New admin

1125 Posts
የቲንክ ያንግ ኮዲንግ ስኩል ስልጠና በድጋሜ ሊጀምር እንደሆነ ተገለጸ

የቲንክ ያንግ ኮዲንግ ስኩል ስልጠና በድጋሜ ሊጀምር እንደሆነ ተገለጸ

ቲንክ ያንግ (ThinkYoung) እና ቦይንግ (Boeing) ለሁለተኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው 20ኛው የThinYoung Codeing School ምዝገባ መጀመሩን አስታውቀዋል። መርሃ ግብሩ ከሀምሌ 7 እስከ 10 ቀን 2015 ዓ. ም የሚካሄድ ሲሆን እድሜያቸው ከ9-18 ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ነፃ የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ ትምህርት ይሰጣል ተብሏል። የቲንክ ያንግ ኮዲንግ ትምህርት ቤት ሥርዓተ ትምህርት በባለሙያዎች የተመቻቹ ሮቦቲክስ እና ሮቦቲከስን  ጨምሮ የተለያዩ ተግባራትን የሚሽፍን ይሆናል። በተጨማሪም የቦይንግ ተወካዮች በአቪዬሽን እና በሌሎች የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ መስኮች ተነሳሽነትን ለመፍጠር ልምዳቸውን ለተሳታፊዎች እንደሚያካፍሉ ተገልጿል። እንዲህ ባለው የቲንክ ያንግ እና በቦይንግ አጋርነት በመሰል ኮዲንግ ትምህርት ላይ በተሳተፉ ከ1,300 በላይ ወጣቶች ህይወት ላይ በጎ ተጽዕኖ ያሳድረ ሲሆን በቀደሙት ዙሮች ውስጥ…
Read More
ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

በኮንስትራክሽን ሥራ የሚሰማሩ 50 ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ወደ ጀርመን ከማቅናታቸው በፊት አዲስ አበባ ባለው የጀርመን ኢንስቲትዩት ተጨማሪ ስልጠናዎችን በመውሰድ ላይ ናቸው፡፡ በኮንስትራክሽን ሥራ ለመሠማራት የሚያበቃቸውን ሥልጠና ያጠናቀቁ የመጀመሪያው ዙር ባለሙያዎች ወደ ጀርመን እንደሚሄዱ ተገልጿል፡፡ ሥልጠናቸውንና ፈተናቸውን አጠናቀው ጀርመን ከሚገኙ አሠሪዎቻቸው ጋር የሥራ ውል የተፈራረሙት የመጀመሪያዎቹ ተጓዦች በመጪው አንድ ወር ውስጥ  ጉዞ እንደሚያደርጉ ተሰምቷል።  ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በሲቭል ኢንጂነሪንግ፣ በኮንስትራክሽን ማናጅሜንት ቴክኖሎጂ፣ በአርክቴክቸርና መሰል ሙያዎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ምሩቃን ወጣቶች ጎኤቴ በመባል በሚታወቀው የጀርመን ባህልና ቋንቋ ኢንስቲትዩት ሥልጠናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሥምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ንጉሡ ጥላሁን እንዳሉት ሥልጠናው ከሦሥት ዓመት በፊት በቀድሞው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር…
Read More
ኢትዮጵያ የሂዩማን ራይትስ ዋች ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የሂዩማን ራይትስ ዋች ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ ሂዩማን ራይትስ ዋች በትግራይ ክልል ተፈጸመ በሚል ያወጣውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርት እንደማትቀበለው አስታውቃለች። በፌደራል መንግስቱ እና በትግራይ ሀይሎች መካከል የሰላም ስምምነት ቢፈረምም አሁንም በትግራይ ምዕራባዊ አካባቢዎች የሚካሄደው የዘር ማጽዳት ወንጀል መቀጠሉንና የሰብአዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ አካላትም ለፈጸሙት ግፍ ተጠያቂ አልተደረጉም በማለት ሂዩማን ራይት ወች ከሰሞኑ ያወጣውን ሪፖርት አስመልክቶ መንግስት ምላሽ ሰጥቷል፡፡ መንግስት በምላሹም ሪፖርቱ በአንዳንድ አካባቢዎች ጉልህ የሆኑ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መፈጸማቸውን የሚገልጽ መሰረተ ቢስ ሪፖርት ነው ሲል ተችቷል። አክሎም በሰሜኑ ኢትዮጵያ ክፍል የነበረው ግጭት በርካታ አካባቢዎችን ለጉዳት ያጋለጠ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ የተወሰነ አካባቢን መርጦ ደጋግሞ ሪፖርት በማዘጋጀት በሰብዓዊ መብት አጀንዳ ሽፋን የተለየ የፖለቲካ ተልዕኮዉን ለማሳካት ዓላማ ያደረገ…
Read More
የጸጋ በላቸው ጠላፊ በቁጥጥር ሥር ዋለ

