Business

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያቋረጠችውን እርዳታ ልትጀምር መሆኗን ገለጸች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያቋረጠችውን እርዳታ ልትጀምር መሆኗን ገለጸች

የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ከመጪው ወር ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ የምግብ እርዳታ አጀምራለሁ ብሏል፡፡ የአሜሪካ  መንግስት የዓለም አቀፍ ልማት ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) ካሳለፍነው ሰኔ ወር ጀምሮ በምግብ እርዳታ ስርቆት ምክንያት እርዳታ መስጠቱን ማቆሙ ይታወሳል፡፡ በለጋሾች የተገዛ የምግብ እርዳታ ለገበያ መቅረቡና ወደ ውጪ አገራት ጭምር መላኩን የጠቀሰው የተራድኦ ድርጅቱ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የእርዳታ ስርጭቱን በተመለከተ ተከታታይ ውይይት ማድረጉን ገልጿል። በዚህም ባለፈው ወር በሀገሪቱ ለሚገኙ ስደተኞች የምግብ እርዳታ ማቅረብ የጀመረ ሲሆን ከመጪው ወር ጀምሮ ደግሞ በመላው ኢትዮጵያ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች እርዳታ ማቅረብ እንደሚጀምር ገልጿል። ኢትዮጵያ የምግብ ድጋፍ ስርጭት ስርአቷን በመሰረታዊነት የሚያስተካክል ስራ መከወኗንና ለጋሽ ድርጅቶች እርዳታው ለተገቢው አካል መድረሱን እንዲከታተሉ መስማማቷን ድርጅቱ አስታውቋል። ለጋሽ…
Read More
ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ጥምረትን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ተገለጸ

ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ጥምረትን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ተገለጸ

ከ24 ዓመት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን የኢኮኖሚ ትስስር ለማሳለጥ የተቋቋመው የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ ጥምረት በየጊዜው አዳዲስ አባላትን በመሳብ ላይ ይገኛል። ጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ከአንድ ዓመት በፊት ይህን ጥምረት ለመቀላቀል በይፋ መጠየቋ ይታወሳል። ጥምረቱም የመቋዲሾን ጥያቄ ለመመለስ ባለሙያዎቹን አሰማርቶ የተለያዩ ግምገማዎችን ሲያደርግ ቆይቶ ሶማሊያን ስምንተኛዋ አባል ሀገር አድርጎ እንደሚቀበል አስታውቋል። ዋና መቀመጫውን አሩሻ ታንዛኒያ ያደረገው ይህ የኢኮኖሚ ጥምረት በሚቀጥለው ሳምንት በሚያደርገው ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ሶማሊያን በይፋ በአባልነት እንደሚቀበል ገልጿል። የጥምረቱ ዋና ጸሀፊ ፒተር ማቱኪ በሞሮኮ ማራካሽ በተካሄደው የኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ እንዳሉት "ሶማሊያ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ አባል ትሆናለች" ብለዋል። ዋና ጸሀፊው አክለውም "የጥምረቱ ቀጣይ አባል ሀገር ኢትዮጵያ ልትሆን ትችላለች፣ ኢትዮጵያ…
Read More
ኢትዮጵያ ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ማምጠቂያ ጊዜን አራዘመች

ኢትዮጵያ ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ማምጠቂያ ጊዜን አራዘመች

ኢትዮጵያ ETRSS-02 የሚል ስያሜ የተሰጣትን ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት በወራት ውስጥ እንደምትመጥቅ ተገልጾ የነበረ ቢሆንም መራዘሙ ተገልጿል፡፡ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከሶስት ወራት በፊት በሰጠው መግለጫ በቅርቡ ሶስተኛዋን ሳተላይት አመጥቃለሁ ሲል ገልጾ ነበር፡፡ ይሁንና ETRSS-02 የተሰኘችው ሳተላይት በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥ እንደምትመጥቅ አስታውቋል፡፡ ከዚህ በፊት በቻይና አጋዥነት ወደ ሕዋ የመጠቁት ሳተላይቶች የተቀመጠላቸውን የአገልግሎት ጊዜ በመጨረስ ተልዕኳቸውን በስኬት ማጠናቀቃቸውም ኢንስቲትዩቱ ገልጿል። የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ፤ ሶስተኛውን ሳተላይት መምጠቅን በተመለከተ መንግስት የፋይናንስና የኢኮኖሚ አዋጪነት ጥናት ማድረጉን ገልጸዋል። ጥናቱ ከዚህ በፊት ወደ ሕዋ ከመጠቁት ሳተላይቶች ተሞክሮ በመውሰድ የቀጣዩን ሳተላይት መረጃ ከመጠቀም አልፎ ሌሎች ተልዕኮዎችን በግልጽ ማስቀመጡንም አመልክተዋል። የሳተላይቱን ጨረታ…
Read More
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በትግራይ የቴሌኮም አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በትግራይ የቴሌኮም አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ

