ኢኮኖሚ

ለኢትዮ ጅቡቲ ባቡር መስመር አዲስ ሀላፊ ተሾመለት

ለኢትዮ ጅቡቲ ባቡር መስመር አዲስ ሀላፊ ተሾመለት

ዳንኤል ኃ/ሚካኤል የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ዋና ስራ አስፈፃሚ ተደርገው ተሾመዋል፡፡ የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር (ኢዲአር) ቺፍ ቴክኒካል ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ኢንጂነር ዳንኤል ኃ/ሚካኤል ከሰኔ 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተጠባባቂ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነዉ ተሾመዋል። የኢትዮ ጂቡቲ ባቡር የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ ለኢትዮ ጂቡቲ ባቡር አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ በነበሩት አብዲ ዘነበ ምትክ ዳንኤልን ኃ/ሚካኤልን ተጠባባቂ ዋና ስራ አስፈፃሚ እንዲሆኑ መድበዋል። የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከተጓዦችና የጭነት አገልግሎት ከ2 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱ ይታወሳል። ማኅበሩ በየቀኑ ከ700 እስከ 1 ሺህ ሰዎችን የማጓጓዝ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከ155…
Read More
ሳፋሪኮም ኬንያ የደንበኞችን መረጃ ለመንግስት አሳልፎ እንዳልሰጠ ገለጸ

ሳፋሪኮም ኬንያ የደንበኞችን መረጃ ለመንግስት አሳልፎ እንዳልሰጠ ገለጸ

ዋና መቀመጫውን ናይሮቢ ያደረገው ሳፋሪኮም ኬንያ የደንበኞቹን መረጃ ለመንግስት እንዳልሰጠ አስታውቋል፡፡ ድርጅቱ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የአገሪቱን የመረጃ ጥበቃ ህግ መሰረት በማድረግ የደንበኞቹን ነፃነት እንደሚያከብር አስታውቋል፡፡ ተቋሙ እንዳለው በፍርድ ቤት አማካኝነት ካልታዘዘ በስተቀር ማንኛውንም የደንበኞቹን መረጃ ለሌላ ሶስተኛ አካል አሳልፎ እንደማይሰጥ ገልጿል፡፡ ድርጅቱ እስካሁን የደንበኞቹን መረጃ እንዲሰጥ ከመንግስት ጥያቄ እንዳልቀረበለት አስታውቋል፡፡ እንዲሁም የደንበኞቹን መረጃ ለመንግስት አካል አሳልፎ እንዲሰጥ የሚጠይቅ የፍርድ ቤት ትእዛዝ እንዳልደረሰውም በመግለጫው ላይ ጠቅሷል፡፡ የድርጅቱ እህት ኩባንያ የሆነው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ አጋርነት ለኢትዮጵያ በሚል ሰኔ ወር 2013 ዓ.ም ላይ በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ህጋዊ ፍቃድ ከተቀበለ ከአንድ ዓመት በኋላ ስራ መጀመሩ ይታወሳል፡፡ ከሶስት ዓመት በፊት ወደ…
Read More
በአማራ ክልል የተወሰኑ ወረዳዎች የባንክ አገልግሎት ተቋረጠ

በአማራ ክልል የተወሰኑ ወረዳዎች የባንክ አገልግሎት ተቋረጠ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የፋኖ ሀይሎች በተቆጣጠሯቸውና ወጣ ገባ በሚሉባቸው ወረዳዎች የባንክ አገልግሎት ተቋርጧል፡፡ የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ አደራጃለሁ የሚል ውሳኔ ከወሰነበት ጀምሮ በአማራ ክልል በፋኖ ታጣቂዎች እና የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች መካከል ጦርነት ከተቀሰቀሰ አንድ ዓመት አልፎታል፡፡ በዚህ ጦርነት ምክንያት በክልሉ ለ10 ወራት የዘለቀ የአስቸኳይ አዋጅ የታወጀ ሲሆን ካሳለፍነው ሳምንት ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም ጀመሮም የአዋጁ ጊዜ ቢያበቃም ክልሉ በኮማንድ ፖስት እየተዳደረ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለም ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ በሰሜን ሸዋ ዞን የተወሰኑ ወረዳዎች የባንክ አገልግሎት ተቋርጧል፡፡ የባንክ አገልግሎት ከተቋረጠባቸው ወረዳዎች መካከል መንዝ ላሎ፣ ግሼ ራቤል፣ አንፆኪያ ገምዛ እና ቀወት ወረዳዎች እንደሚገኙበት ዋዜማ ሬዲዮ…
Read More
ማስተርካርድ ፋውንዴሽን ለ12 የኢትዮጵያ ጀማሪ ተቋማት 720 ሺህ ዶላር ድጋፍ አደረገ