የጸጋ በላቸው ጠላፊ በቁጥጥር ሥር ዋለ

የዳሽን ባንክ ሐዋሳ ቅርንጫፍ ባልደረባ የሆነችውን ጸጋ በላቸው በማገት ወንጀል የተጠረጠረውና ክትትል ሲደረግበት የቆየው ዋና ሳጂን የኋላ መብራት በቁጥጥር ሥር መዋሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፤ ግለሰቡ የጸጥታ ኃይሉ ባደረገው ክትትል፤ ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት ከ40 ደቂቃ ላይ በሀገረ ሰላም ወረዳ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ገልጿል። የጸጥታ ኃይሉ ቀደም ሲል ተበዳይዋን ከጠላፊው ማስጣል መቻሉን ያስታወሰው የሰላምና ጸጥታ ቢሮው፤ በወቅቱ ያመለጠው ተጠርጣሪው ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን፤ በሻፋሞ ጫካ ለጫካ ሲዘዋወር እንደነበረ መቆየቱን ተገልጿል። በዚህም ተጠርጣሪው አካባቢ በመቀየር ፍለጋውን አስቸጋሪ ማድረጉ የተገለጸ ሲሆን፤ ማህበረሰቡን በማሳተፍ በተደረገው አሰሳ በዛሬው ዕለት በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተመላክቷል። ተጠርጣሪው ግለሰብ ወንጀሉን ለመፈጸም ሲጠቀምባቸው…
Read More
ኢትዮጵያ ለ2016 ነዳጅ ግዢ ከአራት ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

ኢትዮጵያ ለ2016 ነዳጅ ግዢ ከአራት ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

ኢትዮጵያ በ2016 ዓ.ም 4 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ ከውጭ ለማስገባት ማቀዷን አስታውቃለች። የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት እንዳስታወቀው ለ2016 ዓ/ም ወደ አገር ለማስገባት ለታቀደው 4.3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ 4.4 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ። ኢትዮጵያ በ2016 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋትን ነዳጅ ለማስገባት የወጣውን ዓለም አቀፍ ጨረታ፣ " ቪቶል " የተባለው የባህሬን ኩባንያ በድጋሚ በማሸነፉ የኮንትራት ውል ስምምነት ተፈርሟል፡፡ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት በ2016 ዓ.ም. ለማስገባት ያቀደውን ሙሉ ለሙሉ ቤንዚን፣ እንዲሁም ከጠቅላላው የነጭ ናፍጣ ግዥ 40 በመቶውን " ቪቶል " ኩባንያ እንደሚያስገባ ታውቋል፡፡ በስምምነቱ መሠረት ለ1 ዓመት የሚያስፈልገውን 760 ሺሕ ሜትሪክ ቶን ቤንዚንና 1.2 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነጭ ናፍጣ ኩባንያው ያቀርባል ተብላል፡፡…
Read More
ከፊሊፒንስ ጋር የተጣላችው ኩዌት ኢትዮጵያዊያንን እንደምትቀጥር ገለጸች

