ዜና

ኢትዮጵያ በእስር ላይ ለሚገኙ ታሳሪዎች በቂ ምግብ እያገኙ አይደለም ተባለ

ኢትዮጵያ በእስር ላይ ለሚገኙ ታሳሪዎች በቂ ምግብ እያገኙ አይደለም ተባለ

በፌደራል ማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ ታራሚዎች በቀን ለአንድ ታራሚ የሚመደበው በጀት 35 ብር ብቻ በመሆኑ በቂ ምግብ እያገኙ እንዳልሆነ ተገልጿል፡፡ የተመደበው በጀት አነስተኛ መሆኑ እና የወቅታዊ የገበያ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ ለታራሚዎች የሚቀርብ ምግብ በቂ እንዳይሆን አድርጎታል ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፤ በቃሊቲ ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማእከል (በተለምዶ አባ ሳሙኤል) በመባል በሚጠራው ማረሚያ ቤት የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ጉብኝት ማድረጉን ተናግሯል፡፡ በዚህም ከምግብ አቅርቦት ማነስ በተጨማሪ አልፎ አልፎ አጃቢ የለም በማለት በቀጠሯቸው ፍርድ ቤት እና ሆስፒታል የማይወሰዱ ታራሚዎች እንዳሉም ባደረኩት ምልከታ ለማወቅ ችያለሁ ብሏል ኢሰመኮ፡፡ የአጃቢዎች እጥረት የሚፈጠረውም በማረሚያ ቤቱ የሰው ኃይል ቁጥር ማነስ እና የመርኃ ግብር መደራረብ…
Read More
ኢትዮጵያ 2,500 ወታደሮችን በሶማሊያ ልታሰማራ ነው

ኢትዮጵያ 2,500 ወታደሮችን በሶማሊያ ልታሰማራ ነው

ኢትዮጵያ እና ግብጽን ጨምሮ አምስት ሀገራት 12 ሺህ ገደማ ወታደሮችን ለማሰማራት ተስማምተዋል የአፍሪካ ህብረት እና የሶማሊያ መንግስት በተልዕኮው በሚሳተፉ ሀገራት ዝርዝር እንዲሁም በሚያዋጡት የወታደር ቁጥር ዙሪያ ከስምምነት ደርሰዋል በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ (አውሶም) ውስጥ በሚሳተፉ ሀገራት እና በሚያዋጡት የወታደር ቁጥር ዙሪያ ስምምነት ላይ ተደርሷል ተብሏል። የሶማሊያ ፌዴራል መንግስት እና የአፍሪካ ህብረት በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ላይ በመወከል ወታደር በሚያዋጡ ሀገራት ቁጥር ላይ መስማማታቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። አትዮጵያ እና ሶማሊያ የኢትዮጵያ ጦር በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንዲሳተፍ ተስማሙ የሞቃዲሾ መንግስት ከብሩንዲ እና ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ገብቶበት የነበረውን ውዝግብ ተከትሎ የተሳታፊ ሀገራትን ቁጥር እና የሚልኳቸውን ወታደሮች መጠን ለመወሰን…
Read More
የኢትዮጵያ ጦር በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንዲሚሰማራ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ጦር በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንዲሚሰማራ ተገለጸ

