ተመረጡ። "Choiseul 100 አፍሪካ" ልዩ የሆነ በሿዘል ኢንስቲትዩት የሚደረግ ጥናት ሲሆን አፍሪካን ወደ ከፍተኛ የኢኮኖሚ፣ የማህበረሰብ እና የባህል እድገት ደረጃ የማድረስ አላማ ያነገበና እድሜያቸው 40 እና ከዚያ በታች የሆኑትን 200 ወጣት የአፍሪካ መሪዎችን በመለየት እውቅና የሚሰጥ በፈረንሳይ የሚገኝ ተቋም ነው። ኩባንያው ሽልማቱን አስመልክቶ ባሰራጨው መግለጫ "...የሞባይል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን፣ የዲጂታል እና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ ረገድ  ላከናወኗቸውናእና እያከናወንን ላለናቸው ስራዎችና ስለጥረታችን  የተሰጠ አበረታች እውቅና መሆኑን በመገንዘብ ታላቅ ኩራት ይሰማናል" ብሏል። ፍሬህይወት ታምሩ ከ2018 ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ንብረት…
Read More
የአፍሪካ ከተማ ከንቲባዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው

የአፍሪካ ከተማ ከንቲባዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው

ከነገ ጀምሮ የአፍሪካ ከንቲባዎች የሊደርሺፕ ኢኒሼቲቭ መድረክ በአዲስ አበባ እንደሚያካሂድ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ እናትአለም መለሰ እንዳሉት ከተማዋ ከነገ ጀምሮ ዓለም አቀፍ፣ አሕጉር አቀፍ እንዲሁም አገር አቀፍ ልዩ ልዩ መድረኮች እንደምታስተናግድ አመልክተዋል። ለሁለት ቀናት በሚካሄደው የአፍሪካ ከንቲባዎች የሊደርሺፕ ኢኒሼቲቭ መድረክ፣ ከ28 እና 29 የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም የልህቀት ማዕከልን ለማቋቋም የሚረዳ ዓለም አቀፍ የምክክር መድረክ እንዲሁም ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 1 ቀን 2016 ዓ.ም የሀገር አቀፍ መሪዎች የልምድ ልውውጥ መድረኮች ይካሄዳሉ ብለዋል፡፡ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም አበረታች ውጤት ማስመዝገብ የቻለ መሆኑን በመግለጽ አስተዳደሩ 9 ሺህ 500 ለሚሆኑ ሕጻናትና ወላጆች በከተማዋ አልሚ ምግብ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ መድረኮቹ በሁሉም…
Read More
ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል አደረጉ

ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል አደረጉ

የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ በላቲቪያ ሪያ በመደረግ ላይ ሲሆን የወንዶች እና የሴቶች የ5 ሺህ ሜትር ውድድር ፍጻሜውን አግኝቷል። በወንዶች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት ውድድሩን አጠናቀዋል። አትሌት ሀጎስ ገብረ ህይወት 12:59 በሆነ ሰዓት ውድድሩን በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ ደግሞ በ13:02 በመግባት ሁለተኛ ሆኖ አጠናቋል። ኢትዮጵያዊው አትሌት ሀጎስ ገብረ ህይወት የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ የወንዶች 5ኪ.ሜ ውድድርን ማሸነፍ የቻለ የመጀመሪያው አትሌት ሆኗል። በሴቶች ተመሳሳይ ርቀት ውድድር ኬንያዊያኑ አትሌት ቺቤት አንደኛ እንዲሁም ናሬንጉሩክ ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ኢትዮጵያዊያኑ አትሌቶች እጅጋየሁ ታዬ እና መዲና ኢሳ ደግሞ ሶስተኛ እና አራተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በሌላ የ1 ማይል ርቀት ውድድር ደግሞ አትሌት ድርቤ ወልተጂ ኬንያዊቷን የ 1500ሜ…
Read More
ሶስተኛው የህዳሴው ግድብ ድርድር በካይሮ እንደሚካሄድ ተገለጸ

