04
Oct
ከነገ ጀምሮ የአፍሪካ ከንቲባዎች የሊደርሺፕ ኢኒሼቲቭ መድረክ በአዲስ አበባ እንደሚያካሂድ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ እናትአለም መለሰ እንዳሉት ከተማዋ ከነገ ጀምሮ ዓለም አቀፍ፣ አሕጉር አቀፍ እንዲሁም አገር አቀፍ ልዩ ልዩ መድረኮች እንደምታስተናግድ አመልክተዋል። ለሁለት ቀናት በሚካሄደው የአፍሪካ ከንቲባዎች የሊደርሺፕ ኢኒሼቲቭ መድረክ፣ ከ28 እና 29 የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም የልህቀት ማዕከልን ለማቋቋም የሚረዳ ዓለም አቀፍ የምክክር መድረክ እንዲሁም ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 1 ቀን 2016 ዓ.ም የሀገር አቀፍ መሪዎች የልምድ ልውውጥ መድረኮች ይካሄዳሉ ብለዋል፡፡ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም አበረታች ውጤት ማስመዝገብ የቻለ መሆኑን በመግለጽ አስተዳደሩ 9 ሺህ 500 ለሚሆኑ ሕጻናትና ወላጆች በከተማዋ አልሚ ምግብ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ መድረኮቹ በሁሉም…