መነሻ ገፅ

ሶማሊያ የኢትዮጵያ አማጺያንን ልታስታጥቅ እንደምትችል አስጠነቀቀች

ሶማሊያ የኢትዮጵያ አማጺያንን ልታስታጥቅ እንደምትችል አስጠነቀቀች

ኢትዮጵያ ባሳለፍነው ጥር ወር ላይ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ጋር የወደብ ስምምነት ካደረገች በኋላ ከሶማሊያ ጋር ያላት ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ሻክሯል፡፡ የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አህመድ ሞዓሊም ፊኪ እንዳሉት ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ያደረገችውን ስምምነት ከተገበረች የትጥቅ ትግል እያደረጉ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን ታጣቂዎች ልንደግፍ እንችላለን ብለዋል፡፡ ሚኒስትሩ አክለውም “ስምምነቱ ከተተገበረ ታጣቂዎችን አልያም የኢትዮጵያን መንግስት ለመጣል የሚታገሉ አማጺያን ጋር ለመገናኘት እንሞክራለን” ብለዋል፡፡ “እስካሁን ታጣቂዎቹን ለማግኘት እየሞከርን አይደለም፣ ለችግሩ ሁሉ መፍትሄ ሊኖር እንደሚችል ተስፋ አለን” የሚሉት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ስምምነቱን ወደ መተግበር ከገባች ግን አማጺያኑን መርዳት የምችልበት መንገድ ይኖራል ሲሉ መናገራቸውን ቪኦኤ ዘግቧል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት ህወሃትን ትረዱ ነበር? በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄም “ተመካክረንበት ነበር፣ ነገር ግን…
Read More
ዮሀንስ አያሌው(ዶ/ር) የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ

ዮሀንስ አያሌው(ዶ/ር) የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ

ባለፈው ሳምንት ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ በጤና እክል ምክንያት ከሃላፊነት የለቀቁት ዮሀንስ አያሌው ብሩ (ዶ/ር)፣ የአማራ ባንክ አክሲዮን ማኅበር የዳይሬክተሮች ቦርድ  ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሸመዋል፡፡ የአማራ ባንክ በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ላይ እንዳጋራው ዩሀንስ አያሌው ከዛሬ መስከረም 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በዋና ስራ አስፈጻሚነት መሾማቸውን ገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ የግል ባንኮች ታሪክ በሰባት ቢሊዮን ብር መነሻ ካፒታል ከሁለት ዓመት በፊት ስራ የጀመረው የአማራ ባንክ 138 ሺህ ባለ አክስዮኖች የመሰረቱት የግል ባንክም ነው፡፡ ዮሐንስ አያሌው በልማት ባንክ የስራ ዘመናቸው ባንኩ ከነበረበት ውስብስብ ችግርና ክስረት  ወደ ተሻለ አቋም እንዲመለስ ማስቻላቸው ይታወሳል። በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ጠለቅ ያለ እውቀት እንዳላቸው የሚነገርላቸው ዶክተር ዮሀንስ አያሌው ከዚህ ቀደም…
Read More
የቀድሞ አትሌቶች በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አመራሮች ላይ ክስ አቀረቡ

የቀድሞ አትሌቶች በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አመራሮች ላይ ክስ አቀረቡ

የኢትዮጵያ ቦክስ እና ቴኒስ ፌዴሬሽን እንዲሁም ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ እና አትሌት ገዛኸኝ አበራ በጋራ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አመራሮች ላይ ክስ መስርተዋል። ክስ ከተመሰረተባቸው አመራሮች መካከል የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ፣ የኮሚቴው ዐቃቤ ነዋይዋ ዶ/ር ኤደን አሸናፊ ፣ ዋና ፀሐፊው አቶ ዳዊት አስፋው እና ምክትል ፀሐፊው አቶ ገዛኸኝ ወልዴ ዋነኞቹ ናቸው። ክሱን ተከትሎም የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ሁሉም የባንክ አካውንቶች በፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዳይንቀሳቀሱ ታግደዋልም ተብሏል፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ እና የኢትዮጵያ ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ክስ እንደቀረበባቸውም ይፋ ተደርጓል። በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እና በዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ ላይ ከተመሰረቱ ክሶች መካከል :- ባልተገባ መልኩ የሰው…
Read More
አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ሁለት ቋሚ ወንበር እንዲኖራት አሜሪካ ጠየቀች

አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ሁለት ቋሚ ወንበር እንዲኖራት አሜሪካ ጠየቀች