ሶስተኛው የህዳሴው ግድብ ድርድር በካይሮ እንደሚካሄድ ተገለጸ

ባሳለፍነው ሐምሌ ወር ላይ በሱዳን ለተከሰተው ጦርነት እልባት ለመፈለግ በሚል በካይሮ በተካሄደው የጎረቤት ሀገራት መድረክ ላይ ለመሳተፍ ወደ ስፍራው ያቀኑት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ ጋር የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድርን ለማስቀጠል መስማማታቸው ተገልጾ ነበር፡፡ በዚህ ስምምነት መሰረት ከሶስት ሳምንት በፊት የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የግድቡ ተደራዳሪ የቴክኒክ ባለሙያዎች በግብጽ ካይሮ ተገናኝተው ተወያይተዋል። እንዲሁም ሁለተኛው ዙር የቴክኒክ ባለሙያዎች ውይይት ደግሞ ባሳለፍነው ቅዳሜ እና እሁድ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የግድቡ ተደራዳሪዎች፣ ባለሙያዎች እና ዲፕሎማቶች የተሳተፉበት ይህ ውይይት ከተጠናቀቀ በኋላ የሁለቱም ሀገራት በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫ አውጥተዋል፡፡ የግብጽ ውሃ እና መስኖ ሚኒስትር ሀኒ ስዌለም እንዳሉት በአዲስ አበባ የተካሄደው ድርድር…
Read More
ስድስት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአበረታች መድሀኒት ምክንያት ለዓመታት ከውድድሮች ታገዱ

ስድስት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአበረታች መድሀኒት ምክንያት ለዓመታት ከውድድሮች ታገዱ

የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን በተጠረጠሩ አትሌቶች ላይ ጊዜያዊ እገዳ በመጣል ጉዳዩን ሲያጣራ መቆየቱን አስታውቋል። እገዳ የተላለፈባቸው አይሌቶች አትሌት ሹሜ  ጣፋ ደስታ እና  አትሌት መንግስቱ በቀለ ተዴቻ  የተከለከሉ አበረታች ቅመሞችን ወይም ዶፒንግ በመጠቀም የህግ ጥሰት የፈፀሙ መሆኑን አረጋግጫለሁ ብላል። በዚህም መሠረት የረጅም ርቀት ሯጭ የሆነዉ አትሌት  ሹሜ ጣፋ ደስታ 5-methylhexan-2-amine የተባለውን የተከለከለ ንጥረ-ነገር ተጠቅሞ በፈፀመው  የፀረ-አበረታች ቅመሞች የህግ ጥሰት በውድድሩ ያስመዘገበው ውጤት እንዲሰረዝ እና  እ.ኤ.አ ከግንቦት 25/2023  ጀምሮ ለአራት (4) አመታት በማንኛውም ስፖርታዊ ውድድር ላይ እንዳይሳተፍ  የቅጣት ውሳኔ እንደተላለፈበት ተገልጿል። በተመሳሳይ መልኩ አትሌት መንግስቱ በቀለ ተዴቻ ቻይና አገር ውስጥ በነበረው ውድድር ላይ Erythropoietin (EPO) የተባለዉን የተከለከለ አበረታች ቅመም ተጠቅሞ በመገኘቱ የፀረ-…
Read More
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እየተባባሰ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳሳሰበው ገለጸ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እየተባባሰ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳሳሰበው ገለጸ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እየተባባሳ ነው ያለው ወንጀልና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳስጨነቀው ተናግሯል። የህብረቱ ከፍተኛ ተወካይ ጆሴፍ ቦሬል የኢትዮጵያ መንግስት አፋጣን እርምጃ መውሰድ አለበት ብለዋል። ፍትህና ተጠያቂነት የህብረቱና የኢትዮጵያ ግንኙነት ቀስ እያለ ወደ መደበኛነት ለሚመጣው ግንኙነት ሁኔታዎች ናቸውም ሲሉ ሀሳባቸውን በቀድሞው ትዊተር በአሁኑ ኤክስ ገልጸዋል። ከሰሞኑን በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሁኔታ የቀረበ ሲሆን፤ ሀገሪቱ ከፍተኛ ክስ ቀርቦባታል። በተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት የተቋቋመው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የኢትዮጵያ መሪማሪ ሪፖርቱን አቅርቧል። የመርማሪ ቡድኑ ባለሞያ የሆኑት መሀመድ ቻንዴ ኦቶማን ባለፈው ዓመት ለተመድ የሰብዓዊ ምክር ቤት የኢትዮጵያን ሁኔታ ከገለጽን ወዲህ ሰብዓዊ መብት በሀገሪቱ በእጅጉ ተባብሶ ቀጥሏል ብለዋል። በትግራይ ክልል…
Read More
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ዙር የሶስትዮሽ ድርድር በአዲስ አበባ ተጀመረ

