መነሻ ገፅ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቤይሩት እና ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቤይሩት እና ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ

ለፍልስጤም ነጻነት የሚታገለው ሐማስ በእራኤል ላይ ድንገተኛ ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ በመካከለኛው ምስራቅ የተጀመረው ጦርነት አንድ ዓመት ሞልቶታል፡፡ ይህ ጦርነት ወደ ሊባኖስ መስፋፋቱን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በርካታ ዓለማችን አየር መንገዶች ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚያደርጓቸውን በረራዎች አቋርጠዋል፡፡ ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ወደ ቤይሩት እና ወደ ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ በጊዜያዊነት ማቋረጡን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል። አየር መንገዱ በድረገ ገጹ ባጋራው መረጃ ተለዋጭ ማስታወቂያ እስከሚያወጣ ድረስ ወደ ቤይሩት የሚያደርጋቸውን ሁሉንም በረራዎች ማቋረጡን ገልጿል። ወደ ቴልአቪቭ ደግሞ እስከ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በረራ የማያደርግ መሆኑን ነው አየር መንገዱ የገለጸው። በተጠቀሱት አካባቢዎች ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን የጠቀሰው አየር መንገዱ፤ ስለጉዳዩ…
Read More
ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለአንድ ዓመት ዝም ብለው መቆየታቸው ተናገሩ

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለአንድ ዓመት ዝም ብለው መቆየታቸው ተናገሩ

ፕሬዝዳንቷ በX ወይም በቀድሞው ትዊተር ገጻቸው ላይ ባጋሩት ጽሁፍ ላይ "ዝምታ ነው መልሴ" የሚል ጽሁፍ አጋርተዋል። ለምን ዝም እንዳሉ በጽሁፋቸው ላይ ያልገለጹት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ " እነ ጥላሁን ገሰሰ፣ ቴዲ አፍሮ፣ አሊ ቢራ ፣ማህሙድ አክመድ ... ድንቅ ድምጻዊያን መካከል ናቸው። ሲሉም አክለዋል። ፕሬዝዳንቷ የማህሙድ አህመድ ዘፈንን በሚያስታውሰው "የሰው ልጅ ሆዱ ሲከፋው ጊዜም እንደሰው ሲገፋው፣ መሄጃ መውጫ ሲጠፋው ዝምታ ብቻ ነው ተስፋው" የሚለውን ግጥምም በጽሁፋቸው ላይ ጠቅሰው አጋርተዋል። ዝምታን "ለአንድ ዓመት ሞከርኩት" ያሉት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ምን ደርሶባቸው እንደከፋቸው፣ ለምን እንደከፋቸው እና ለምን ዝም እንዳሉ ከመጥቀስ ተቆጥበዋል። የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት በበኩሉ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ያጋሩት ጽሁፍ የግላቸው እንጂ የጽህፈት ቤቱ እንዳልሆነ ጠቅሷል። ኢትዮ…
Read More
ሶማሊያ ኢትዮጵያ ግድቦችን በመልቀቅ በውሃ እንድጥለቀለቅ እያደረገች ነው ስትል ከሰሰች

ሶማሊያ ኢትዮጵያ ግድቦችን በመልቀቅ በውሃ እንድጥለቀለቅ እያደረገች ነው ስትል ከሰሰች

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ኢትዮጵያ ሆን ብላ ጎርፍ እንዲፈጠር ውሃ እየለቀቀች ነው ሲሉ ከሰዋል፡፡ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሃሙድ ኢትዮጵያ “በሶማሊያ ጎርፍ እንዲከሰት ሆን ብላ ከግድቦቿ ውሃ እየለቀቀች ነው” ሲሉ  ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ ከዘኢኮኖሚስት ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ፤ በሶማሊያ በጎርፍ የተጥለቀለቁ አካባቢዎችን ፎቶግራፎች አቅርበው፤ አደጋው ኢትዮጵያ ሆን ብላ ያደረገችው ነው ሲሉ ከሰዋል። ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሃሙድ ኢትዮጵያ በድንበር አቅራቢያ “በጎሳ ለተመሰረቱ ለሶማሊያ ሚሊሻዎች ትጥቅ እያስተላለፈች ነው” ሲሉም ተጨማሪ ክስ አቅርበዋል። እነዚህ መሳሪያዎች በሶማሊያ በሚንቀሳቀሰው “በአልሸባብ እጅ ሊወድቁ ይችላሉ” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል። አክለውም ኢትዮጵያ “የግብፅ ወታደሮች ስምሪትን እንዲቃወሙ በሶማሊያ ውስጥ ያሉ የጎሳ መሪዎችን እና የተቃዋሚ ፖለቲከኞችን እያበረታታች ነው” ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ባሳለፍነው ጥር ወር…
Read More
በውጭ ሀገራት የተቀጠሩ ኢትዮጵያዊያንን ደህንነት ለማስከበር ያለመ ስምምነት ተፈረመ