ማስተርካርድ ፋውንዴሽን ለ12 የኢትዮጵያ ጀማሪ ተቋማት 720 ሺህ ዶላር ድጋፍ አደረገ

ለስምንት ሳምንታት ያህል ማመልከቻዎችን ሲቀበል ከቆየ በኋላ፣ ሪች ፎር ቼንጅ ኢትዮጵያ (Reach for Change Ethiopia) በዛሬው ዕለት የማስተርካርድን ኤድቴክ ፕሮግራም የመጀመሪያውን ዙር የተቀላቀሉትን 12 የኤድቴክ ሥራ ፈጣሪዎች ይፋ አድርጓል። “ኤድቴክ” (EdTech) በእንግሊዝኛው ትምህርት እና ቴክኖሎጂን አጣምሮ የያዘ ቃል ሲሆን፣ ትምህርትን አሳታፊ በሆነና ምቹ መንገድ ለማቅረብ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀምን የሚገልጽ ሐሳብ ነው። ፕሮግራሙ የሪች ፎር ቼንጅ እና የማስተርካርድ ፋውንዴሽን አጋርነት አንድ አካል ሲሆን፣ የአጋርነቱ ዓላማም ለተመረጡ የኤድቴክ ድርጅቶች ቁልፍ የሆነ የቢዝነስና የፋይናንስ ድጋፍ መስጠት ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ ፕሮግራሙ ለድርጅቶቹ አዲስን ነገር ስለ መማር ሳይንስ፣ ስለ እድገትና መስፋፋት፣ ስለ ዘላቂነት እንዲሁም ተጽዕኖ ስለ መፍጠር ምልከታን የሚያስጨብጥ ይሆናል። “እነዚህ ፕሮግራሙን የተቀላቀሉ 12 የኤድቴክ…
Read More
ሳፋሪኮም እና ገበያ ኩባንያ የኢትዮጵያን የሥራ ፈጠራ ሥነ ምህዳር የሚያሳድግ “ታለንት ክላውድ” ጀመሩ

ሳፋሪኮም እና ገበያ ኩባንያ የኢትዮጵያን የሥራ ፈጠራ ሥነ ምህዳር የሚያሳድግ “ታለንት ክላውድ” ጀመሩ

ሳፋሪኮም ከገበያ ኩባንያ ጋር በአጋርነት፣ እንዲሁም የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (JICA) ድጋፍ ታክሎበት “ሳፋሪኮም ታለንት ክላውድ” የተሰኘ ፕሮግራም ይፋ አድርገዋል። ፕሮግራሙ የመረጃ መረብን በመጠቀም የሥራ ዕድልን የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል። ፕሮግራሙ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነና ቀጣዩን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎች እንዲሁም የዲጅታሉ ዓለም መሪዎችን አቅም ለማሳደግ ያለመ ነው። ይህ የተለየ አሠራርን ይዞ የመጣው ፕላትፎርም እስከ 2024 እ.ኤ.አ ማብቂያ ድረስ፣ ለ10 ሺሕ ልዩ ልዩ ክህሎት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች አጠቃላይ የአቅም ግንባታ እንዲሁም የሥራ ጉዟቸውን ማሳደጊያ ዕድሎችን የሚያቀርብ ነው። ይህንን በማድረግ፣ በአገሪቱ ውስጥ የሚስተዋለውን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂውን ኢንዱስትሪ ዕድገት የገታውን የቴክኖሎጂ ክህሎት እጥረት ለመቅረፍ ፕሮግራሙ ዒላማ ያደርጋል። "የሳፋሪኮም ታለንት ክላውድ “ለመጪው ዲጂታል ዘመን የኢትዮጵያንን…
Read More
ዳሸን ባንክ ለሶስተኛ ጊዜ የዳሸን ከፍታ የስራ ፈጠራ ውድድርን ሊጀምር ነው                                                                                 

