13
Oct
በኢትዮጵያ በፌደራል መንግሥት የጸጥታ ሀይሎች እና በተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ ታጣቂዎች መካከል በቀጠለው ውጊያ ምክንያት፤ የዘር ማጥፋት እና ተያያዠ አሰቃቂ ወንጀሎች እንዲፈጸሙ የሚያስችል ከፍተኛ ስጋት መፍጠሩን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካሪ ገለጹ። የድርጅቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል መከላከል ልዩ አማካሪ አሊስ ዋይሪሙ በኢትዮጵያ ስላለው ኹኔታ አስመልክተው ባወጡት መግለጫ፤ በትግራይ፣ አማራ፣ አፋር እና ኦሮሚያ ክልሎች እየተካሄዱ ባሉ ውጊያዎች ምክንያት በአገሪቱ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት እና ተያያዠ አሰቃቂ ወንጀሎች የመፈጸም ኹኔታዎች እንዲኖሩ ማድረጉን ጠቁመዋል። "በኢትዮጵያ እየተፈጸሙ ስላሉት ወንጀሎች የተመለከቱ የሚደርሱን ሪፖርቶች እጅግ የሚረብሹ ናቸው" ያሉት ልዩ አማካሪዋ፤ "በአፋጣኝ ኹኔታውን ለመከላከል እርምጃ ሊወሰድ ይገባል።" ብለዋል። አክለውም፤ "እየደረሱን ካሉ ሪፖርቶች መካከል የአንድ ቤተሰብ አባላት በሙሉ ግድያ እንደተፈጸመባቸው፣ ቤተሰቦች…