አሜሪካ አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ድጋፍ እንደምታደርግ ገልጻለች፡፡  በተመድ የአሜሪካ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ በምክር ቤቱ አፍሪካ ሁለት ቋሚ መቀመጫዎች እና ትናንሽ የደሴት ሀገራት አንድ ተለዋዋጭ ወንበር እንዲያገኙ ግፊት እያደረግን ነው ብለዋል፡፡   ጀርመን፣ ህንድ እና ጃፓን በምክር ቤቱ ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራቸው እየጠየቁ ከሚገኙ ሀገራት መካከል ናቸው፡፡ አምባሳደሯ አፍሪካ ቋሚ ውክልና እንዲኖራት አሜሪካ እንደምትደግፍ ቢናገሩም ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት አሁን ላይ ከሚገኙት አምስት አባል ሀገራት ውጪ እንዲሰጥ ዋሽንግተን ፍላጎት እንደሌላት ገልጸዋል፡፡   በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት ከፍተኛ ስልጣን ባለው የጸጥታው ምክር ቤት ውክልና እንዲኖራቸው መጠየቅ ከጀመሩ አመታት ተቆጥረዋል፡፡ ለበርካታ ጊዜያት በዚህ ጉዳይ ተደጋጋሚ ድርድር ቢደረገም ውጤታማ…
Read More
ሶማሊላንድ በሀርጌሳ የሚገኘው የግብጽ ባህላዊ ቤተ መጽሃፍትን ዘጋች

ሶማሊላንድ በሀርጌሳ የሚገኘው የግብጽ ባህላዊ ቤተ መጽሃፍትን ዘጋች

ራስ ገዟ ሶማሊላንድ በሀርጌሳ ያለው የግብጽ ባህላዊ ቤተ መጽሃፍት በቋሚነት እንዲዘጋ መወሰኗን ገልጻለች፡፡ የሶማሊላንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኤክስ አካውንቱ ለይ እንዳስታወቀው በሀርጌሳ ያለው የግብጽ ቤተ መጽሃፍት እንዲዘጋ የተወሰነ ሲሆን የቤተ መጽሀፍት ቤቱ ሰራተኞችም በ72 ሰዓት ውስጥ ሀርጌሳን ለቀው እንዲወጡ ታዘዋል፡፡ እንደ ሚኒስቴሩ መግለጫ ሶማሊላንድ ይህንን እርምጃ የወሰደችው ከደህንነት ጋር በተያያዘ ነው፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኢሳ ክዛ ሞሀሙድ ተቀማጭነታቸው በሀርጌሳ ላደረጉ የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች ስለ ሶማሊላንድ እና ኢትዮጵያ የወደብ ስምምነት ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል ተብሏል፡፡ ሚኒስትሩ ለዲፕሎማቶቹ ከኢትዮጵያ ጋር ያደረጉት የወደብ መግባቢያ ስምምነት የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ መድረሱን እና በቅርቡ የትግበራ ስምምነት እንደደረግ መናገራቸው ተገልጿል፡፡ ሚኒስትሩ አክለውም “የግብጽ ጦር በጎረቤት ሀገር ሶማሊያ መግባቱ…
Read More
በሀገር ክህደት ወንጀል የሞት ፍርድ ተወስኖባቸው የነበሩ 178 ወታደሮች በይቅርታ ተለቀቁ

በሀገር ክህደት ወንጀል የሞት ፍርድ ተወስኖባቸው የነበሩ 178 ወታደሮች በይቅርታ ተለቀቁ

ወታደሮቹ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እና አመራሮች የነበሩ ሲሆን አዲስ አመትን አስመልክቶ ይቅርታ ተደርጎላቸዋል ከሶስት ዓመት በፊት ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሀገር መከላከያ የሰሜን እዝ በህወሃት ታጣቂዎች መጠቃቱን ተከትሎ ነበር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተቀሰቀሰው፡፡ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ይህ ያልታሰበ ጥቃት እንዲደርስባቸው አቀነባብረዋል የተባሉ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እና አመራሮች በሀገር ክህደት ወንጀል ተጠርጥረው ታስረው ነበር፡፡ እነዚህ 178 ወታደሮች በተመሰረተባቸው ክስ ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተው የእድሜ ልክ እና ሞት ፍርድ ውሳኔ ተላልፎባቸው በእስር ላይ ነበሩ፡፡ በእስር ላይ የነበሩት የሠራዊት አባላቱ በፈፀሙት ወንጀል ተፀፅተው የይቅርታ ጥያቄአቸውን ለመንግስት እና ለመከላከያ ሚኒስቴር አሥገብተዋል ተብሏል። ወታደሮቹ የይቅርታ ጥያቄ ማስገባታቸውን ተከትሎ በአንድ በኩል ጉዳያቸው ለይቅርታ ቦርድ…
Read More
ግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ አዋጭነታቸው ያልተረጋገጡ ፕሮጀክቶችን እንዳትገነባ ኢትዮጵያ ጠየቀች

ግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ አዋጭነታቸው ያልተረጋገጡ ፕሮጀክቶችን እንዳትገነባ ኢትዮጵያ ጠየቀች

