ዜና

ሀይኒከን ኩባንያ አራዳ ቢራን ጠቀለለ

ሀይኒከን ኩባንያ አራዳ ቢራን ጠቀለለ

የአራዳ መጠጥ ምርቶች አቅራቢ የሆነው ኮማሪ ቤቭሬጅ ለሃይኒከን መሸጡ ተገልጿል፡፡ በአጭር ጊዜ በተጠቃሚዎች ከፍተኛ ተቀባይነት ያገኘው የአራዳ መጠጦች አምራች ኮማሪ ፋብሪካውን ለሃይኒከን ለመሸጥ ሲያደርግ የነበረው ድርድር ከሳምንት በፊት አጠናቋል ተብሏል፡፡ የሽያጩ ድርድር ለበርካታ ወራት ሲደረግ ነበር የተባለ ሲሆን ሁለቱ ወገኖች በሀምሌ ወር ወደ መጨረሻ የድርድር ምእራፍ ቢሸጋገሩም ሀምሌ 22 ቀን 2016 ዓም ወደ ትግበራ የገባውን የምንዛሬ ገበያ ለውጥ ተከትሎ ድርድሩ በድጋሚ ሲደረግ እንደነበር ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ የሽያጩ ዋጋ በዚህ ወር መጨረሻ በይፋ ይገለጻል የተባለ ሲሆን ሁለቱ ወገኖች በዚሁ ወቅት በይፋ ፋብሪካውን እንደሚረካከቡ ተገልጿል፡፡ ኮማሪ ከአዲስ አበባ በሰሜን ምስራቅ 96 ኪሜ ርቀት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጨኬ አካባቢ በገነባው ፋብሪካ…
Read More
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ መንገድ ልጅ መውለድ ላልቻሉ ሰዎች አዲስ ህግ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ በተፈጥሮ መንገድ ልጅ መውለድ ላልቻሉ ሰዎች አዲስ ህግ አዘጋጀች

የዘር ፍሬ ልገሳን የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ “የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር ረቂቅ አዋጅ” በሚል ርዕስ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ አስራ ሁለት ክፍሎች ያሉት ረቂቅ አዋጁ ስለ አጠቃላይ የጤና አገልግሎት፣ ስለ ጤና አገልግሎት አሰጣጥ፣ ስለ ልዩ የጤና አገልግሎቶች፤ ስለ ጤና ዘርፍ የሰው ኃብት ልማት እና አስተዳደር፤ ስለ ጤና እና ጤና ነክ ተቋማት እንዲሁም የጤና ባለሙያዎች ቁጥጥርን የሚመለከቱ 60 አንቀጾች አሉት። ስለ ልዩ የጤና አገልግሎቶች የሚያወሳው የአዋጁ አራተኛ ክፍል ከዘረዘራቸው የጤና አገልግሎቶች መካከል አንዱ በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥነ ተዋልዶ ሕክምና አገልግሎት ነው። በዚህ ንዑስ ክፍል ሥር የተካተተው አንቀጽ “ፈቃድ የተሰጠው የጤና ተቋም በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥነ ተዋልዶ የሕክምና አገልገሎት ሊሰጥ ይችላል” ሲል ሕክምናው…
Read More
እንግሊዝ ለትግራይ ታጣቂዎች መልሶ ማቋቋሚያ 16 ሚሊዮን ፓውንድ እንደምትሰጥ ገለጸች

እንግሊዝ ለትግራይ ታጣቂዎች መልሶ ማቋቋሚያ 16 ሚሊዮን ፓውንድ እንደምትሰጥ ገለጸች

የብሪታኒያ የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጉብኝት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ ብሪታንያ መንግሥት ለኢትዮጵያ የ23 ሚሊየን ፓውንድ ድጋፍ እንደምታደርግ አስታውቃለች፡፡ ከዚህ ውስጥ 16 ሚሊዮን ፓውንዱ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት ከተሳተፉት ውስጥ የትግራይ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም የሚውል እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የእንግሊዝ መንግስት በኢትዮጵያ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ዘርፍን ለመደገፍ የሚውል እና ለሶስት አመታት የሚቆይ የ6 ነጥብ 9 ሚሊየን ፓውንድ ድጋፍ እንደሚያደርግም አስታውቋል፡፡ ድጋፉ ትግራይን ጨምሮ ለተለያዩ ክልሎች የሚውል ሲሆን 7000 የሚሆኑ ሴት ሰራተኞችን ህይወት ለማሻሻል እና የወጭ ንግድን 20 በመቶ ለማሳደግ ያለመ ነው ተብሏል። ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመታት በተካሄደው በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተሳተፉ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው ለመመለስ በጀት በማሰባሰብ ለይ ስትሆን የአውሮፓ ህብረት 12 ሚሊዮን…
Read More
ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ መደበኛ የስልክ አገልግሎት ተቋረጠ

ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ መደበኛ የስልክ አገልግሎት ተቋረጠ

በ2010 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ነበር ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ለ20 ዓመታት ተቋርጦ የነበረውን ግንኙነት ያደሱት፡፡ ሁለቱ ሀገራት የመደበኛ የስልክ አገልግሎትን ዳግም ካስጀመሩ ከሰባት ዓመታት በኋላ ተቋርጧል፡፡ ይህን ተከትሎም ከሐምሌ 2010 ዓ.ም ጀምሮ መደበኛ የስልክ አገልግሎት ሲሰራ የነበረ ሲሆን ከትናንት በስቲያ ማለትም ከመስከረም 28 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እንደተቋረጠ በኢትዮጵያ ከሚኖሩ ኤርትራዊያን ሰምተናል፡፡ ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ በኢትዮጵያ የሚኖሩ ኤርትራዊ ለአል-ዐይን እንዳሉት “ከማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መደበኛ ስልክ መደወል አልቻልኩም” ብለዋል፡፡ በኤርትራ ኢንተርኔት አገልግሎት ባለመኖሩ ምክንያት ቤተሰቦቻችንን የምናገኘው በመደበኛ ስልክ ብቻ ነበር የሚሉት እኝህ አስተያየት ሰጩ አገልግሎቱ መቋረጡ እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል፡፡ “ቀስ በቀስ የኢትዮጵያ እና…
Read More
የጣና ፎረም ጉባኤ ለሶስተኛ ጊዜ ተራዘመ

የጣና ፎረም ጉባኤ ለሶስተኛ ጊዜ ተራዘመ

በባህር ዳር ከተማ ሊካሄድ የነበረው 11ኛው የጣና ፎረም ለሶስተኛ ጊዜ ተራዝሟል፡፡ የአፍሪካ ሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ የሚመክረው እና በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ የሚካሄደው ዓመታዊው የጣና ፎረም ጉባኤ ለሶስተኛ ጊዜ ተራዘመ። 11ኛው ጉባኤ መጀመሪያ ሊካሄድ ቀን ተቆርጦለት የነበረው ባለፈው ዓመት ከጥቅምት 2-4 ቀን 2016 ዓ.ም ነበር። ሆኖም ጉባኤው “ባልተጠበቁ ሁኔታዎች ምክንያት” እንደተራዘመ የፎረሙ ጽህፈት ቤት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሰላም እና ደህንነት ጥናቶች ተቋም አስታውቆ ነበር። ጉባኤው ሚያዚያ ወር 2016 ዓ.ም. እንደሚካሄድ ጽህፈት ቤቱ በጊዜው አስታውቆ የነበረ ቢሆንም በተባለው ጊዜ ሳይካሄድ ለሁለተኛ ጊዜ ተራዝሟል። “አፍሪካ እየተሻሸለ በመጣው የዓለም ሥርዓት ውስጥ” የሚል መሪ ቃል የያዘው 11ኛው ጉባኤ ከጥቅምት 15-17 2017 ይካሄዳል…
Read More
አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

ላለፉት ዘጠኝ ወራት በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሲያገለግሉ የቆዩት አምባሳደር ታዬ የኢትዮጵያ ስድስተኛው ፕሬዝዳንት ሆነዋል 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡ ሁለቱ ምር ቤቶች በጋራ ባካሄዱት የመክፈቻ ስነ ስርዓትም አምባሳደር ታዬ አስጸቀስላሴ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት አድርጎ ሾሟል። የፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ የሥራ ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሹመዋል። አምባሳደር ፕሬዚዳንት ታዬም በምክር ቤቶቹ ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ የፈጸሙ ሲሆን ከቀድሞዋ ፕሬዚዳንት ሣለወርቅ ዘውዴ ጋር ሥራ እርክክብ አድርገዋል፡፡ አምባሳደር ታዬ፤ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓ መምሪያ የሥራ ክፍል ፣የምዕራብ አውሮፓ ዋና ክፍል ኃላፊ፣የኢንፎርሜሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር፣ስቶክሆልም የኢፌዲሪ ኤምባሲ በአማካሪነት፣በዋሽንግተን የኢፌዲሪ ኤምባሲ በአማካሪነት እንዲሁም…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቤይሩት እና ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቤይሩት እና ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ

ለፍልስጤም ነጻነት የሚታገለው ሐማስ በእራኤል ላይ ድንገተኛ ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ በመካከለኛው ምስራቅ የተጀመረው ጦርነት አንድ ዓመት ሞልቶታል፡፡ ይህ ጦርነት ወደ ሊባኖስ መስፋፋቱን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በርካታ ዓለማችን አየር መንገዶች ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚያደርጓቸውን በረራዎች አቋርጠዋል፡፡ ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ወደ ቤይሩት እና ወደ ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ በጊዜያዊነት ማቋረጡን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል። አየር መንገዱ በድረገ ገጹ ባጋራው መረጃ ተለዋጭ ማስታወቂያ እስከሚያወጣ ድረስ ወደ ቤይሩት የሚያደርጋቸውን ሁሉንም በረራዎች ማቋረጡን ገልጿል። ወደ ቴልአቪቭ ደግሞ እስከ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በረራ የማያደርግ መሆኑን ነው አየር መንገዱ የገለጸው። በተጠቀሱት አካባቢዎች ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን የጠቀሰው አየር መንገዱ፤ ስለጉዳዩ…
Read More
ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለአንድ ዓመት ዝም ብለው መቆየታቸው ተናገሩ