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የኢትዮጵያ ጦር በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንዲሳተፍ ተስማሙ፡፡ በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ (አውሶም) ውስጥ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንዲሰማራ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መስማማታቸው ተገልጿ፡፡ ከሁለት ቀናት በፊት ወደ ሶማሊያ ያቀኑት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ  ከሶማሊያ መከላከያ ሰራዊት አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ኦዳዋ ዩሱፍ ራጌ  ጋር ተገናኝተው በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ ስምምነቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሃሙድ በቅርቡ በአዲስ አበባ ያደረጉትን የሁለትዮሽ ውይይት ተከትሎ የተደረገ የቴክኒክ ምክክር አካል ነው ተብሏል፡፡ የጦር መሪዎቹ የሞቃዲሾ ውይይት በቀጠናዊ ደህንነት፣ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምን እና መረጋጋትን የማስጠበቅ አስፈላጊነት ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተዘግቧል፡፡…
Read More
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 60 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 60 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ነገ እንደሚያካሂድ ገልጿል፡፡ 60 ሚሊየን ዶላር በነገው ዕለት በሁሉም ባንኮች ለጨረታ እንደሚቀርብ ባንኩ አስታውቋል። ባንኩ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ፕሮግራምን ተከትሎ የኢትዮጵያ የውጭ ክፍያ ሚዛን በተለይም የወጪ ንግድ፣ ሐዋላና የካፒታል ፍሰት በከፍተኛ ደረጃ መሻሻል ማሳየቱን ጠቅሷል። በተለይም ከቅርብ ወራት ወዲህ ወርቅን ወደ ውጭ የመላክ ብቸኛ ሥልጣን ላለው ብሔራዊ ባንክ የሚቀርበው የወርቅ መጠን በመጨመሩ ምክንያት የባንኩ ዓለም አቀፍ የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት መጨመሩን ገልጿል። በመሆኑም ከባንኩ የወርቅ ግዥ ጋር በተያያዘ የሚከሰተውን የገንዘብ አቅርቦት ዕድገት ለማገናዘብና በማዕከላዊ ባንኩ እጅ ካለው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ክምችት ከፊሉን ለግሉ ዘርፍ በመስጠት በገበያው ላይ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦትን ለማሻሻል ባንኩ የተወሰነ…
Read More
ኢትዮጵያ ለ10 ዓመት የሚያገለግል አዲስ ፓስፖርት ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ ለ10 ዓመት የሚያገለግል አዲስ ፓስፖርት ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ አራት አይነት ፓስፖርቶችን በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጋለች የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ፓስፖርቶችን ይፋ አድርጓል። ዛሬ በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም ይፋ የተደረጉት ፓስፖርቶች አራት አይነት ሲሆኑ ከመደበኛ ፓስፖርት በተጨማሪ የዲፕሎማት፣ ውጭ ሀገራት እና የአገልግሎት ፓስፖርቶችም ይገኙበታል። ፓስፖርቶቹ በጃፓኑ ቶፓን የደህንነት ኩባንያ እና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ኩባንያ ትብብር ስለመመረቱም ተገልጿል። 10 ዓመት እንዲያገለግል ተደርጎ የተሰራው ይህ ፓስፖርት በአዲስ አበባ በሚገኘው ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የተመረተ ነው። የፓስፖርቱ አገልግሎት ጊዜ 10 ዓመት መደረግ የዜጎችን ጊዜ፣ ገንዘብ እና ጉልበት እንደሚቆጥብ ተገልጿል። ይህ በዚህ እንዳለም በፓስፖርቱ ውስጥ ገጾች ላይ የኢትዮጵያን መልካም ገጽታዎች የሚያጎለብቱ እና ታሪካዊ ቅርጾችን ይዟልም ተብሏል። እንዲሁም ፓስፖርቱ የማይክሮ ችፕስ የተገጠመለት…
Read More
ኢትዮጵያ በዓመት 400 ሺህ ዜጎችን ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ እየላከች ነው ተባለ

ኢትዮጵያ በዓመት 400 ሺህ ዜጎችን ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ እየላከች ነው ተባለ

ኢትዮጵያ በሰለጠነ የሰው ሀይል ዕጥረት ምክንያት ሰራተኞችን ወደ ውጭ ሀገራት መላክ እንዳልቻለች ተገለጸ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በዘረጋው የውጪ ሀገር የሥራ ስምሪት ገበያ ላይ ሂዶ ለመስራት ከሀገራት ከሚቀርበው ጥያቄ አንፃር፤ በከፍተኛ ሁኔታ የሚላኩ ዜጎች እጥረት መኖሩን ገልጿል፡፡ ከመዳረሻ ሀገራት በኩል በርካታ የሰለጠነ የሰው ሀይል ጥያቄን ለኢትዮጵያ እንደሚቀርብ የገለጹት፤ በሚኒስቴሩ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ፕሮጀክት ፅ/ቤት ኃላፊ ብርሀኑ አለቃ ናቸው፡፡ በብዛት የሰው ሀይል ጥያቄ ያለባቸው ሀገራት በሙሉ ከኢትዮጵያ ሰው ለመውሰድ ፍላጎት እንዳላቸውም ሀላፊው አንስተዋል። ጥያቄ ከሚያቀርቡ ሀገራት መካከልም ከመካከለኛው ምስራቅ ኳታር፣ ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ኩዌት፣ ሊባኖስ እና ጆርዳን ናቸው። እንዲሁም ከአውሮፓ ሀገራት ደግሞ ጀርመን፣ ስዊድን፣ ኖርዌይ እና ፖላንድ በከፍተኛ…
Read More
ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ለሚነሱ ችግሮች ማዕከል ነች ስትል ኤርትራ ገለጸች

ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ለሚነሱ ችግሮች ማዕከል ነች ስትል ኤርትራ ገለጸች

