Blog

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ቻይና አመሩ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ቻይና አመሩ

የቻይና ቤልት ኤንድ ሮድ ዓመታዊ ጉባኤ ከሁለት ቀናት በኋላ በቤጂንግ ይካሄዳል፡፡ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን ጨምሮ በርካታ የዓለማችን መሪዎች በዚህ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ቤጂንግ በማምራት ላይ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በዚሁ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ቻይና ማምራታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ ቻይና ለኢትዮጵያ ብድር ከሚሰጡ ሀገራት መካከል ዋነኛዋ ስትሆን በተለይም ለኤርፖርት ማስፋፊያ፣ ለመንገድ እና ለደረቅ ወደብ ልማት ግንባታዎች በቻይና ብድር ተገንብተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በጦርነት እና በኮሮና ቫይረስ መጎዳቱን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት የብድር ጫና ውስጥ በመግባቱ የብድር መክፈያ ጊዜ እንዲራዘምለት በመጠየቅ ላይ ነው፡፡ ቻይና የኢትዮጵያን የብድር መክፈያ ጊዜ በአንድ ዓመት ማራዘሟ የተገለጸ ሲሆን ከዓለም ባንክ…
Read More
በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት ወንጀል ከፍተኛ ስጋት መኖሩን ተመድ አስታወቀ

በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት ወንጀል ከፍተኛ ስጋት መኖሩን ተመድ አስታወቀ

በኢትዮጵያ በፌደራል መንግሥት የጸጥታ ሀይሎች እና በተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ ታጣቂዎች መካከል በቀጠለው ውጊያ ምክንያት፤ የዘር ማጥፋት እና ተያያዠ አሰቃቂ ወንጀሎች እንዲፈጸሙ የሚያስችል ከፍተኛ ስጋት መፍጠሩን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካሪ ገለጹ። የድርጅቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል መከላከል ልዩ አማካሪ አሊስ ዋይሪሙ በኢትዮጵያ ስላለው ኹኔታ አስመልክተው ባወጡት መግለጫ፤ በትግራይ፣ አማራ፣ አፋር እና ኦሮሚያ ክልሎች እየተካሄዱ ባሉ ውጊያዎች ምክንያት በአገሪቱ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት እና ተያያዠ አሰቃቂ ወንጀሎች የመፈጸም ኹኔታዎች እንዲኖሩ ማድረጉን ጠቁመዋል። "በኢትዮጵያ እየተፈጸሙ ስላሉት ወንጀሎች የተመለከቱ የሚደርሱን ሪፖርቶች እጅግ የሚረብሹ ናቸው" ያሉት ልዩ አማካሪዋ፤ "በአፋጣኝ ኹኔታውን ለመከላከል እርምጃ ሊወሰድ ይገባል።" ብለዋል። አክለውም፤ "እየደረሱን ካሉ ሪፖርቶች መካከል የአንድ ቤተሰብ አባላት በሙሉ ግድያ እንደተፈጸመባቸው፣ ቤተሰቦች…
Read More
ኢትዮጵያ ከእስራኤል ጎን እንድትቆም ተጠየቀች

ኢትዮጵያ ከእስራኤል ጎን እንድትቆም ተጠየቀች

ኢትዮጵያ ከእስራኤል ጎን እንድትቆም በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ ጥሪ አቀረበ የኢትዮጵያ መንግሥት እና ተቋማት፣ በሐማስ የተፈጸመውን ጥቃት እንዲያወግዙ፣ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለልኝ አድማሱ በሰጡት መግለጫ ጠይቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት እስከ አሁን ስለጥቃቱም ይኹን ስለ ግጭቱ በይፋ የሰጠው መግለጫ የለም፡፡ ኾኖም፣ ኢትዮጵያ ገለልተኛ አቋም እንዳላትና ግጭቱ በሰላም እንዲፈታ እንደምትፈልግ፣ በእስራኤል የኢትዮጵያ አምባሳደር፣ ትላንት ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡ ሃማስ በእስራኤል ላይ መጠነ ሰፊ  ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ በሀገሪቱ የሚገኙ ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያዉያን ሰለባ መሆናቸዉን በኢትዮጵያ እስራኤል ኤምባሲ  አስታዉቋል፡፡ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለሊ አደማሱ እንዳሉት በወቅታዊ የጉዳቱን መጠን አሁን ላይ መግለጽ ባይቻልም ከተጎጂዎች መካከል ግን ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያዉያን እንደሚኖሩ ተናግረዋል፡፡ በጥቃቱ ከ1200 በላይ እስራኤላዉያን መሞታቸዉን አምባሳደር አለሊ…
Read More
ኢትዮጵያ ከሱዳን ሽንኩርት ልታስመጣ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ ከሱዳን ሽንኩርት ልታስመጣ መሆኗን ገለጸች

በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያጋጠመውን የጸጥታ ችግር ተከትሎ የመሰረታዊ ምግብ አቅርቦቶች እጥረት አጋጥሟል፤፡ የምርት እጥረት ማጋጠሙን ተከትሎም ህዝቡ በዋጋ ንረት እየተጎዳ እንደሆበነም ተገልጿል፡፡ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ በከተማዋ ያጋጠመውን የሽንኩርት እጥረት ለመፍታት ከሱዳን ለማምጣት ማቀዱን አስታውቋል፡፡ ከበዓላቱ ጋር ተያይዞ የሽንኩርት ዋጋ ጭማሪ በማሳየቱ እና በየጊዜው በአትክልት ላይ  ለሚደረገው የዋጋ ጭማሪ መፍትሄ ተብለው እየተሰሩ ያሉ ስራዎች መኖራቸውን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ እንደተናገሩት በመደበኛ ገበያው ላይ ለተከሰተው  የዋጋ ንረት መፍትሄ ተብለው እየተሰሩ ያሉ ስራዎች  መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የእሁድ ገበያ ላይ ከሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ጋር በተያያዘ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን እና ሱዳንን ጨምሮ…
Read More
የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሲቪል ሥራ በተያዘው ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ፡፡

የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሲቪል ሥራ በተያዘው ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች እና ፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ከሁለት ወራት የእረፍት ጊዜ በኋላ ተከፍቷል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በምክር ቤቶቹ የመክፈቻ ንግግራቸው ላይ የመንግስትን የአንድ ዓመት የትኩረት መስኮች ይፋ አድርገዋል፡፡ ፕሬዝዳንቷ በንግግራቸው ላይ ያለፈው ዓመት የኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ ግድብ 4ኛ ዙር የውኃ ሙሌት መጠረናቀቁ ትልቁ ስኬት ነበር ብለዋል፡፡ 90 በመቶ ግንባታው የተጠናቀቀው የህዳሴው ግድብ የሲቪል ምህንድስና ስራ ሙሉ ለሙሉ በዚህ ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተናግረዋል፡፡ ይህ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ የሚያመነጭ ግድብ ሳይሆን የቱሪዝምና የውሃ ሀብት፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የሞራል ልዕልና ነው ብለዋል፡፡ ፕሬዝዳንቷ አክለውም መንግስት በተያዘው ዓመት የሕግ የበላይነትን ማስከበር፣ የኑሮ ውድነትን መቀነስ፣ የስራ እድል ፈጠራ ፣ የምግብ ዋስትና እና መልካም አስተዳድር ልዩ ትኩረት…
Read More
ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውስጥ 817 ሺህ ተማሪዎች መውደቃቸው ተገለጸ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውስጥ 817 ሺህ ተማሪዎች መውደቃቸው ተገለጸ

1ሺህ 328 ትምህርት ቤቶች ደግሞ አንድም ተማሪ እንዳላሳለፉ ተገልጿል።በ2015 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺሕ 099 ተማሪዎች ውስጥ፤ 817 ሺሕ 838 ተማሪዎች ከ50 በመቶ በታች የሆነ ውጤት ማምጣታቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የ2015  የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ ከአጠቃላይ 845 ሺሕ 099 ተፈታኞች ውስጥ 27 ሺሕ 267 ተማሪዎች ወይንም (ሦስት ነጥብ ኹለት በመቶ ብቻ) 50 በመቶ እና ከዛ በላይ ውጤት አምጥተዋል። በተፈጥሮ ሳይንስ ከተፈተኑ 356 ሺሕ 878 ተማሪዎች ውስጥ 19 ሺሕ 017 ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዛ በላይ ውጤት ሲመጡ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ ከተፈተኑ 488 ሺሕ 221 ተማሪዎች ውስጥ 7…
Read More
በእስራኤልና ሃማስ ጦርነት ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያውያን መጎዳታቸው ተገለጸ

በእስራኤልና ሃማስ ጦርነት ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያውያን መጎዳታቸው ተገለጸ

ሃማስ በእስራኤል ላይ መጠነ ሰፊ  ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ በሀገሪቱ የሚገኙ ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያዉያን ሰለባ መሆናቸዉን በኢትዮጵያ እስራኤል ኤምባሲ  አስታዉቋል፡፡ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለሊ አደማሱ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት በወቅታዊ የጉዳቱን መጠን አሁን ላይ መግለጽ ባይቻልም ከተጎጂዎች መካከል ግን ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያዉያን እንደሚኖሩ ተናግረዋል፡፡ በጥቃቱ ከ700 በላይ እስራኤላዉያን መሞታቸዉን አምባሳደር አለሊ አስታዉቀዋል፡፡ በተጨማሪም ከ2 ሺህ በላይ ዜጎች ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዉ በሞት አፋፍ ላይ እንደሚገኙ አምባሳደሩ ተናግረዋል፡፡ አሁን ላይ የእስራኤል ጦር ኃይል የሃማስን ጥቃት በመመከት  ጎን ለጎን የሞቱ ዜጎችን እየቀበረ እንደሚገኝ ኤምባሲዉ አስታዉቋል፡፡ ሃማስ የጀመረዉ ጥቃት በቀላሉ የሚታልፍ እንዳልሆነም አምባሳደር አለሊ ገልጸዋል፡፡ እስራኤል አንድ መቶ ሺህ ወታደሮቿን ወደ ጋዛ ማሰመራቷንም አስታዉቃለች፡፡…
Read More
ቻይና በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልህቀት ማዕከል ለመገንባት ተስማማች

