29
Nov
የኢትዮጰያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ እንደገለጸው መነሻውን አራት ኪሎ ያደረገ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለከንቲባ ቢሮ ማስገባቱን ገልጿል፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ "ጦርነት ይቁም! ሠላም ይስፈን፣ መከላከያ ሰራዊቱ ባስቸኳይ ወደ ካምፕ ይግባ!" በሚል መሪ ቃል እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚካሄደውን ደም አፋሳሽ ጦርነት ለማስቆም በሚል የተዘጋጀው ይህ ሰላማዊ ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ. ም በሀገሪቱ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ይካሄዳል ተብሏል፡፡ የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪዎች ደብዳቤውን ጦርነት እንዲቆም፣ መከላከያ ሠራዊቱ ከዘመተባቸው ክልሎች ወጥቶ ወደ ጦር ካምፑ እንዲመለስና ፖለቲካዊ ውይይቶች እንዲከፈቱ በሰልፉ ላይ እንጠይቃለንም ብለዋል፡፡ የኢትዮጰያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ /ኢህአፓ/ እና ሌሎች ዜጎች አስተባባሪነት የተጠራው ይህ ሰላማዊ ሰልፍ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት…