Lebanon

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቤይሩት እና ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቤይሩት እና ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ

ለፍልስጤም ነጻነት የሚታገለው ሐማስ በእራኤል ላይ ድንገተኛ ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ በመካከለኛው ምስራቅ የተጀመረው ጦርነት አንድ ዓመት ሞልቶታል፡፡ ይህ ጦርነት ወደ ሊባኖስ መስፋፋቱን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በርካታ ዓለማችን አየር መንገዶች ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚያደርጓቸውን በረራዎች አቋርጠዋል፡፡ ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ወደ ቤይሩት እና ወደ ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ በጊዜያዊነት ማቋረጡን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል። አየር መንገዱ በድረገ ገጹ ባጋራው መረጃ ተለዋጭ ማስታወቂያ እስከሚያወጣ ድረስ ወደ ቤይሩት የሚያደርጋቸውን ሁሉንም በረራዎች ማቋረጡን ገልጿል። ወደ ቴልአቪቭ ደግሞ እስከ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በረራ የማያደርግ መሆኑን ነው አየር መንገዱ የገለጸው። በተጠቀሱት አካባቢዎች ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን የጠቀሰው አየር መንገዱ፤ ስለጉዳዩ…
Read More
በሊባኖስ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በከፋ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን ተናገሩ

በሊባኖስ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በከፋ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን ተናገሩ

አንድ ዓመት ሊሞላው ጥቂት ቀናት የቀሩት የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት አሁንም የቀጠለ ሲሆን እስራኤል እና የሊባኖሱ ሂዝቦላህ አዲስ ጦርነት ጀምረዋል፡፡ ኢትዮጵያዊያን ከሚኖሩባቸው የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ሊባኖስ ዋና ከተማዋ ቤሩትን ጨምሮ ሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች በእስራኤል የአየር ላይ ጥቃት ሰለባ ሆነዋል፡፡ ይህን ተከትሎም በሊባኖስ የሚኖሩ ከ30 ሸህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ከቀሪው የሀገሪቱ ዜጎች ጋር የደህንት ስጋት ውስጥ ወድቀዋል፡፡ በሊባኖስ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ህይወታቸውን እንዴት እየመሩ ይሆን ሲል የሀገሪቱ መዲና በሆነችው ቤሩትን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን ጠይቋል፡፡ ለደህንነቷ በመስጋት ስሟ እንዳይጠቀስ የፈለገች አንድ ኢትዮጵያዊ እንዳለችን ከሆነ ነበለት በሚባለው ቦታ ትኖር እንደነበር ነግራናለች፡፡ በአካባቢው ተከታታይ የእስራኤል የአየር ላይ ጥቃቶች መፈጸማቸውን ተከትሎ ወደ…
Read More
ኢትዮጵያ በሊባኖስ የሚኖሩ ዜጎቿን አስጠነቀቀች

ኢትዮጵያ በሊባኖስ የሚኖሩ ዜጎቿን አስጠነቀቀች

በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በቤሩት የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ አስታውቋል። እስራኤል የሃመስ መሪ ኢስማኤል ሃኒየህ እና የሊባሱ ሄዝቦላህ የጦር መሪ ፉአድ ችኩር መግደሏን ተከትሎ ኢራን በእስራኤል ላይ የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ዝታለች። የኢራንን ዛቻ ተከትሎ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል በሚል ከፍተኛ ስጋት በመንገሱ ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚደረጉ በረራዎች የተሰረዙ ሲሆን ሀገራትም ዜጎቻቸውን በማስጠንቀቅ ላይ ናቸው። በቤሩት የሚገኘው የኢትዮጵያ የቆንስላ ጄኔራል ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፤ በሊባኖስ እና በቀጠናው ያለው ወቅታዊ የፀጥታ ስጋት እና ውጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ መምጣቱን አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ደህንነት ለማስጠበቅ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመሆን በትኩረት እየተከታተለ መሆኑን ገልጿል። በዚህም መሰረት ኢትዮጵያውያን ጥንቃቄ እንዲያደርጉና…
Read More