ዜና

ኢትዮጵያ የሳሞአ ስምምነትን እንድትሰርዝ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠየቀ

ኢትዮጵያ የሳሞአ ስምምነትን እንድትሰርዝ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠየቀ

የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ እንዳስታወቀው ኢትዮጵያ በአውሮፓ ኅብረት፣ አፍሪካ፣ ካሪቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት መካከል የተፈረመውንና የሳሞአ ስምምነት በመባል የሚታወቀውን የንግድና የኢኮኖሚ አጋርነት ስምምነትን ውድቅ እንድታደርግ ጠይቋል፡፡ ተቋሙ ይህ ስምምነት የተጠቀሰው የወሲብና የስነ ተዋልዶ ጤና እና መብቶች በሚል ዘርፍ የተደረገው ስምምነት ከግብረሰዶም መብቶች፤ ከፆታ መቀየር፤ ከጽንስ ማቋረጥ እንዲሁም የወሲብ ንግድን የሚያበረታታ እንደሆነ አስታውቋል፡፡ በስምምነቱ የአፍሪካ ፕሮቶኮል አንቀፅ 40.6 ላይ በአህጉሪቱ ለሚገኙ ልጆችና ታዳጊዎች ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርት የተባለ እጅግ አደገኛ ልቅ የወሲብ ትምህርት እንዲማሩ የሚያስገድድ በመሆኑ እንደሚቃወመውም ገልጿል፡፡ ሌላኛው ተቋሙ የተቃወመው የፆታ ትንኮሳን ማስቀረት በሚል የተቀመጠው ይዘት በጣም አሻሚ የሆነ ግብረሰዶማዊ አስተሳሰቦችን ለማስረፅ እንዲረዳው በሰነዱ በበርካታ ክፍሎች ውስጥ " አካታች "…
Read More
አሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ በኢትዮጵያ ቢሮውን እንደሚከፍት አስታወቀ

አሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ በኢትዮጵያ ቢሮውን እንደሚከፍት አስታወቀ

ድርጅቱ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በአፍሪካና በምስራቅ አውሮፓ ሀገራት ውስጥ 30 ወኪል ቢሮዎችን እከፍታለሁ ብሏል፡፡ ሪቭኤክሴል እና አሜሪካን ሆስፒታል ዱባይ ከሰሃራ በታች ባሉ ሀገራት የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ስትራቴጂያዊ አጋርነትን እንደፈጠሩ አስታውቋል፡፡ አሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ በአፍሪካና ምስራቅ አውሮፓ 30 ወኪል ቢሮዎችን የመክፈት ዕቅዱን ያስጀመረ ሲሆን በዱባይ ጤና ባለስልጣን ዕውቅና ያላቸው 3 የህክምና ቱሪዝም ቢሮዎችን በናይጄርያ የተለያዩ ከተሞች ከፍቷል፡፡ በዓለምአቀፍ የንግድ መፍትሄዎች መሪ ተዋናይ የሆነው ሪቭኤክሴል ዓለምአቀፍ ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራትን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለማሳደግ ያለውን ቁርጠኝነት በማጠናከር ከአሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ ጋር የለውጥ ስትራቴጂያዊ አጋርነቱን በይፋ አሳውቋል፡፡ የአሜሪካን ሆስፒታል-ዱባይ ይህንን ያረጋገጠው በ30 ወሳኝ የአፍሪካና የምስራቅ አውሮፓ ከተሞች የወኪል ቢሮዎች የማስፋፍያ ዕቅዱ አካል ሆኖ በናይጄርያ…
Read More
ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ

ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ

የትግራይ ክልል የቀድሞ ፕሬዝዳንት ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ:: ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ኢትዮጵያ ለዓመታት ወደ ጦርነት እንድተገባ የተገደደችበትን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን እዝ እሳቸው የሚመሩት የትግራይ ልዩ ሀይል እንዲያጠቃ ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን የተገደሉበት እና 28 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ ንብረት የወደመበት ይህ ጦርነት ከአንድ ዓመት በፊት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ቆሟል፡፡ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በዛሬው ዕለት ከአራት ዓመት በኋላ ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ሲሆን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተዋል፡፡ ደብረጽዮን እና ሌሎች የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ኃላፊዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር በአዲስ አበባ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም…
Read More
በኢትዮጵያ የሚገኘው ባለ ጥቁር ጎፈር አንበሳ የመጥፋት አደጋ ተጋርጦበታል ተባለ