ኤርትራ በቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) ለቀረበባት ክስ ምላሽ ሰጥታለች። የሀገሪቱ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል በኤክስ ገጻቸው ባጋሩት ጽሁፍ በቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት የተነሱትን ነጥቦች አጣጥለዋል። ሙላቱ ከሁለት ቀናት በፊት አልጀዚራ ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ "የኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሰ ነው፤ በምስራቅ አፍሪካ አዲስ ግጭት እንዳይከፈት ለማስቆም ጊዜው አሁን ነው" ማለታቸው ይታወሳል። "ጦርነት የኤርትራ መንግስት ዋናኛ ቢዝነስ ነው" የሚሉት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ባለፉት 30 ዓመታት በተለያዩ ድንበር ተሻጋሪ ግጭቶች መሳተፋቸውን በጽሁፋቸው አብራርተዋል። የትግራዩን ጦርነት "እንደ እድል በመጠቀም"ም ወታደሮቻቸውን ወደ ክልሉ አስገብተው "ውድመት" ማስከተላቸውን በመጥቀስ፥ ጦርነቱን ያስቆመው የፕሪቶሪያ ስምምነት ግን ለፕሬዝዳንት ኢሳያስ "መሰናክል" ፈጥሯል ሲሉም ያትታሉ።…
Read More
ማሕሙድ አሊ ይሱፍ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሆነው ተመረጡ

ማሕሙድ አሊ ይሱፍ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሆነው ተመረጡ

የጅቡቲ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ማሕሙድ አሊ ይሱፍ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሆነው ተመረጡ። የ59 ዓመቱ ዲፕሎማት ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት ኮሚሽኑን እንዲመሩ የተመረጡት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሔድ በጀመረው የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ የመሪዎች  ጉባኤ ላይ ነው። አሊ ሞሐመድ ይሱፍ ላለፉት ሥምንት ዓመታት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋኪ ማኅማትን ይተካሉ። ይሱፍ የተመረጡት የኬንያው ጉምቱ ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋ እና የማዳጋስካር የቀድሞ የኤኮኖሚ እና የፋይናንስ ሚኒስትር ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን አሸንፈው ነው። የአፍሪካ ኅብረት 38ኛ ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ ሲጀመር የአንጎላው ፕሬዝደንት ዮዋዎ ሎሬንሶ የዓመቱን የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነት ከሞሪታኒያው ፕሬዝደንት ሞሐመድ ዑልድ ተረክበዋል።
Read More
የአንጎላ ፕሬዝዳንት ዣዎ ሎሬንስ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር ሆኑ

የአንጎላ ፕሬዝዳንት ዣዎ ሎሬንስ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር ሆኑ

አንጎላ የ2025 አፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበርነትን ከሞሪታኒያ በይፋ ተረክባለች። 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በጉባኤው መክፈቻ መርሃ ግብር የወቅቱ የሕብረቱ ሊቀ መንበር ሞሪታኒያ ለአንጎላ ሊቀ መንበርነቷን በይፋ አስረክባለች። የ2024 የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር የነበሩት የሞሪታኒያ ፕሬዝዳንት መሐመድ ኦውልድ ጋዙዋኒ ለአንጎላ ፕሬዝዳንት ዣዎ ማኑኤል ጎንሳልቬስ ሎሬንስ በ2025 የአፍሪካ ሕብረትን በሊቀ መንበርነት እንዲመሩ አስረክበዋል። የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር በየዓመቱ በአባል ሀገራቱ የሚመራ ሲሆን በ2025 ዓመት አንጎላ ተረኛ ሊቀመንበር ሀገር ሆና ትቀጥላለች፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ለሁት ቀናት የሚመክረው የመሪዎች ጉባዔ ከሁለት ቀናት በፊት በተጠናቀቀው 46ኛው የሕብረቱ የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት በመደበኛ ስብሰባ በተለዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል። ከዘንድሮው የመሪዎች…
Read More
የአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

የአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። ስብሰባው “ የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል የአፍሪካ ሕብረት ባዘጋጀው የ2025 መሪ ሃሳብ የሚካሄድ ነው። በስብሰባው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ የሀገራት መሪዎች እና ሌሎች ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል። ከዛሬ ጀምሮ ለሁት ቀናት የሚመክረው የመሪዎች ጉባዔ ከሁለት ቀናት በፊት በተጠናቀቀው 46ኛው የሕብረቱ የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት በመደበኛ ስብሰባ በተለዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል። ከዘንድሮው የመሪዎች ጉባዔ አጀንዳዎች መካከል የሕብረቱ ተቋማዊ ማሻሻያዎች፣ የማካካሻ…
Read More