ኢትዮጵያ በጸጥታው ምክር ቤት በግብጽ ለቀረበባት ክስ ምላሽ ሰጥታለች ከአንድ ሳምንት በፊት ኢትዮጵያ በታላቁ ህዳሴ ግድብ አምስተኛው ዙር ውሃ ሙሌት ማከናወኗ እና ተጨማሪ ተርባይኖች ሀይል ማመንጨት መጀመራቸውን ይፋ ማድረጓ ይታወሳል፡፡ ይህን ተከትሎም ግብጽ ኢትዮጵያ በግድቡ ለይ የተናጠል እርምጃ ወስዳለች በሚል ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ክስ አስገብታለች፡፡ በግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተፈረመው ይህ ደብዳቤ ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2015 የተፈረመውን የመርህ ስምምነት ጥሳለች፣ ድርጊቱም ለአካባቢው ሀገራት አለመረጋጋት የሚሆን ነው፣ ግብጽ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ በተመድ ቻርተር አማካኝነት እርምጃ ትወስዳለች ሲልም ያትታል፡፡ ኢትዮጵያ በግብጽ ለቀረበባት ክስ በይፋ ባሳለፍነው ቅዳሜ ለተመድ ይፋዊ ምላሽ መስጠቷን አል ዐይን ከታማኝ ምንጮች አረጋግጧል፡፡ አል ዐይን የተመለከተው ይህ ደብዳቤ…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ ከሶስት ዓመት በፊት የተቀሰቃሰው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የአሜሪካንን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ይጎዳል በሚል ነበር ጦርነቱ እንዲቆም ጫና ስታደርግ የቆየችው፡፡ ይህ ጦርነት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በተደረገ የሰላም ስምምነት ቢቆምም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ግን እንደቀጠሉ ናቸው በሚል ማዕቀቡ ተራዝሟል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ እየተፈጸሙ ናቸው የተባሉት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ምስራቅ አፍሪካን እና አሜሪካንን ይጎዳል በሚል የተለያዩ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች፡፡ በዋሸንግተን ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል በኢትዮጵያ ላይ ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ ማዕቀብ የሚባል ሲሆን በፈረንጆቹ መስከረም 2021 ላይ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ማዕቀብ ተጥሎ ነበር፡፡ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ይህ ማዕቀብ ከአንድ ዓመት በፊት ለተጨማሪ አንድ ዓመት እንዲራዘም መፈረማቸው አይዘነጋም፡፡ ፕሬዝዳንቱ ፈርመውበት የነበረው…
Read More
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዮሀንስ አያሌው ከኃላፊነት ለቀቁ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዮሀንስ አያሌው ከኃላፊነት ለቀቁ

የልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዮሀንስ አያሌው ስራቸውን የለቀቁት "በፈቃዳቸውና በግል ምክንያት" መሆኑን ተናግረዋል። በተጠባባቂነት የባንኩ ምክትል ፕሬዝዳን ጌታቸው ዋቄ ሀለፊነቱን እንደተረከቡ ተገልጿል። ዮሀንስ አያሌው በስራ ዘመናቸው ባንኩ ከነበረበት ውስብስብ ችግርና ክስረት  ወደ ተሻለ አቋም እንዲመለስ ማስቻላቸውን የዘርፉ ባለሙያዎች ይመስክሩላቸዋል። በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ጠለቅ ያለ እውቀት እንዳላቸው የሚነገርላቸው ዶክተር ዮሀንስ አያሌው ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክን በምክትል ገዥነት እና በዋና ኢኮኖሚስትነት አገልግለዋል። በዚህም በገንዘብ ኢኮኖሚስትነታቸው ብዙዎች የሚያደንቋቸው ሲሆን ከአምስት አመት በፊት የኢትዮጵያ ልማት ባንክን በቦርድ አባልነት አገልግለዋል፡፡ የቀድሞው የልማት ባንኩ ፕሬዝዳንት ሀይለኢየሱስ በቀለ ሲለቁ የተኩት ዮሃንስ የባንኩ ፕሬዝዳንት በመሆን ለአራት አመታት የባንኩን ፖሊሲ  መርተዋል ሲል ዋዜማ ሬዲዮ ዘግቧል። የኢትዮጵያ ልማት ባንክን ዶክተር…
Read More
ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ የሚዘልቅ የነዳጅ መስመር ልገነባ ነው አለች

ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ የሚዘልቅ የነዳጅ መስመር ልገነባ ነው አለች

የተትረፈረፈ የነዳጅ ሀብት ካላቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ደቡብ ሱዳን ከዚህ በፊት ነዳጇን በሱዳን በኩል አድርጋ ለዓለም ገበያ ስታቀርብ ቆይታለች፡፡ ሱዳን በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ መሆኗን ተከትሎ እስከ ፖርት ሱዳን የተዘረጋው የደቡብ ሱዳን ነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር በጦርነቱ ወድሞባታል፡፡ በዚህም ምክንያት ሀገሪቱ በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ ወደብ ድረስ የተዘረጋ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት ማቀዷ ተገልጿል፡፡ በቻይና አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ሲሳተፉ የነበሩት ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ ወደብ ድረስ የሚዘረጋ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ዙሪያ መክረዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ ከቻይና ብሔራዊ ነዳጅ ኮርፖሬሽን ሃላፊ ዳይ ሁሊያንግ ጋር በቤጂንግ መምከራቸውን የደቡብ ሱዳን ዜና አገልግሎት ዘግቧል፡፡ እንደ ዘገባው ከሆነ የቻይናው ነዳጅ ኮርፖሬሽን…
Read More