ቻይና በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልህቀት ማዕከል ለመገንባት ተስማማች

ይህ የቴክኖሎጂ ልህቀት ማዕከል ግንባታ ዘጠኝ ቢሊዮን ብር ይፈጃል ተብሏል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና የቻይናው ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የቴክኖሎጂ ልኅቀት ማዕከል ለመገንባት የውል ስምምነት ሠነድ ተፈራርመዋል፡፡ የልህቀት ማዕከል ግንባታው ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ ግቢ ውስጥ ይገነባል የተባለ ሲሆን ለፕሮጀክቱ 9 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ተመድቧል ተብሏል፡፡ ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሽፈራው ተሊላና የቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ኤክስኪዩቲቭ ማኔጅንግ ዳይሬክተር ው ጁይ ናቸው፡፡ ማዕከሉ ሲጠናቀቅ ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር የተጣጣመና ለደንበኞች የሚሰጠውን አገልግሎት አስተማማኝ፣ ቀልጣፋና ዘመናዊ የሚያደርግ እንደሆነ አቶ ሽፈራው ገልጸዋል፡፡ ው ጁይን  በበኩላቸው የማዕከሉን ግንባታ በተያዘለት ጊዜ በጥራት  አጠናቅቀው እንደሚያስረክቡ አረጋግጠዋል፡፡ ማዕከሉ የኤሌክትሪካል ቴክኖሎጂ ሙያ የሰው ኃይል…
Read More
የሆቴል ባለቤቶች የባንክ ዕዳ መክፈያ ጊዜ እንዲራዘምላቸው ጠየቁ

የሆቴል ባለቤቶች የባንክ ዕዳ መክፈያ ጊዜ እንዲራዘምላቸው ጠየቁ

የኢትዮጵያ የሆቴል እና ቱሪዝም አሠሪዎች ፌዴሬሽን እንደገለጸው በኢትዮጵያ የሆቴል እና ቱሪዝም ስራ በየጊዜው እየተዳከመ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ዶክተር ፍትህ ወልደሰንበት ለቪኦኤ እንዳሉት የሆቴል እና ቱሪዝም ቢዝነስ በዓለም ላይ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ተዳክሞ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ ወደ ቀድሞ አቋሙ ተመልሷል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያም የሆቴል ኢንዱስትሪ ከኮሮና ቫይረስ ጉዳት እንዲያገግም ለመንግስት በቀረቡለት ምክረ ሀሳቦች መሰረት እርምጃ መውሰዱ ዘርፉን ከባሰ ጉዳት ታድጎታል ብለዋል። የኮቪድ ፕሮቶኮል በሚል ወደ ስራ የተተገበረው አሰራር በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ስራ አቁመው የነበሩ ሆቴሎችን ወደ ስራ እንዲመለሱ ማድረጉን ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል። ይሁንና በኢትዮጵያ ግን በየጊዜው እየተዳከመ እና በርካታ የሆቴል ቢዝነስ ባለሀብቶች እና ባለሙያዎች ወደ ሌላ ቢዝነስ እየገቡ መሆኑንም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል፡፡…
Read More
ኢትዮጵያ በእርዳታ ስርጭት ላለመሳተፍ መስማማቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በእርዳታ ስርጭት ላለመሳተፍ መስማማቷ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ካሳለፍነው ግንቦት ወር ጀምሮ የመጋዝን ስርቆት ተፈጽሞብናል በሚል እርዳታ መስጠት አቁመው ነበር፡፡ እርዳታ መቆሙን ተከትሎም ስደተኞች እና የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ረሀብን ጨምሮ ተረጂዎች ህይወታቸውን እስከማጣት መድረሳቸው በተደጋጋሚ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡ በእርዳታ እህል ስርቆቱ ላይ የፌደራል እና የክልል መንግስታት ባለስልጣናት እጃቸው እንዳለበት በወቅቱ በረድኤት ድርጅቶቹ በኩል ተገልጾም ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ለተረጂዎች የተቀመጠን እህል ወደ ጎረቤት ሀገር ይላክ እንደነበርም የተገለጸ ሲሆን የፌደራል መንግስት በወቅቱ የቀረበበትን ክስ ውድቅ አድርጓል፡፡ የአሜሪካ የልማት ተራድዖ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) ዛሬ ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ያቋረጠውን የምግብ እርዳታ ዳግም ለማስጀመር መወሰኑን አስታውቋል፡፡ እርዳታው የተጀመረው የኢትዮጵያ መንግስት ከእርዳታው ጋር በተያያዘ በስርጭቱ ላይ እጁን እንደማያስገባ ከተስማማ በኋላ…
Read More