Dopinginethiopia

ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከማንኛውም ስፖርታዊ ውድድሮች ታገዱ፡፡

ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከማንኛውም ስፖርታዊ ውድድሮች ታገዱ፡፡

የአለም አትሌቲክስ እና ብሔራዊ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን የአበረታች ቅመምች ህግ ጥሰት በፈፀሙ አትሌቶች ላይ የቅጣት ውሳኔ ማስተላለፉ ተገልጿል። የቅጣት ውሳኔው ከተላለፈባቸው አትሌቶች መካከል አትሌት ሳሙኤል አባተ ዘለቀ ፣ አትሌት ፀሐይ ገመቹ በያን እና አትሌት ህብስት ጥላሁን አስረስ ሲሆኑ የአበረታች ቅመሞች ህግ ጥሰት መፈጸማቸው ተረጋግጧል ተብሏል። ጥሰቱን ተከትሎም አትሌት ሳሙኤል አባተ ዘለቀ የካቲት 2015 ዓ.ም በተካሄደው ምርመራ ኢፒኦ የተባለውን የተከለከለ ንጥረ ነገር መጠቀሙ ተረጋግጧል፡፡ በዚህም መሰረት አትሌት ሳሙኤል አባተ ለ2 ዓመታት ማለትም እስከ ሚያዝያ 2018 ዓ.ም ድረስ በማንኛውም የስፖርት ውድድር እንዳይሳተፍ ቅጣት ተጥሎበታል፡፡ አትሌት ፀሐይ ገመቹ በያን በተደረገላት የአትሌት ባይሎጂካል ፖስፖርት (ABP) ምርመራ አበረታች ቅመም መጠቀሟ የተረጋገጠባት ሌላኛዋ ኢትዮጵያ አትሌት ስትሆን…
Read More
ስድስት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአበረታች መድሀኒት ምክንያት ለዓመታት ከውድድሮች ታገዱ

ስድስት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአበረታች መድሀኒት ምክንያት ለዓመታት ከውድድሮች ታገዱ

የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን በተጠረጠሩ አትሌቶች ላይ ጊዜያዊ እገዳ በመጣል ጉዳዩን ሲያጣራ መቆየቱን አስታውቋል። እገዳ የተላለፈባቸው አይሌቶች አትሌት ሹሜ  ጣፋ ደስታ እና  አትሌት መንግስቱ በቀለ ተዴቻ  የተከለከሉ አበረታች ቅመሞችን ወይም ዶፒንግ በመጠቀም የህግ ጥሰት የፈፀሙ መሆኑን አረጋግጫለሁ ብላል። በዚህም መሠረት የረጅም ርቀት ሯጭ የሆነዉ አትሌት  ሹሜ ጣፋ ደስታ 5-methylhexan-2-amine የተባለውን የተከለከለ ንጥረ-ነገር ተጠቅሞ በፈፀመው  የፀረ-አበረታች ቅመሞች የህግ ጥሰት በውድድሩ ያስመዘገበው ውጤት እንዲሰረዝ እና  እ.ኤ.አ ከግንቦት 25/2023  ጀምሮ ለአራት (4) አመታት በማንኛውም ስፖርታዊ ውድድር ላይ እንዳይሳተፍ  የቅጣት ውሳኔ እንደተላለፈበት ተገልጿል። በተመሳሳይ መልኩ አትሌት መንግስቱ በቀለ ተዴቻ ቻይና አገር ውስጥ በነበረው ውድድር ላይ Erythropoietin (EPO) የተባለዉን የተከለከለ አበረታች ቅመም ተጠቅሞ በመገኘቱ የፀረ-…
Read More