ከፊሊፒንስ ጋር የተጣላችው ኩዌት ኢትዮጵያዊያንን እንደምትቀጥር ገለጸች

በነዳጅ የበለጸገችው የመካከለኛው መስራቅ ሀገር ኩዌት የሦስት ወራት አስገዳጅ ስልጠና የወስዱ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ለመቀበል ከመንግሥት ጋር ስምምነት ላይ መድረሷ ተገልጿል። በኢትዮጵያ እና ኩዌት መንግሥታት በኩል መግባባት ላይ መደረሱን ተከትሎም፤ በጥቂት ቀናት ውስጥ የጋራ የሥራ ስምምነት እንደሚፈረም አረብ ታይምስ ዘግቧል። ከስምምነቱ በኋላ በኢትዮጵያ የሚገኙ 600 የሚሆኑ የሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች የሰው ኃይል በማቅረብ ይሰራሉም ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያን ሰራተኞች ቢያንስ ብቃቱ ከተረጋገጠ ተቋም የ3 ወር ስልጠና መውሰድ በግዴታ ተጥሎባቸዋል፡፡ ኩዌት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የቤት ሰራተኞች የምታገኘው ከፊሊፒንስ ሲሆን፤ በኹለቱ አገራት መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ አገሪቱ የሰራተኛ እጥረት በማጋጠሙ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ለመቀበል ማቀዷ ተገልጿል። የኢትዮጵያ መንግሥት ከኩዌት መንግሥት ጋር በተስማሙት መሰረት፤ አንድ ሰራተኛ በወር 90…
Read More
በአዲስ አበባ አንዋር መስጅድ የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ

በአዲስ አበባ አንዋር መስጅድ የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ

በአዲስ አበባ መርካቶ አካባቢ ባለው አንዋር መስጅድ ዛሬ ምሳ ሰዓት አካባቢ የጸጥታ ችግር መከሰቱ ይታወቃል። ለአርብ ወይም ጁመዓ ጸሎት በስፍራው የነበሩ የእስልምና እምነት ተከታዮች እንዳሉን ከሆነ የሶላት ስነ ስርዓቱ ተጠናቆ ወደ ውጪ እየወጡ እያለ ከጸጥታ ሀይሎች ጥይት መተኮሱን ተከይሎ በአካባቢው ችግር ተፈጥሯል። ለደህንነቱ በመፍራት ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የአይን እማኝ ለአልዐይን እንዳለው " በአንዋር መስጅድ የጁመዓ ስግደትን ስግደት ጨርሰን ወደ ውጪ እየወጣን እያለ ፖሊሶች ጥይት ተኮሱ፣ ከዚያም ሰዎች መውደቅ እና መጮህ ጀመሩ" ሲል ነግሮናል። "አጠገቤ የነበሩ ሁለት ሰዎች እጅ እና እግራቸውን በጥይት ተመተው ሲወድቁ አይቻለሁ" ያለን ይህ የአይን እማኝ እኔ ወደ መስጅዱ ተመልሼ በመግባቴ ተርፌያለሁ ሲልም የአይን እማኙ አክሏል። "ምንም አይነት…
Read More
በባለስልጣን ጠባቂ ወታደር የተጠለፈችው የባንክ ሰራተኛ እስካሁን ያለችበት አልታወቀም

በባለስልጣን ጠባቂ ወታደር የተጠለፈችው የባንክ ሰራተኛ እስካሁን ያለችበት አልታወቀም

የዳሽን ባንክ ሐዋሳ ቅርንጫፍ ባለሙያ የሆነችው ፀጋ በላቸው በሐዋሳ ከንቲባ ጠባቂ ኮንስታብል የኋላመብራት ወልደማርያም መጠለፏ ተገልጿል። የሲዳማ እና ደቡብ ክልል ዋና ከተማ በሆነችው ሀዋሳ ከተማ ይህ መፈጸሙ ብዙዎችን ያስደነገጠ ድርጊት ሆኗል። ባለሙያዋ በሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ፀጋዬ ቱኬ የግል ጠባቂ ኮንስታብል የኋላመብራት ወ/ማሪያም ተጠልፋ ከተወሰደች ከሳምንት በላይ ሆኗታል። የተጎጂዋ ቤተሰቦች እንዳሉት የግል ተበዳይ በቤተ ክርስቲያን ደንብ መሰረት የጋብቻ ትምህርት ከወደፊት የትዳር አጋሯ ጋር ተምረው በማጠናቀቅ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ ለመጋባት ቀን ቆርጠው የቤት ዕቃዎችን በማሟላት ላይ ነበሩ። ይሁን እንጂ ጥቃት አድርሷል በሚል በፖሊስ የሚፈለገው ተጠርጣሪ የግል ተበዳይን በተደጋጋሚ ይዝትባት እና ያስፈራራት እንደነበር ቤተሰቦቿ ተናግረዋል። የግል ተበዳይ ቤተሰቦች ፀጋ ያለችበትን ባለማወቃቸው ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ…
Read More
የተመድ ፈንጅ አምካኝ ቢሮ በትግራይ ክልል ቢሮ ሊከፍት መሆኑን አስታወቀ

