አካባቢ ጥበቃ

ኢትዮጵያ የህዳሴው ግድብ ውሀ መያዣ ጊዜን አራዘመች

ኢትዮጵያ የህዳሴው ግድብ ውሀ መያዣ ጊዜን አራዘመች

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እስከ መስከረም ውሀ እንደማይዝ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ተናግረዋል። ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ እየሰጡ ያሉት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ በበርካታ ጉዳዮች ዙሪያ ከአባላቱ ለተነሳላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት የኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ ውሀ ሙሌት አይከናወንም ብለዋል። "ኢትዮጵያ የሱዳንን እና ግብፅ ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ የህዳሴ ግድብ ሙሌቱ እስከ መስከረም መጀመሪያ አታከናውንም" ሲሉ ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናግረዋል። ታላቁ የህዳሴ ግድብ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከሀምሌ ወር ጀምር ውሀ ሲይዝ የቆየ ሲሆን ዘንድሮ ግን ውሀ የመያዣው ጊዜ ወደ መስከረም መዛወሩ ተገልጿል። እንደ ጠቅላይ ሚንስትሩ ገለጻ የዘንድሮው ውሀ ሙሌት ወደ ግብጽ እና ሱዳን በቂ የዉሃ ከደረሰ በኋላ ሙሌቱ…
Read More
የአዲስ አበባ የ70 ዓመት ባለውለታ አረፉ

የአዲስ አበባ የ70 ዓመት ባለውለታ አረፉ

በአዲስ አበባ ከተማ ላለፉት 70 ዓመት ዳቦ በማቅረብ የሚታወቁት የ'ሸዋ ዳቦ' መሥራቹ ዘሙይ ተክሉ ማረፋቸው ተሰምቷል። የአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ሥያሜውን የተዋሱት የሸዋ ዳቦ መሥራቹ አቶ ዘሙይ ተክሉ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ታውቋል። የኤርትራ መሠረት ያላቸው ዘሙይ ወደ አዲስ አበባ ዘልቀው ያቋቋሙት ሸዋ ዳቦ ለ70 ዓመታት ለአዲስ አበቤዎች ዳቦ ሲያቀርብ ቆይቷል። የአምስት ልጆች አባት የሆኑት አቶ ዘሙይ አንደኛዋ ልጃቸው በአዲስ አበባ ሥማቸው ከሚጠራ ኬክ ቤቶች መካከል የሆነው የ'ቤሎስ ኬክ' ቤት መስራች ሆናለች። በደርግ አስተዳድር ዘመን ለኤርትራ መገንጠል የሚዋጉ አማጽያንን በመደገፍ ታስረው የነበሩት ዘሙይ ተክሉ፣ በከተማዋ የሌላኛው ሥመ ጥር ኬክ ቤት መሥራች የበላይ ተክሉ ወንድምም ናቸው። ሸዋ ዳቦ ቤት በስንዴ መወደድ…
Read More
ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ኢትዮጵያ እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ የ10 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነትን በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የኮይካ ሃላፊ ሊ ቢዩንግህዋ ፈርመውታል። የገንዘብ ድጋፉ የኢትዮጵያን ግብርና ለማዘመን ይውላል የተባለ ሲሆን በተለይም የወተት እና የወተት ተዋጽኦ ምርታማነትን ለማሳደግ ያስችላል ተብሏል። የወተት ምርታማነትን የሚያሳድገው ይህ ፕሮጀክት በቀጣዮቹ ስድስት ዓመታት እንደሚተገበር የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፕሮጄክቱ በወተት ልማት እና እንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን መደገፍ ላይ ትኩረቱን እንደሚያደርግም ተገልጿል። የተሻሻሉ የወተት ላሞችን ለአርሶ አደሩ ማቅረብ፣ የወተት ምርታማነትን መጨመር፣ በማህበር የተደራጁ ወተት አቅራቢዎችን የገበያ እድሎችን ማስፋት፣ ተጨማሪ ሌሎች አሰራሮችን መዘርጋት የፕሮጀክቱ ዓላማ ነው ተብሏል።…
Read More
ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የቡና ሳይንስ ምሁራን ሊኖሯት ነው