ዳሸን ባንክ ለሶስተኛ ጊዜ የዳሸን ከፍታ የስራ ፈጠራ ውድድርን ሊጀምር ነው                                                                                 

ዳሸን ባንክ በስራ ፈጠራ ዘርፍ የበኩሉን አስተዋፅኦ ለማበርከት እየተገበረ ያለው ዳሸን ከፍታ የስራ ፈጠራ ውድድር ለሶስተኛ ጊዜ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ይካሄዳል፡፡ ባንኩ ውድድሩን ስኬታማ በሆነ መልኩ ለማካሄድ በአማካሪነት ከቀጠረው ዊቬንቸር ሆልዲንግስ ከተሰኘ ሃላፊነቱ የተወሰነ ድርጅት እንዲሁም የሚዲያ አጋር ከሆነው የአፍሪካ ሬኔሳንስ ቴሌቪዥን (አርትስ ቲቪ) ጋር ዛሬ በዋናው መስሪያ ቤት ስምምነት መፈራረሙን ለኢትዮ ነጋሪ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ የዘንድሮው ውድድር በባህር ዳር፣ ደሴ፣ መቀሌ፣አዳማ፣ድሬዳዋ፣ወላይታ፣ ሃዋሳ፣ጅማ እና አዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን በነዚህ ከተሞች በባንኩ ቅርንጫፎች የሰልጣኞች ምዝገባ ከሰኔ 18 እስከ ሰኔ 29-2016 ዓ.ም ይከናወናል፡፡ ለተመዘገቡ ሰልጣኞች በስራ ፈጠራ ዙሪያ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የሚያስችል ስልጠና በነዚህ ከተሞች ከተሰጠ በኋላ ሰልጣኞቹ የፈጠራ መነሻ ሃሳባቸውን በፅሁፍ በባንኩ…
Read More
በርበራ ወደብ በዓለም ባንክ የጥራት መመዘኛ ከአፍሪካ በቀዳሚነት ተመረጠ

በርበራ ወደብ በዓለም ባንክ የጥራት መመዘኛ ከአፍሪካ በቀዳሚነት ተመረጠ

የዓለም ባንክ በመላው ዓለም ያሉ ወደቦች እቃ የመጫን አቅማቸውን የተመለከተ አሁናዊ ያሉበትን ሁኔታ አስመልክቶ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የእቃ ጫኝ ኮንቴይነር የመያዝ አቅማቸውን መሰረት በማድረግ የወደቦችን ደረጃ ያወጣው ባንኩ ኢትዮጵያ የባህር ሀይሏን ልታቋቁምበት ያሰበችበት በርበራ የተሻለ ደረጃን አግኝቷል፡፡ በባንኩ ሪፖርት መሰረት የራስ ገዟ ሶማሊላንድ ንብረት የሆነው በርበራ ወደብ ከሰሃራ በረሃ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ የመጀመሪያው ወደብ ተብሏል፡፡ በርበራ ወደብ በዓለም ካሉ ወደቦች በ103ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ከሰሀራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ ቀዳሚው ሆኗል፡፡ ሞቃዲሾ ወደብ ከበርበራ ወደብ በመቀጠል በሁለተኝነት ሲጠቀስ የጊኒው ኮናክሪ በሶስተኝነት ሲቀመጥ  የኢኳቶሪያል ጊኒው ማለቡ ወደብ ደግሞ በአራተኝነት ተቀምጧል፡፡ ከመላው ዓለም ደግሞ የቻይናው ያንግሻህ ወደብ በአንደኝነት ሲቀመጥ…
Read More
ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ዓመት 1 ትሪሊየን ብር አመታዊ በጀት መደበች

ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ዓመት 1 ትሪሊየን ብር አመታዊ በጀት መደበች

የሚንስትሮች ምክር ቤት በ34ኛ መደበኛ ስብሰባው የ2017 በጀት አመት የፌዴራል መንግስት ረቂቅ በጀት አዘጋጅቷል። የ2017 ዓ.ም የፌደራል መንግስት በጀት የአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነውን የ2016-2018 የልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችን እና የ2017-2021 የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚና የፊስካል ማዕቀፍን ማስፈጸም እንዲቻል በሚያደርግ መልኩ መዘጋጀቱን አስታውቋል። እንዲሁም የ2016 የፌደራል መንግስትን የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም መነሻ በማድረግ፤ የመንግስት የፋይናንስ አቅም እና ተጠባቂ ገቢዎችን ታሳቢ በማድረግ እንዲሁም አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የተሰጣቸውን ተልኮና ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስፈልጋቸውን ወጪ በመገምገም እንዲዘጋጅ መደረጉንም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በዚሁ መሰረት ለፌዴራል መንግስት መደበኛ ወጪዎች ፣ ለካፒታል ወጪዎች ፣ ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ…
Read More
ኢትዮጵያ ከአበባ ንግድ ከ300 ሚሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከአበባ ንግድ ከ300 ሚሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ባለፋት አስር ወራት ከአበባ ኤክስፓርት ከ 3 መቶ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች፡፡ የሆርቲካልቸር ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተለይም የአበባ ኤክስፖርት ለኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ግኝት ከፍተኛ አስተዋጽኦን  እያበረከተ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ኢንቨስትመንት እና ምርት ግብይት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ አበበ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፋት አስር ወራት 79 ሺህ 819 ቶን የአበባ ምርት ለውጪ ገበያ በማቅረብ 392 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ አግኝታለች ብለዋል። የኢትዮጵያ የአበባ ምርት በአብዛኛው ወደ አውሮፓና ኤዥያ ሀገራት እንደሚላክ  የተናገሩት   ስራ አስፈፃሚው  ምርጥ አስር ተብለው ከተለዩት ተቀባይ ሀገራት መካከል ደግሞ ኔዘርላንድ ትልቁን ድርሻ ትይዛለች ብለዋል።  በበጀት አመቱ አስር ወራት ከእቅድ አፈፃፀም አንጻር ሲታይ የተገኘው ገቢ…
Read More
ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ ግብይትን ማስቆም እንዳልቻለች ተገለጸ

ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ ግብይትን ማስቆም እንዳልቻለች ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ከወርቅ ማዕድን 363 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ያቀደች ቢሆንም የተገኘው ግን 67 በመቶው ብቻ ነው ተብሏል፡፡ ህገ ወጥ የወርቅ ግብይት ዋነኛው ችግር መሆኑን ተከትሎ በመከላከያ ኮማንድ ፖስትና በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጭምር ክትትል ቢደረግም ህገ ወጥ የወርቅ ንግድን ማስቆም እንዳልተቻለ ማዕድን ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ በማዕድናት ሕገ ወጥ ግብይት፣ ኮንትሮባንድና የፀጥታ ችግር ምክንያት በባለፉት ዘጠኝ ወራት ወደ ብሔራዊ ባንክ የገባው ወርቅ ሦስት ቶን ብቻ እንደሆነ፣ ይህም ከዕቅዱ 50 በመቶ ብቻ መሆኑ ታውቋል፡፡ በመጋቢት ወር ብሔራዊ ባንክ የገባው ወርቅ 350 ኪሎ ግራም ሲሆን ይህም በ2014 መጋቢት ወር ከተገኘው 800 ኪሎ ግራም በእጅጉ ያነሰ ነው ተብሏል፡፡ በአገሪቱ ያሉ ወርቅ…
Read More