መነሻ ገፅ

በኢትዮጵያ የፓለቲካ ምህዳሩ ወደ አስቸጋሪ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑ ተገለፀ

በኢትዮጵያ የፓለቲካ ምህዳሩ ወደ አስቸጋሪ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑ ተገለፀ

በኢትዮጵያ የስነ መንግስት ታሪክ ውስጥ ኢትዮጵያ አሁን የምትገኝበት የፓለቲካ ምዕራፍ እጅግ  አስቸጋሪ ደረጃ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርታ (ኢዜማ) ዋና ፀሐፊ አበበ አካሉ ገልፀዋል። አቶ አበበ አካሉ ይሄን በእናት ፓርቲ አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንዳሉት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ወደ አስቸጋሪ ሁኔታ እየገባ ነው። በኢትዮጵያ እየተሸጋገረ የመጣውን አደገኛ የፓለቲካ ምዕራፍ በተበታተነ ትግል ውስጥ መቀልበስ እንደማይቻልም አቶ አንስተዋል። አሁን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ዴሞክራሲ ቅንጦት ነው የሚሉት አቶ አበበ ሰውነት እጅግ የረከሰበት ዘመን ላይ መድረሳቸውን አስታውሰዋል። አክለውም የአገር እሴት ሲናድ አብሮ የሚናድ አገረ መንግስት ምስረታ በመኖሩ የሀገርን ቋሚ እሴት'ና ምዕተ አመት ዘለል ተቋማት መከበር አለባቸው ብለዋል። ምንም እንኳን እንደ ፓርቲ ህገመንግስቱ እንዲቀየር…
Read More
ሞ ፋራህ የፖርት-ጄንቲል 10 ኪሎ ሜትር ውድድርን በሰባተኛነት አጠናቀቀ

ሞ ፋራህ የፖርት-ጄንቲል 10 ኪሎ ሜትር ውድድርን በሰባተኛነት አጠናቀቀ

በሳሙኤል አባተ ሞ ፋራህ በፖርት-ጄንቲል 10 ኪሎ ሜትር ውድድርን በሰባተኛነት አጠናቀቀ። ሞ ፋራህ የጋቦን ፖርት-ጄንቲል 10 ኪሎ ሜትር ሩጫ በ30 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ ሰባተኛ ሆኖ አጠናቋል። የአራት ጊዜ የኦሎምፒክ ሻምፒዮን የሆነው ሞ ፋራህ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ለሚካሄደው የለንደን ማራቶን ውድድር በኢትዮጵያ ልምምዱን አድርጓል ተብሏል። አትሌቱ 2023 ጡረታ ከመውጣቱ በፊት የመጨረሻው የውድድር ዓመቱ እንደሚሆን ባለፈው በጥር ወር አስታውቋል። ጋቦን ላይ ኬንያዊው ቪንሴንት ኪፕኬሞይ በ28 ደቂቃ ከ11 ሰከንድ አንደኛ በመውጣት አሸንፏል። ፋራህ እ.ኤ.አ. በ2022 የለንደን ማራቶን በሽንጥ ጉዳት ምክንያት ያልተሳተፈ ሲሆን፤ የዘንድሮው ውድድር ከ2019 በኋላ የመጀመሪያው ሙሉ ማራቶን ይሆናል ተብሏል። ለብሪታኒያዊው የመጨረሻ የለንደን ማራቶን ውድድር እንደሚሆን የሚጠበቅ ሲሆን፤ ቀነኒሳ በቀለን ጨምሮ በታሪክ…
Read More
የኢትዮጵያ ትልቁ ባንክ ከቻይናው የቴክስታይል ኩባንያ ጋር ስምምነት ተፈራረመ

