15
Sep
ኢትዮጵያ ባሳለፍነው ጥር ወር ላይ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ጋር የወደብ ስምምነት ካደረገች በኋላ ከሶማሊያ ጋር ያላት ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ሻክሯል፡፡ የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አህመድ ሞዓሊም ፊኪ እንዳሉት ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ያደረገችውን ስምምነት ከተገበረች የትጥቅ ትግል እያደረጉ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን ታጣቂዎች ልንደግፍ እንችላለን ብለዋል፡፡ ሚኒስትሩ አክለውም “ስምምነቱ ከተተገበረ ታጣቂዎችን አልያም የኢትዮጵያን መንግስት ለመጣል የሚታገሉ አማጺያን ጋር ለመገናኘት እንሞክራለን” ብለዋል፡፡ “እስካሁን ታጣቂዎቹን ለማግኘት እየሞከርን አይደለም፣ ለችግሩ ሁሉ መፍትሄ ሊኖር እንደሚችል ተስፋ አለን” የሚሉት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ስምምነቱን ወደ መተግበር ከገባች ግን አማጺያኑን መርዳት የምችልበት መንገድ ይኖራል ሲሉ መናገራቸውን ቪኦኤ ዘግቧል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት ህወሃትን ትረዱ ነበር? በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄም “ተመካክረንበት ነበር፣ ነገር ግን…