የተመድ ፈንጅ አምካኝ ቢሮ በትግራይ ክልል ቢሮ ሊከፍት መሆኑን አስታወቀ

በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት የሰላም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ መቆሙ ይታወሳል፡፡ በዚህ ጦርነቱ ምክንያት ተቋርጠው የነበሩ አገልግሎቶች ወደ ነበሩበት እንዲገቡ የማድረግ ስራ በፌደራል እና ክልል መንግስታት እየተሰራም ይገኛል፡፡ ይሁንና በጦርነቱ ወቅት በየቦታው ተቀብረው የነበሩ ፈንጂዎች ትምህርትን እና ሌሎች አገልግሎቶችን ማስቀጠል አልቻሉም ተብሏል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት (UNMAS ትግራይ ክልልን ጨምሮ በሰሜን ኢትዮጵያ ቦታዎች ያሉ ፈንጂዎችን እና ሌሎች የጦር መሣሪያ ቅሪቶችን የማስወገድ ተልዕኮ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት ፈቃድ ተሰጥቶታል ተብሏል፡፡ እንደ አፍሪካ ህብረት መግለጫ ከሆነ ፈንጂዎችና ሌሎች ያልፈነዱ የጦር መሣሪያ ቅሪቶች ጦርነት በተካሄደባቸው የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች፣ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት እያደረሱ በመሆኑ አካባቢዎችን ከፈንጂዎች ለማጽዳት እንዲቻል፣ የተመድ ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት በመሰማራት…
Read More
ኢትዮጵያን የጉዛራ ቤተ መንግሥት በ35 ነጥብ ስምንት ሚሊየን ብር ጥገና ሊደረግለት ነው

ኢትዮጵያን የጉዛራ ቤተ መንግሥት በ35 ነጥብ ስምንት ሚሊየን ብር ጥገና ሊደረግለት ነው

በዓለም ቅርስነት የተመዘገበው በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚገኘው የጉዛራ ቤተመንግሥት ከተደቀነበት የመፍረስ አደጋ ለመታደግ፤ ከፌደራል መንግሥት በተበጀተ 35 ሚሊዮን 800 ሺሕ ብር በጀት የጥገና ሥራው በዛሬው ዕለት እንደሚጀመር ተገልጿል። የጥገና ሥራው በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የጎንደር ዙሪያ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት የቅርስ ጥበቃና ቱሪዝም ልማት ቡድን መሪ ግርማቸው ሙሉጌታ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። ጉዛራ ቤተመንግሥት በጣና ተፋሰስ አካባቢዎች የሚገኝ የመጀመሪያው ቤተመንግሥት እንደሆነ ይነገራል። ጉዛራ ቃሉ የግዕዝ ሲሆን፤ ትርጉሙም ምቹ ማለት ነው። በጎንደር የነገሥታት ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን የጉዛራን ቤተመንግሥት የመሰረቱትም ያሳነፁትም ኢትዮጵያን ከ1556-1589 ድረስ በመሩት በአፄ ሰርፀ ድንግል መሆናቸው በፁሁፍ የሰፈሩ ማስረጃዎች ያሳያሉ። የጉዛራ ቤተመንግሥት ከእንፍራንዝ በስተደቡብ 5 ኪሎሜትር ወጣ ብሎ የተሰራ…
Read More