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለአንድ ዓመት ዝም ብለው መቆየታቸው ተናገሩ

ፕሬዝዳንቷ በX ወይም በቀድሞው ትዊተር ገጻቸው ላይ ባጋሩት ጽሁፍ ላይ "ዝምታ ነው መልሴ" የሚል ጽሁፍ አጋርተዋል። ለምን ዝም እንዳሉ በጽሁፋቸው ላይ ያልገለጹት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ " እነ ጥላሁን ገሰሰ፣ ቴዲ አፍሮ፣ አሊ ቢራ ፣ማህሙድ አክመድ ... ድንቅ ድምጻዊያን መካከል ናቸው። ሲሉም አክለዋል። ፕሬዝዳንቷ የማህሙድ አህመድ ዘፈንን በሚያስታውሰው "የሰው ልጅ ሆዱ ሲከፋው ጊዜም እንደሰው ሲገፋው፣ መሄጃ መውጫ ሲጠፋው ዝምታ ብቻ ነው ተስፋው" የሚለውን ግጥምም በጽሁፋቸው ላይ ጠቅሰው አጋርተዋል። ዝምታን "ለአንድ ዓመት ሞከርኩት" ያሉት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ምን ደርሶባቸው እንደከፋቸው፣ ለምን እንደከፋቸው እና ለምን ዝም እንዳሉ ከመጥቀስ ተቆጥበዋል። የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት በበኩሉ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ያጋሩት ጽሁፍ የግላቸው እንጂ የጽህፈት ቤቱ እንዳልሆነ ጠቅሷል። ኢትዮ…
Read More
ሶማሊያ ኢትዮጵያ ግድቦችን በመልቀቅ በውሃ እንድጥለቀለቅ እያደረገች ነው ስትል ከሰሰች

ሶማሊያ ኢትዮጵያ ግድቦችን በመልቀቅ በውሃ እንድጥለቀለቅ እያደረገች ነው ስትል ከሰሰች

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ኢትዮጵያ ሆን ብላ ጎርፍ እንዲፈጠር ውሃ እየለቀቀች ነው ሲሉ ከሰዋል፡፡ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሃሙድ ኢትዮጵያ “በሶማሊያ ጎርፍ እንዲከሰት ሆን ብላ ከግድቦቿ ውሃ እየለቀቀች ነው” ሲሉ  ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ ከዘኢኮኖሚስት ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ፤ በሶማሊያ በጎርፍ የተጥለቀለቁ አካባቢዎችን ፎቶግራፎች አቅርበው፤ አደጋው ኢትዮጵያ ሆን ብላ ያደረገችው ነው ሲሉ ከሰዋል። ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሃሙድ ኢትዮጵያ በድንበር አቅራቢያ “በጎሳ ለተመሰረቱ ለሶማሊያ ሚሊሻዎች ትጥቅ እያስተላለፈች ነው” ሲሉም ተጨማሪ ክስ አቅርበዋል። እነዚህ መሳሪያዎች በሶማሊያ በሚንቀሳቀሰው “በአልሸባብ እጅ ሊወድቁ ይችላሉ” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል። አክለውም ኢትዮጵያ “የግብፅ ወታደሮች ስምሪትን እንዲቃወሙ በሶማሊያ ውስጥ ያሉ የጎሳ መሪዎችን እና የተቃዋሚ ፖለቲከኞችን እያበረታታች ነው” ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ባሳለፍነው ጥር ወር…
Read More
በውጭ ሀገራት የተቀጠሩ ኢትዮጵያዊያንን ደህንነት ለማስከበር ያለመ ስምምነት ተፈረመ

በውጭ ሀገራት የተቀጠሩ ኢትዮጵያዊያንን ደህንነት ለማስከበር ያለመ ስምምነት ተፈረመ

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽንና የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሠሪ ፌዴሬሽን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመዋል፡፡ ስምምነቱ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሠሪ ፌዴሬሽን በውጭ ሀገር በሥራ የሚሰማሩ ዜጎችን መብት እና ደህንነት ለማስጠበቅ ያለመ ነው፡፡ በስምምነቱ ወቅት የፌዴሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት ፣የዓለም ሥራ ድርጅት ተወካይ እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ በፊርማው ሥነ-ስርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ኮንፌዴሬሽኑ በሀገር ውስጥ በተለያዩ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኞች መብቶች እንዲከበሩ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡ ከሀገር ውስጥ በተጨማሪም በውጭ ሀገራት ተቀጥረው የሚሠሩ ኢትዮጵያዊን መብታቸው ተጠብቆ እዲሠሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ…
Read More