የኢትዮጵያ ትልቁ ባንክ ከቻይናው የቴክስታይል ኩባንያ ጋር ስምምነት ተፈራረመ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሠራተኞቹ የደንብ ልብስ ከሚያቀርብ የቻይና ቴክስታይል ኩባንያ ጋር ተፈራርሟል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሠራተኞቹ የደንብ ልብስ አቅርቦት ከቻይናው ጂያንግሱ ሰንሻይን ግሩፕ ጋር መፈራረሙን አስታውቋል። የንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቤ ሳኖ ጥራት ያለው የደንብ ልብስ ለሠራተኞች እንዲቀርብ የሚያስችል ውይይት ከጂያንግሱ ሰንሻይን ግሩፕ ተወካዮች ጋር መወያየታቸው ተመላክቷል፡፡ ለደንብ ልብስ አቅርቦቱ ባንኩ ከፍተኛ ወጪ በመመደብ ለአብዛኛው ሠራተኛ ወጪውን የሸፈነ ሲሆን፣ በመካከለኛና ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ የባንኩ ሠራተኞች እንዲሁም የሥራ ኃላፊዎች ደግሞ የተወሰነ ወጪ ተጋርተው የሚቀርብ መሆኑን አቶ አቤ ገልፀዋል፡፡ የጂያንግሱ ሰንሻይን ግሩፕ በኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚ/ር ጋዊ ቻንሁሀ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች ደንብ ልብስ ተቋማቸው በኢትዮጵያ ቅርንጫፉ ከሚሰራቸው አቅርቦቶች ትልቁ…
Read More
ሸራተን ሆቴል በጅማ ከተማ ባለ አምስት ኮኮብ ሆቴል ሊገነባ ነው

ሸራተን ሆቴል በጅማ ከተማ ባለ አምስት ኮኮብ ሆቴል ሊገነባ ነው

በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር ያለው ሸራተን ሆቴል በ ጅማ ከተማ በፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ደረጃ ባለ አምስት ኮከብ ኢንተርናሽናል ሆቴል ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀምጧል:: የግንባታ መሰረተ ድንጋዩን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ አስቀምጠዋል፡፡ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከዚህ በፊት ጅማ ከተማ ኖክ ማደያ አካባቢ ለመገንባት አቅዶ የነበረውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ዘመናዊ ሆቴል ወደ ከተማዋ መግቢያ እንዲዛወር ተደርጓል። ከዚህ በፊት ሆቴሉ ሊገነባበት የነበረው ቦታ ላይም ዘመናዊ የገበያ ማዕከል እንደሚገነባም የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ኩባንያ አቶ ጀማል አህመድ ተናግረዋል። የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በበኩላቸው ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በኦሮሚያ ክልል ሰፊ…
Read More
ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ በመሸመት ቀዳሚ አገር ሆነች

ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ በመሸመት ቀዳሚ አገር ሆነች

ኬንያ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል በመሸመት ቀዳሚ መሆኗ የተገለጸ ሲሆን፤ በተለይ ባለፈው ጥር ወር ያስገባቸው የኃይል መጠን በታሪክ ከፍተኛው ነው ተብሏል፡፡ ይህ የሆነውም በምስራቅ አፍሪካ ባጋጠመው አስከፊ ድርቅ ምክንያት የኃይል ማመንጫ ግድቦች ውሃቸው በመድረቁ ምክንያት መሆኑ ተነግሯል፡፡ ከኬንያ ስታትስቲክስ ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፤ አገሪቱ ባለፈው ጥር ወር 68 ነጥብ 48 ሚሊዮን ኪሎዋት ኤሌክትሪክ ኃይል አስገብታለች፡፡ ኹለቱ አገራት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ የኤሌክትሪክ ኃይል በቅናሽ ለመገበያየት ከተስማሙ በኋላ፤ ኬንያ 39 ሚሊዮን ዩኒት ኃይል ከኢትዮጵያ ማስገባቷ ተነግሯል፡፡ በዚህም አገሪቷ በርካሽ ዋጋ ኃይል ለማስገባት ከተስማማች በኋላ ጥር ላይ 200 ሜጋዋት የኤሌክትርክ ኃይል ከኢትዮጵያ ማስገባቷ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህም የኃይል አቅርቦቱን ለማረጋጋት እንዳስቻላት ተጠቁሟል፡፡ ኬንያ…
Read More
ኢትዮጵያ በህገ ወጥ ማዕድን ማውጣት ስራ ተሰማርተው የተገኙ 90 የውጭ ዜጎችን አሰረች