በኢትዮጵያ የሚገኘው ባለ ጥቁር ጎፈር አንበሳ የመጥፋት አደጋ ተጋርጦበታል ተባለ

የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን እንዳስታወቀው የኢትዮጲያው ጥቁር ጎፈር አንበሳ ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥሩ እየተመናመነ በመምጣቱ የመጥፋት አደጋ ተጋረጦበታል ተብሏል፡፡ በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት ህገወጥ ዝውውር ቁጥጥር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ዳንኤል ጳውሎስ እንደተናገሩት ህገወጥ የነዋሪዎች ሰፈራ፣ የደን ጭፍጨፋ መኖር፣ የእርሻ ስራ እና  ግጦሽ  መበራከት የእንስሳቶቹ ስፍራ እንዲወድም ያደረጉ ዋና ዋና ምክንያቶች ናቸው። በዚህም አንበሳን ጨምሮ የዱር እንስሳት የሚፈልጉትን ምግብ እንዳያገኙና በምግብ ሰንሰለት ውስጥ ችግር እንዲፈጠር ብሎም ለህገወጥ አደን  በስፋት ተጋላጭ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል ሲሉ አክለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የተለየ የአንበሳ ዝርያ ነው ተብሎ የሚታወቀው እና የመጥፋት አደጋ ያጠላበት የጥቁር ጎፈር አንበሳ  ቆዳም በአብዛኛው  በኬንያ ፣በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን በኩል የህገወጥ ዝውውር …
Read More
አሜሪካ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ግድያ በገለልተኛ ወገን እንዲመረመር ጠየቀች

አሜሪካ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ግድያ በገለልተኛ ወገን እንዲመረመር ጠየቀች

ከአማራ ክልል ዋና ከተማ ከሆነችው ባህርዳር በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው መራዊ ከተማ ባሳለፍነው ሳምንት ከሰሞኑ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከባድ ውጊያ ተቀስቅሶ ነበር፡፡ በዚህ ውጊያ ምክንያት የፋኖ ታጣቂዎች የመራዊ ከተማን ተቆጣጥረው የነበረ ቢሆንም በኋላ ለቀው መሄዳቸውን ተከትሎ ወደ ከተማው የገባው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ50 በላይ የከተማዋ ነዋሪዎችን እንደገደሉ ቢቢሲ ነዋሪዎችን አነጋግሮ ዘግቧል፡፡ እንደ ነዋሪዎቹ አስተያየት ከሆነ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ነዋሪዎቹን ከመንገድ ላይ እና መኖሪያ ቤታቸው በማሰባሰብ ገድለዋቸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በኢምባሲው ማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ባወጡት መግለጫ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ዜጎች ግድያ እንደሚያሳስባቸው፣ ጉዳዩ በገለልተኛ አካል እንዲመረመር ጠይቀዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ እና ኦሮሚያ…
Read More
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በጸጥታ እና ዲፕሎማሲ ተቋማት ላይ የአመራር ሹም ሽር አደረጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በጸጥታ እና ዲፕሎማሲ ተቋማት ላይ የአመራር ሹም ሽር አደረጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አዳዲስ ሹመቶችን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው አጸድቀዋል፡፡ በዚህም መሰረት የብሔራዊ ደህንነት ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሲሆኑ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የቀድሞ አምባሳደር የነበሩት ታዬ አጽቀስላሴ ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነዋል፡፡ እንዲሁም ዶክተር መቅደስ ዳባ ደግሞ ከጤና ሚኒስትርነት ሀላፊነታቸው የመልቀቂያ ደብዳቤ ላሰገቡት ዶክተር ሊያ ታደሰ ምትክ ሆነው ተሾመዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የደህንነት አማካሪ የነበሩት ሬድዋን ሁሴን ደግሞ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይረክተር ተሹመዋል። አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሆነው ከመስራታቸው በፊት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኢታ፣በኤርትራ እና አየርላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል፡፡ ትዕግስት ሃሚድ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና…
Read More
አራት ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ባንኮች በኢትዮጵያ ለመሰማራት መፈለጋቸው ተገለጸ

አራት ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ባንኮች በኢትዮጵያ ለመሰማራት መፈለጋቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዳይሬክተር ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) በተቋሙ ስራ ዙሪያ በሰጡት መግለጫ ከየካቲት 4 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ዘርፍ መሰማራት ለሚፈልጉ የሀገር ውስጥ እና ውጭ ተቋማት ፈቃድ መስጠት ይጀመራል ብለዋል። "እስካሁን ባለው ሂደት በርካታ ኢትዮጵያዊያን እና የውጭ ኩባንያዎች በኢንቨስትመንት ባንክ ለመሰማራት ፍላጎታቸውን አሳይተውናል" ያሉት ዳይሬክተሩ "ሶስት በዓለም አቀፍ ደረጃ ስም ያላቸው የውጭ ሀገር ኢንቨስትመንት ባንክ እና ሁለት የሀገር ውስጥ ተቋማት ፈቃዱን ለማግኘት እየጠየቁን ነው" ሲሉም ተናግረዋል። ይሁንና ዋና ዳይሬክተሩ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ባንክ ለማቋቋም ፍላጎታቸውን የገለጹት ዓለም አቀፍ ባንኮች ስም ዝርዝር ከመናገር ተቆጥበዋል፡፡ ዋና መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደረገው እና በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ቅርንጫፍ ያለው ስታንደርድ ባንክ ባሳለፍነው…
Read More
ሱዳን የኢትዮጵያ 70 ሚሊዮን ዶላር የኤሌክትሪክ እዳ እንዳለባት ተገለጸ