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ዙር የሶስትዮሽ ድርድር በአዲስ አበባ ተጀመረ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ ግብጽ በሱዳን መረጋጋት ዙሪያ ባዘጋጀችው የጎረቤት ሀገራት የመሪዎች መድረክ ላይ በተገኙበት ወቅት ከግብጽ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ጋር በግድቡ ዙሪያ መምከራቸው ይታወሳል፡፡ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ መወያየታቸው ሲገለጽ የግድቡ ውሀ አሞላል ዙሪያ ተወያይተው እስከ መስከረም ወር ድረስ ተቋርጦ የነበረውን የሶስትዮሽ ውይይት ለማስጀመር ተስማምተው ነበር፡፡ በዚህ ስምምነት መሰረት ከሁለት ሳምንት በፊት የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የግድቡ ተደራዳሪ የቴክኒክ ባለሙያዎች በግብጽ ካይሮ ተገናኝተው ተወያይተዋል፡፡ ሁለተኛው የሶስትዮሽ ውይይትም ዛሬ በአዲስ አበባ የተጀመረ ሲሆን የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የግድቡ ተደራዳሪዎች፣ ባለሙያዎች እና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት በሁለት ተርባይኖቹ ሀይል ማመንጨት የጀመረው የሕዳሴው ግድብ…
Read More
ብሪታንያ ከመቅደላ የዘረፈቻቸውን ቅርሶች ለኢትዮጵያ አስረከበች

ብሪታንያ ከመቅደላ የዘረፈቻቸውን ቅርሶች ለኢትዮጵያ አስረከበች

ከመቅደላ ተዘርፈው የተወሰዱ የተለያዩ የኢትዮጵያ ቅርሶች በለንደን ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተመለሱ በ1868 በአጼ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግሥት በብሪታንያ ተዘርፈው የተወሰዱ የኢትዮጵያ ቅርሶች መመለሳቸውን በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡ ከተመለሱት ቅርሶች መካከል በ1868 ዓ.ም ከመቅደላ የተዘረፈ የመድሃኒያለም ታቦት፣ የልኡል አለማየሁ የጸጉር ዘለላ፣ ከብር የተሰሩና በነሃስ የተለበጡ ሦስት ዋንጫዎች እንዲሁም በዘመኑ ጦርነት ላይ የዋለ የጦር ጋሻ እንደሚገኙበት ገልጿል፡፡ ለንደን በሚገኘው የአቴናየም ክለብ በተካሄደው የቅርሶቹ ርክክብ ሥነ ስርዓት ላይ፤ በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈሪ መለሰ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ልኡካን ቡድን፣ የብሄራዊ ቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ ተወካይ፣ የብሪታኒያ ፓርላማ አባላት፣ ቅርሶቹን ለማሰመለስ የተባበሩ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በመርሀ ግብሩ ላይም አምባሳደር ተፈሪ መለሰ፤ የተመለሱት የተለያዩ…
Read More
በአማራ ክልል አራት ሚሊዮን ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት አለመመለሳቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል አራት ሚሊዮን ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት አለመመለሳቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ለ2016 የትምህርት ዘመን 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ገደማ ተማሪዎች እስካሁን አልተመዘገቡም ተባለ በአማራ ክልል ለ2016 የትምህርት ዘመን ይመዘገባሉ ተብሎ ከተያዘው ከ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች መካከል እስከ  ሰኞ መስከረም 07/2016 ድረስ የተመዘገቡት ተማሪዎች ቁጥር 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብቻ መሆኑን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ገልጿል፡፡ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጌታቸው ቢያዝን፤ ለ2016 የትምህርት ዘመን ከነሐሴ 23/2015 ጀምሮ እየተካሄደ ባለው የተማሪዎች ምዝገባ እስከ ሰኞ ድረስ የተመዘገቡት ተማሪዎች 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ተማሪዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። የተማሪዎችን የምዝገባ ጊዜ እስከ ሚቀጥለው ሳምንት ድረስ ነው ያሉት ኃላፊው “በተያዘው ዓመት ከ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ በእቅድ ተይዞ…
Read More