ኢትዮጵያ በህገ ወጥ ማዕድን ማውጣት ስራ ተሰማርተው የተገኙ 90 የውጭ ዜጎችን አሰረች

የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ያላቸው ዜጎች በኢትዮጵያ በማእድን ማውጣት ስራ ተሰማርተው ተገኝተዋል ተብሏል፡፡ በጋምቤላ ክልል በህገ ወጥ መንገድ ወርቅን ጨምሮ ማእድን ማውጣት ሰራ ላይ የተሰማሩ 45 የውጭ ሀገራት ዜጎች መያዛቸውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገልጿል። የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ደኤታ ሰላማዊት ካሳ በሰጡት መግለጫ በክልሉ 3 ኢትዮጵያውያንም ተይዘዋል ብለዋል፡፡ በተመሳሳይ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል 47 የውጭ ዜጎች ወርቅን ጨምሮ በማእድን ማውጣት ስራ ላይ ተሰማርተው ሲያዙ 9 የግል ማህበራትና 7 ኢትዮጵያውያንም በቁጥጥር ስር ውለዋል ተብላል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ከሰሞኑ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዳሉት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በህገ ወጥ ማእድን ንግድ መታወኩን ተናግረው ነበር። እነዚህን ህገወጥ የማእድን አዘዋዋሪዎች ለመቆጣጠር የጸጥታ ሀይል እናሰማራለን ሲሉ ለምክር ቤቱ…
Read More
በኢትዮጵያ የምልክት ቋንቋ ህገ-መንግታዊ እውቅና እንዲሰጠው ተጠየቀ

በኢትዮጵያ የምልክት ቋንቋ ህገ-መንግታዊ እውቅና እንዲሰጠው ተጠየቀ

ሩትስና ዊንግስ የተባለ ሀገር በቀል ግብረ ሰናይ ድርጅት የምልክት ቋንቋ በሚሊዮኖች ቢነገርም ተገቢውን እውቅና አላገኘም ብሏል። ከተመሰረተ ሁለት ዓመት የሞላው ድርጅቱ ይህም በመሆኑ መስማት የተሳናቸው ዜጎች በቋንቋቸው የመማር፣ የመገልገልና መረጃ የማግኘት መብታቸው እንደተገደበ ተናግሯል። የኢትዮጵያ የምልክት ቋንቋ እንደሌሎች ቋንቋዎች "ሀገርኛ" ቢሆንም እንዳላደገ ተነግሯል። የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ሰርካለም ግርማ (ዶ/ር) ለአል ዐይን  የምልክት ቋንቋ በቋንቋ ፖሊሲው እንዲካተት ጥረት እንደሚደረግ ተናግረዋል።ፖሊሲው ገና ባለመጽደቁ "ተስፈኞች" ነን ብለዋል። ከ90 በመቶ በላይ የምልክት ቋንቋ ተናጋሪዎች ቋንቋቸውን የሚማሩት ት/ቤት ቢሆንም ሀገሪቱ ካሏት ት/ቤቶች አንድ በመቶ የማይሞሉት ብቻ 'አካቶ ትምህርት የሚያስተምሩ መሆናቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት እያሱ ኃይሉ (ዶ/ር) ተናግረዋል። ቋንቋው እንዲያድግና ትኩረት እንዲሰጠው የሀገሪቱ የስራ…
Read More
አሰልጣኝ ውበቱ አባተ የስራ መልቀቂያ ማስገባታቸው ተገለጸ።