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የቡና ሳይንስ ምሁራን ሊኖሯት ነው

ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በቡና ሳይንስ ትምህርት መስክ የተማሩ ተማሪዎች ሊመረቁ ነው። የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፤ በ2015 የትምህርት ዘመን መጨረሻ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 37 ተማሪዎችን በ " ቡና ሳይንስ " የትምህርት መስክ ያስተማራቸውን ተማሪዎች እንደሚያስመርቅ አሳውቋል። ዩኒቨርሲቲው የቡና ምርት ኢትዮጵያ ትልቁ የውጭ ምንዛሬ የምታገኝበት ሸቀጥ በመሆኑ በ2015 ዓ.ም መጨረሻ 37 ተማሪዎችን በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በቡና ሳይንስ የትምህርት መስክ ይመረቃሉ ብሏል። ኢትዮጵያ ቡናን ለዓለም ያበረከተች ሀገር ብትሆንም እስካሁን ድረስ የቡና ትምህርት መስክ ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት አዳጋች ሆኖ ነበር ያለው ተቋሙ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት የቡና ሳይንስ ትምህርት ክፍል እራሱን ችሎ በ2012 ዓ.ም እንዲከፈት ማድረጉን አስታውሷል ። በቡና ምርት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመመርመር ከዘርፉ ተጠቃሚ…
Read More
በደብረ ብርሃን ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑ ተገለጸ

በደብረ ብርሃን ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑ ተገለጸ

የደብረብርሃን ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሪት መሰረት መንገሻ እንደገለጹት ከትላንት ጀምሮ መርዝ ተጨምሮበት ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ተቋማቸው አንዱ ተግባሩ የሚያመርተውን ውሃ ጥራት አረጋግጦ ለተጠቃሚዎች ማሰራጨት ሃላፊነታቸው በመሆኑን ባለሙያዎች እሁድ ቅዳሜን እና የበዓላትን ቀናት ጭምር አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡ የውሃ ማጠራቀሚያ ጋኖች ታጥረው የሚጠበቁ ከመሆኑም በላይ ሁል ጊዜ በባለሙያ ክትትል እየተደረገላቸው ውሃው በባለሙያ ጥራቱ ተረጋግጦ ለደንበኞች እንደሚሰራጭ አረጋግጠዋል፡፡ የፀጥታ ችግር ሲከሰት ደግሞ በልዩ ሁኔታ ጥበቃና ክትትል እንደሚደረግላቸው ጠቁመዋል፡፡ ችግር ካጋጠመም ውሃው እንደማይለቀቅ ጠቅሰው ህብረተሰቡ የውሃ ተቋሙ የሚያደርገውን ጥንቃቄ በአግባቡ ተረድቶ በአሉባልታ ወሬ እንዳይረበሽ መክረዋል፡ ውሃው 100 ፐርሰንት ንጹህ መሆኑን ስራ አስኪያጇ መልዕክታቸውን…
Read More
ግብጽ የህዳሴው ግድብን ዓለም አቀፋዊ ከማድረግ እንድትታቀብ ኢትዮጵያ አሳሰበች

ግብጽ የህዳሴው ግድብን ዓለም አቀፋዊ ከማድረግ እንድትታቀብ ኢትዮጵያ አሳሰበች

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት ግብጽ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ተደጋጋሚ መግለጫዎችን እያወጣች ነው። መግለጫዎቹ ኢትዮጵያ በቀጣይ ክረምት ወራት ግድቡ ውሀ እንዲይዝ የተናጠል ውሳኔ እንዳትወስን የሚያሳስቡ ናቸው። በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ከጋዜጠኞች ለቀረበው ጥያቄ "ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ ውሀ አሞላል ዙሪያ ማንንም የማስፈቀድ ግዴታ የለባትም" ብለዋል። ታላቁ የህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ ግዛት እና ሀብት እየተገነባ ያለ ፕሮጀክት ነው የሚሉት አምባሳደር መለስ በእቅዳችን እና በፕሮግራማችን እንመራለን ሲሉም አክለዋል። የግብጽ ሰሞንኛ ተደጋጋሚ መግለጫ የህዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር ውሀ መመሙያ ጊዜ እየተቃረበ መምጣቱን ተከትሎ ጉዳዩን ዓለም አቀፋዊ ለማድረግ ያለመ እንደሆነም ቃል አቀባዩ…
Read More
ግዙፉ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገለጸ

ግዙፉ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገለጸ

በቻይና በሲሚንቶ ዘርፍ የተሰማራው ግዙፉ ሲኖማ ዓለም አቀፍ ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገልጿል። በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው የሲኖማ ዓለም አቀፍ ኩባንያ ሊቀመንበር እና የሲኤንቢኤም ተቋም ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ሚስተር ሉ ያን እና የሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር ተወያይተዋል። ኩባንያው በኢትዮጵያ ኢንቨስት በሚደረግበት ዙሪያ ቤጂንግ በሚገኘው የኩባንያው ዋና ጽ/ቤት ተገኝተው ውይይት አድርገዋል። አምባሳደር ተፈራ በውይይቱ ወቅት ኩባንያው በኢትዮጵያ ባሉት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ከዲዛይን ጀምሮ በግንባታ ረገድ ላበረከተው አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበው፣ በኢትዮጵያ ካለው የግንባታ ስፋት አንጻር የሲሚንቶ ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል። አምባሳደር ተፈራ አያይዘውም፣ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ከፍተኛ የሆነ የሲሚንቶ ፍላጎት ግምት ውስጥ በማስገባት በኢንቨስትመንቱ ዘርፍ ቢሰማራ የጋራ ተጠቃሚነቱ ሰፊ መሆኑን ገልጸዋል።…
Read More
ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ በመሸመት ቀዳሚ አገር ሆነች

ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ በመሸመት ቀዳሚ አገር ሆነች

ኬንያ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል በመሸመት ቀዳሚ መሆኗ የተገለጸ ሲሆን፤ በተለይ ባለፈው ጥር ወር ያስገባቸው የኃይል መጠን በታሪክ ከፍተኛው ነው ተብሏል፡፡ ይህ የሆነውም በምስራቅ አፍሪካ ባጋጠመው አስከፊ ድርቅ ምክንያት የኃይል ማመንጫ ግድቦች ውሃቸው በመድረቁ ምክንያት መሆኑ ተነግሯል፡፡ ከኬንያ ስታትስቲክስ ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፤ አገሪቱ ባለፈው ጥር ወር 68 ነጥብ 48 ሚሊዮን ኪሎዋት ኤሌክትሪክ ኃይል አስገብታለች፡፡ ኹለቱ አገራት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ የኤሌክትሪክ ኃይል በቅናሽ ለመገበያየት ከተስማሙ በኋላ፤ ኬንያ 39 ሚሊዮን ዩኒት ኃይል ከኢትዮጵያ ማስገባቷ ተነግሯል፡፡ በዚህም አገሪቷ በርካሽ ዋጋ ኃይል ለማስገባት ከተስማማች በኋላ ጥር ላይ 200 ሜጋዋት የኤሌክትርክ ኃይል ከኢትዮጵያ ማስገባቷ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህም የኃይል አቅርቦቱን ለማረጋጋት እንዳስቻላት ተጠቁሟል፡፡ ኬንያ…
Read More
የ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶ ተጠናቀቀ

የ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶ ተጠናቀቀ

የሕዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶ ተጠናቀቀ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት  እንዳስታወቀው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶ ተጠናቋል። የሕዳሴ ግድብ መሠረተ ድንጋይ የተጣለበት 12ኛ ዓመትን አስመልክቶ ጽህፈት ቤቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ግድቡ በሚቀጥለው ዓመት ተጠናቆ ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ የሚገባ ሲሆን 5200 ሜጋ ዋት ሀይል ያመነጫል። በ5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ እየተገነባ ያለው ይህ የአፍሪካ ግዙፍ ግድብ ወጪው በኢትዮጵያውያን እና በመንግስት በመሸፈን ላይ ይገኛል። የግድቡ ሁለት ቱርባይኖች አሁን ላይ 700 ሜጋ ዋት ሀይል በማመንጨት ላይ ሲሆን የግድቡ አራተኛ ዙር ውሀ ሙሌት በመጪው ክረምት ወራት እንደሚካሄድ ተገልጿል። ግብጽ ኢትዮጵያ በተናጥል በግድቡ ላይ የምትወስደው እርምጃ ታሪካዊ የውሀ ድርሻዬን ይጎዳል በሚል…
Read More
ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ተመራማሪዋን በሞት አጣች

ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ተመራማሪዋን በሞት አጣች

ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ተመራማሪዋን በሞት አጣች ታዋቂው የአካባቢ ጉዳይ ሳይንስቲስት ዶክተር ተወልደ ብርሃን ገብረእግዚአብሄር በ 83 ዓመታቸው ህይወታቸው አልፋል። ዶ/ር ተወልደብርሃን በትግራይ ክልል በአድዋ ከተማ አቅራቢያ ባለችው ‹‹አዲ-ስላም›› የተሰኘች የገጠር መንደር  የተወለዱ ሲሆን ፣ በቀለም ትምህርት ገፍተው የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በ1955 ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተቀበሉ በኋላ የሁለተኛ እና ዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከዌልስ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡ በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ አገልግሎት የተከበረ ሥም ያላቸው ዶክተር ተወልደ በዘርፉ ላደረጉት ምርምርና በጉዳዩ ዙሪያ ከፍተኛ ግንዛቤ እንዲፈጠር ላደረጉት ጥረት በ2000 Right Livlihood Award ሽልማት አግኝተዋል፡፡ በተጨማሪም በ2006 ዓመት የተባበሩት መንግሥታት በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ ሰዎች የሚሰጠውን Champions of the Earth ሽልማት አግኝተዋል፡፡ የተማሩበት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ…
Read More