ሳፋሪኮም በትግራይ ክልል የኔትወርክ እና መሠረት ልማት ዝርጋታ በሚቀጥሉት ሳምንታት እንደሚጀምር ገልጿል ከሁለት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ የገባው ሳፋሪኮም ከትግራይ ክልል ውጪ በመላው አገሪቱ የቴሌኮም አገልግሎቱን ለደንበኞቹ ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ምክንያት የቴሌኮም አገልገሎቱን ማቅረብ ያልቻለው ይህ ኩባንያ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ አገልግሎት እጀምራለሁ ብሏል፡፡ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሔለፑት ወደ ትግራይ ክልል አምርተው ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳድር አመራሮች ጋር መምከራቸውን ድርጅቱ በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡ በሚቀጥሉት ሳምንታት በትግራይ ክልል የኔትወርክ እና የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ለማካሄድ በሚያስችለውን ውይይት ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር አድርጓል፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው እና ሌሎች ሰራተኞች ወደ መቀሌ ከተማ ተጉዘው ከጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው…
Read More
በኢትዮጵያ የአህያ ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ መሆኑ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የአህያ ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ መሆኑ ተገለጸ

በአህያ ደህንነት ዙሪያ የሚሰራው ብሩክ ኢትዮጵያ የተሰኘው የእንስሳት መብት ተሟጋች ድርጅት የአህያ ቁጥር እየቀነሰ መሆኑን ገልጿል፡፡ ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ የአህያ ስጋን ወደ ውጪ ሀገራት መላክ የተጀመረ ሲሆን ዓላማውም የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት እንደሆነ ይገለጻል፡፡ በዚህ የአህያ እርድ3 እና ንግድ ምክንያት የአህያ ቁጥር እየቀነሰ መምጣቱን እና ይህም እንዳሳሰበው ብሩክ ኢትዮጵያ የተሰኘ የአህያ መብት ተሟጋች ድርጅት አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ አህያ እንዲታረድ እና ስጋና ቆዳው ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መደረጉ እንደ አገር የአህያ ቁጥር እየተመናመነ እንዲመጣ ማድረጉን የብሩክ ኢትዮጵያ ድርጅት አማካሪ ይልማ አበበ ለመናኃሪያ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ በኢትጵያ የአህያ እርድ በቻይና ባለሃብቶች በመስፋፋቱ ለአገር የውጭ ምንዛሪን ቢያስገኝም፤ እንደ አገር የአህያ መኖር ከጊዜ ወደ ጊዜ አሳሳቢ ደረጃ ላይ…
Read More
አየርላንድ ለኢትዮጵያ የምግብ ደህንነት 8.4 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ተስማማች

አየርላንድ ለኢትዮጵያ የምግብ ደህንነት 8.4 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ተስማማች

የገንዘብ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስቴር እና የአየርላንድ መንግሥት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። የ8 ሚሊየን 400 ሺሕ ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የፈረሙት የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ እና የአየርላንድ የዓለም አቀፍ ልማትና ዳያስፖራ ሚኒስትር ዴዔታ ሾን ፍሌሚንግ ናቸው፡፡ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱ ሦስት ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ የመጀመሪያው 5 ሚሊየን ዩሮ ለሴፍቲ ኔት ፕሮግራም እንዲሁም 3 ሚሊየን ዩሮ በጤና ላይ ያተኮሩ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለመደገፍ እንደሚውል ተገልጽልል። እንዲሁም 400 ሺሕ ዩሮ ደግሞ ለአገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሐ-ግብር ድጋፍ እንደሚውል በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ ከፊርማ ሥነ- ሥርዓቱ በኋላ የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ባደረጉት ንግግር፤ አየር ላንድ ለኢትዮጵያን የልማት ሥራዎች ቀጣይነት እያደረገችው ላለው ድጋፍ አመስግነዋል፡፡ ሦስቱም ስምምነቶች በመንግሥት…
Read More
ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ሙስና ፈጽመዋል የተባሉ 42 ተጠርጣሪዎች ታሰሩ

ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ሙስና ፈጽመዋል የተባሉ 42 ተጠርጣሪዎች ታሰሩ

የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሰራተኞች ህዝብን ከማማረራቸው ባለፈ ለውጭ ሀገራት ዜጎች ፓስፖርት ሲሰጡ ነበርም ተብሏል፡፡ በሙስና ተጠርጥረው በፖሊስ ከታሰሩ ሰዎች መካከል የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተሩ ይገኙበታል፡፡ 42 የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሰራተኞች ባሳለፍነው ሰኞ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ የመንግሥት አስተዳደር ለውጥ ከተደረገ ጀምሮ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ተቋም ውስጥ የተለያዩ ለውጦች (ሪፎርም) የተደረገ ቢሆንም፣ አንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች በድለላ ሥራ የተሰማሩ አካላት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ ናቸው ተብሏል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ ፓስፖርት ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን መንገላታታቸውን ተከትሎ የተቋሙን አመራሮች ከስልጣን አግደው ነበር፡፡ ሰላማዊት ዳዊት ደግሞ…
Read More
ኢትዮጵያ ያቀረበችው የባህር በር ጥያቄ በጎረቤት ሀገራት ውድቅ ተደረገ

ኢትዮጵያ ያቀረበችው የባህር በር ጥያቄ በጎረቤት ሀገራት ውድቅ ተደረገ

ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስት አብይ አህመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የህዝቧን የመልማት ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት የባህር በር ያስፈልጋታል ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ የጣላቁ ህዳሴ ግድብን ስትገነባ ጉዳዩ ያሳሰባቸው ሀገራት ጠይቀዋል፣ እኛም የባህር በር እንዲኖረን መጠየቅ አለብን ሲሉም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል ያበሉ እንጂ ስለየትኛው የባህር በር ግን ስም አልጠቀሱም ነበር፡፡ ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ጎረቤት የሆኑት እና የባህር በር ያላቸው ኤርትራ፣ ጅቡቲ እና ሶማሊያ ሲሆኑ ሶስቱም ሀገራት የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ውድቅ አድርገዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ አስቀድሞ መግለጫ ያወጣው የኤርትራ መንግስት ሲሆን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ባወጣው መግለጫ ሀገሪቱ ሀብቷን ለማንም አሳልፋ እንደማትሰጥ፣ እስካሁንም የተጀመረ ምንም…
Read More
ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ ኤሌክትሪክ ሀይል እንደምትሽጥ ገለጸች

ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ ኤሌክትሪክ ሀይል እንደምትሽጥ ገለጸች

የኤሌክትሪክ ኃይል በተያዘው ዓመት ከሀገር ውስጥ እና ለውጭ ሀገራት ከተሸጠ የኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ 30 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በተያዘው በጀት ዓመት ሁለት ሺህ ከ993 በላይ ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት ይደረጋል፡፡ ለሦስት ጎረቤት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማለትም ለሱዳን፤ ኬንያ እና ጅቡቲ 2 ሺህ 993 ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት በማድረግ 182 ሚሊዮን ዶላር ወይም 10 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል፡፡ ለሀገር ውስጥ ደንበኞች በሚሸጥ የኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ 20 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት መታቀዱንም አቶ ሞገስ ተናግረዋል፡፡ ባሳለፍነው የ2015 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ እና ለጎረቤት ሀገራት…
Read More
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ቻይና አመሩ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ቻይና አመሩ

የቻይና ቤልት ኤንድ ሮድ ዓመታዊ ጉባኤ ከሁለት ቀናት በኋላ በቤጂንግ ይካሄዳል፡፡ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን ጨምሮ በርካታ የዓለማችን መሪዎች በዚህ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ቤጂንግ በማምራት ላይ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በዚሁ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ቻይና ማምራታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ ቻይና ለኢትዮጵያ ብድር ከሚሰጡ ሀገራት መካከል ዋነኛዋ ስትሆን በተለይም ለኤርፖርት ማስፋፊያ፣ ለመንገድ እና ለደረቅ ወደብ ልማት ግንባታዎች በቻይና ብድር ተገንብተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በጦርነት እና በኮሮና ቫይረስ መጎዳቱን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት የብድር ጫና ውስጥ በመግባቱ የብድር መክፈያ ጊዜ እንዲራዘምለት በመጠየቅ ላይ ነው፡፡ ቻይና የኢትዮጵያን የብድር መክፈያ ጊዜ በአንድ ዓመት ማራዘሟ የተገለጸ ሲሆን ከዓለም ባንክ…
Read More