06
Oct
እርዳታው የተጀመረው የኢትዮጵያ መንግስት ከእርዳታው ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ስምምነት እንደማይኖረው ከተስማማ በኋላ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የአሜሪካ መንግሥት ዓለም አቀፍ የልማት ተራድዖ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) በኢትዮጵያ ያቋረጠውን የምግብ እርዳታ ለስደተኞች ብቻ መልሶ ለማስጀመር መወሰኑን አስታውቋል። ድርጅቱ የእርዳታ እህል አቅርቦቱን የሚጀምረው በኢትዮጵያ ለሚገኙ ለኹሉም የእርዳታ ፈላጊዎች ሳይሆን፤ በአገሪቱ ተጠልለው ለሚገኙ የጎረቤት አገራት ስደተኞች ብቻ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የረድኤት ድርጅቱ የኢትዮጵያ መንግሥት እና አጋሮቹ የስደተኞች የምግብ እርዳታ አቅርቦት መዋቅር ላይ ለውጦችን በማድረጋቸው እዚህ ውሳኔ ላይ መድረሱን የገለጸ ሲሆን፤ “የኢትዮጵያ መንግሥት በአገሪቱ ለሚገኙ ስደተኞች የምግብ እርዳታን በማጓጓዝ፣ በማከማቸት እና በማከፋፈል ዙሪያ ምንም አይነት ተሳትፎ እንደማይኖረው ስምምነት ላይ በመደረሱ የእርዳታ እህል አቅርቦቱን ለመስጀመር መወሰኑን ተገልጿል፡፡ በዚህም በኢትዮጵያ…