ሱዳን የኢትዮጵያ 70 ሚሊዮን ዶላር የኤሌክትሪክ እዳ እንዳለባት ተገለጸ

ጎረቤት ሀገር ሱዳን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ከሚገዙ ሀገራት መካከል አንዷ ስትሆን ለዓመታት የተጠቀመችበትን እዳ አልከፈለችም ተብሏል፡፡ ሱዳን ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ የተጠቀመችበትን 70 ሚሊዮን ዶላር እዳዋን ባለመክፈሏ ምክንያትም የሚቀርብላት የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን በ50 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል፡፡ ካሳለፍነው ሚያዚያ ወር ጀምሮ በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ያለችው ሱዳን ከ8 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የተፈናቀሉ ሲሆን ኢትዮጵያ፣ ግብጽ  እና ቻድ ደግሞ ሱዳናዊያን የተጠለሉባቸው ሀገራት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ለጎረቤት ሀገራት ከሸጠችው የኤሌክትሪክ ሽያጭ 66 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 47 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የፌደራል ኤሌክትሪክ ሀይል አስታውቋል። ሱዳን ባለባት የጸጥታ ችግር ምክንያት ከዚህ በፊት የተጠቀመችበትን የኤሌክትሪክ ኃይል ክፍያ በወቅቱ መክፈል አለመቻሏ ለገቢው…
Read More
ብሪታንያ በኢትዮጵያ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለማቅረብ የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

ብሪታንያ በኢትዮጵያ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለማቅረብ የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

የብሪታንያ የአፍሪካ ልማት ዳይሬክተር በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ከጉብኝቱ በኋላ ድጋፉን አድርገዋል ተብሏል። ሚንስትሩ ከጉብኝታቸው በኋላ እንዳሉት አሳሳቢ የምግብ ዋስትና ችግር ያለባቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር በቀጣይ ወራት 10 ነጥብ 8 ሚሊየን ይደርሳክ ብለዋል። የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፉ ለሶስት ሚሊየን ሰዎች ህይወት አድን እርዳታ ለማቅረብ እንደሚውልም ተገልጿል። አስቸኳይ ድጋፉ በአልሚ ምግብና ሌሎች ወሳኝ ግብአቶች ምክንያት እየተከሰተ የሚገኘውን ሞት ለመቀነስ ለ75 የጤና ተቋማት የተለያዩ ድጋፎችን ለማቅረብ ነውም ተብሏል። የአውሮፓ ህብረት ከአንድ ወር በፊት በኢትዮጵያ በድርቅ እና ግጭቶች ለተፈናቀሉ ዜጎች 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል። በኢትዮጵያ በጦርነት እና ድርቅ ምክንያቶች ለእርዳታ የሚዳረጉ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ የመጣ በመምጣት ላይ ይገኛል።…
Read More
ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ 10 ቢሊዮን ዶላር ብድር መክፈሏ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ 10 ቢሊዮን ዶላር ብድር መክፈሏ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት በመሻሻል ላይ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) የመንግስታቸውን የስድስት ወራት አፈጻጸም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ጊዜ እንዳሌት “ህገ መንግስት ጋር ተያይዞ ከአማራ ክልል ለሚነሳው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሟል፤ ስራውን እየሰራ ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የአማራ ህዝብ በስራ ላይ ባለው ሕገ መንግስት ምክንያት ተንቀሳቅሶ መስራት፣ ሀብት ማፍራት ሌሎች የማንነት ጥያቄዎች እንዳይፈቱ አድርጓል የሚል ጥያቄ አላቸው፡፡ በዚህም መሰረት የአማራ ህዝብ ይህ በስራ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት ሲዘጋጅ እና ሲጸድቅ በቂ ውይይት እንዳልተደረገበት እንዲሁም የአማራ ህዝብን አግላይ ነው በሚል ጥያቄዎችን ሲያነሱ ቆይተዋል፡፡ ለአብነትም የአማራ ክልል ወሰን አከላለል ትክክል…
Read More