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ የስራ መልቀቂያ ማስገባታቸው ተገለጸ።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ውበቱ አባተ የመልቀቂያ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስገብተዋል ተብሏል። የአሰልጣኙን የመልቀቂያ ጥያቄ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እየተወያዩበት እንደሆነ ትርታ ስፖርት ዘግቧል። የስራ አስፈፃሚ አባላቱ በሁለት ሀሳብ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል። አንዳንዶቹ አሁኑኑ ይሰናበት ጥያቄውን እንቀበል ያሉ ሲሆን ሌሎች አባላት ደግሞ ቀሪ ሁለት የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታዎችን ይጨርስ እያሉ ይገኛሉ ተብላል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በቅርቡ ከአሰልጣኙ በቀረበለት ጥያቄ መሰረት ውሳኔውን የሚያሳውቅ ይሆናል። አሰልጣኝ ውበቱ አባተ በኢትዮጵያ ልምድ ካላቸው አንጋፋ አሰልጣኞች መካከል አንዱ ሲሆኑ ከኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ጋር በመሆን የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን አሸንፈዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ከ2020 ጀምሮ በማሰልጠን ላይ ያሉት አሰልጣኝ ውበቱ…
Read More
መንግሥት የአማራ ልዩ ሀይልን ጨምሮ የሁሉንም ክልል ልዩ ሀይሎች ትጥቅ እያስፈታ መሆኑን ገለጸ

መንግሥት የአማራ ልዩ ሀይልን ጨምሮ የሁሉንም ክልል ልዩ ሀይሎች ትጥቅ እያስፈታ መሆኑን ገለጸ

መንግሥት የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መጠበቅ የሚያስችል አንድ ጠንካራ የተማከለ ሠራዊት ለመገንባት አቅጣጫ ማስቀመጡን ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ ገልጿል። በዚህ መሠረት የየክልሉን ልዩ ኃይሎች ወደ ተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች እንዲገቡ የሚያስችላቸውን ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማካሄድ መጀመሩን አሳውቋል። በሁሉም ክልሎች የሚገኙ የልዩ ኃይል አባላት እንደ ምርጫቸውና እንደ ፍላጎታቸው ፣በመከላከያ፣ በፌደራል ፖሊስ፣በክልል ፖሊስ አባልነት መካተት ይችላሉ ብሏል። በዚህ ሐሳብ ላይም ከልዩ ኃይል አመራሮችና አባላት ጋር ከመግባባት ላይ መደረሱን ገልጿል። ቀደም ብሎም በሁሉም ክልል አመራሮች ጥናት ተደርጎበት፣ በተገኘው ውጤት ያለምንም ልዩነት ውሳኔው ስምምነት ተደርሶበታል ሲል አስታውሷል። የክልል ልዩ ኃይልን በተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች የማካተት ውሳኔና የተግባር እንቅስቃሴ በጥናት ላይ ተመሥርቶ የሚከናወን ነው ያለው መንግስት " ይህ…
Read More
በአማራ ክልል ልዩ ኃይልን እና በፌደራል የጸጥታ ኃይሎች መካከል ውጥረት መፈጠሩ ተገለጸ

በአማራ ክልል ልዩ ኃይልን እና በፌደራል የጸጥታ ኃይሎች መካከል ውጥረት መፈጠሩ ተገለጸ

የአማራ ክልል ልዩ ኃይልን በግዴታ ትጥቅ ለማስፈታት እንቅስቃሴ በመጀመሩ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች፤ በክልሉ ልዩ ኃይል እና በፌዴራል የጸጥታ ተቋማት መካከል ከፍተኛ ውጥረት መፈጠሩን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አስታወቀ፡፡ የክልሉን ልዩ ኃይል ያለ በቂ ዝግጅት፣ ውይይት፣ የጋራ መግባባትና መተማመን ሳይደረስ በድንገት እና ያለበቂ የጸጥታ ዋስትና ለማፍረስ መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ እና ውሳኔውን ለማስፈጸም እየሄደበት ያለው መንገድ ኃላፊነት የጎደለው መሆኑን አብን አስታውቋል፡፡ ጉዳዩ በአማራ ክልል ብቻ ሳይወሰን በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ አለመረጋጋት የሚፈጥር፣ ክልሉን እና  ኢትዮጵያን ወደ ሌላ የቀውስ አዙሪት የሚከት አደገኛ አካሄድ መሆኑን አብን ለፌዴራሉ መንግሥትና ለአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አሳስቧል፡፡ በመሆኑም፣ የገዥው ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ውሳኔውን በአፋጣኝ እንዲቀለብስ እና ከአማራ…
Read More