30
Aug
የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ታዬ አጽቀስላሴ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ሚንስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት የሶማሊያ መንግሥት ውስጥ ያሉ የተወሰኑ አካላት በኢትዮጵያ ላይ ያልተገባ ስም ማጥፋት ስራ እየሰሩ ነው ብለዋል። ሶማሊያ እንደ ሉዓላዊ ሀገር ከየትኛውም ሀገር ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መመስረት መብቷ ቢሆንም "ይህ የሚሆነው ግን ለሌላ ሀገር ስጋት በማይሆን መልኩ ነው" ሲሉም ሚንስትሩ ተናግረዋል። "በሶማሊያ ያለውን መንግሥት ያቋቋምነው እኛ ነን" ያሉት አምባሳደር ታዬ ይህን ያደረግነው አልሻባብ ስልጣን ቢይዝ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለአካባቢው ሀገራት ስጋት እንደሚሆን ስለምናምን ነውም ብለዋል። የሶማሊያ ሰላም እኛን ይመለከታል፣ ሰላም እንዲመጣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መስዋዕትነት ከፍሏል፣ አሁንም የሶማሊያ ሁኔታ የሚያሳስበን ድንበር ዘሎ የሚመጣ ትርምስን ስለማንፈልግ ነውም…