በውጭ ሀገራት የተቀጠሩ ኢትዮጵያዊያንን ደህንነት ለማስከበር ያለመ ስምምነት ተፈረመ

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽንና የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሠሪ ፌዴሬሽን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመዋል፡፡ ስምምነቱ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሠሪ ፌዴሬሽን በውጭ ሀገር በሥራ የሚሰማሩ ዜጎችን መብት እና ደህንነት ለማስጠበቅ ያለመ ነው፡፡ በስምምነቱ ወቅት የፌዴሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት ፣የዓለም ሥራ ድርጅት ተወካይ እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ በፊርማው ሥነ-ስርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ኮንፌዴሬሽኑ በሀገር ውስጥ በተለያዩ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኞች መብቶች እንዲከበሩ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡ ከሀገር ውስጥ በተጨማሪም በውጭ ሀገራት ተቀጥረው የሚሠሩ ኢትዮጵያዊን መብታቸው ተጠብቆ እዲሠሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ…
Read More
በአማራ ክልል ከተሞች ሰዎች በዘመቻ እየታሰሩ መሆኑ ተገለጸ

በአማራ ክልል ከተሞች ሰዎች በዘመቻ እየታሰሩ መሆኑ ተገለጸ

ዋና መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገው አምንስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ በተለይም በአማራ ክልል ዋና ዋና ከተሞች አዲስ እስር እየተካሄደ እንደሆነ አስታውቋል፡፡ ከመስከረም 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የመንገስት የጸጥታ ሀይሎች ዜጎችን ከህግ ውጪ እየያዙ እያሰሩ መሆኑንም ተቋሙ በሪፖርቱ ለይ ጠቅሷል፡፡ በአምንስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ዳይሬክተር ትግሬ ቻጉታህ እንዳሉት “የኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ንጹሃንን ከህግ ውጪ በዘመቻ ማሰር መጀመራቸው መንግስት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ፍላጎት እንደሌለው ማሳያ ነው” ብለዋል፡፡ ተቋሙ የአይን እማኞችን ጠቅሶ ባወጣው በዚህ ሪፖርቱ ላይ እንደገለጸው ለእስር የተዳረጉ ንጹሃን ህጉ በሚፈቅደው መሰረት በ48 ሰዓት ውስጥ ወደ ፍርድ ቤት እየቀረቡ አለመሆኑንም አስታውቋል፡፡ መንግስት ጀመረው በተባለው የዘመቻ እስር በክልሉ ባሉ ከተሞች የሚገኙ መምህራን እና…
Read More
ኢትዮጵያ ለአምስት ተቋማት የውጭ ምንዛሬ ቢሮ የስራ ፈቃድ ሰጠች

ኢትዮጵያ ለአምስት ተቋማት የውጭ ምንዛሬ ቢሮ የስራ ፈቃድ ሰጠች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለአምስት ባንክ ላልሆኑ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች የስራ ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ አገልግሎት እና ተደራሽነት ለማስፋት ከባንክ ጋር ከተያያዙ የውጭ ምንዛሬ ቢሮዎች በተጨማሪ ከባንክ ጋር ዝምድና የሌላቸው የግል የውጪ ምንዛሬ ቢሮዎችን ለመክፈት የሚያስችል የውጭ ምንዛሬ መመሪያ አውጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት አምስት የግል የውጭ ምንዛሬ ቢሮዎች መስፈርት በማሟላታቸው የስራ ፍቃድ እንደተሰጣቸው ባንኩ ገልጿል፡፡ ፈቃድ ከተሰጣቸው ድርጅቶች መካከል ዱግዳ ፊደሊቲ ኢንቨስትመንት፣ ኢትዮ ኢንዲፔንደንት፣ ግሎባል፣ ሮቡስት እና ዮጋ ፎርኤክስ የተባሉ የግል የውጪ ምንዛሬ ቢሮዎች ናቸው፡፡ በመሆኑም ቢሮዎቹ ሙሉ ተቀባይነት ያላቸው እና የውጭ ሀገር ጥሬ ገንዘቦችን በመግዛት እና በመሸጥ እንዲሁም ከባንኮች ጋር በመቀናጀት ለወጪ እና ገቢ ንግድ የሚውል የውጭ ምንዛሬ…
Read More
ኢትዮጵያዊያን ታዳጊዎች በዓለም አቀፍ የሮቦት ውድደር ላይ አሸነፉ

ኢትዮጵያዊያን ታዳጊዎች በዓለም አቀፍ የሮቦት ውድደር ላይ አሸነፉ

195 ሀገራት በተሳተፉበት የሮቦቲክስ ውድድር ተሳታፊ የነበሩት ኢትዮጵያዊያን ታዳጊዎች አሸናፊ ሆነዋል፡፡ ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት የተወጣጡ እድሜያቸዉ ከ14 እስከ 18 የሆኑ 5 ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች ከመስከረም 14 እስከ 20 በግሪክ በተከሄደው ዓለም አቀፉ የሮቦቲክስ ውድድር ላይ ተሳትፈዋል፡፡ ከ195 በላይ ሀገራት በሚያሳትፈዉ የሮቦቲክስ ዉድድር  ኢትዮጵያን ወክለዉ ችግሮችን እንዴት መፍታት ይችላሉ የሚለው ላይ ትኩረት አድርገው  በውድድር ላይ ተሳትፈዋል፡፡ ተወዳዳሪዎቹ በ2024 የፈርስት ግሎባል የሮቦቲክስ ቻሌንጅ  ተማሪዎች  በሮቦቲክስ  በኩል  በሳይንስ፣  በቴክኖሎጂ ፣ በምህንድስና እና በሂሳብ  መስኮች  ማበረታት  ዓላማ ባደረገው የወደ ፊቱን መመገብ የሚል መርህ ያለው ውድድር ላይ ተሳትፈዋል፡፡ ይህ ጭብጥ የሚያተኩረው የአለም የምግብ ዋስትናን እና ዘላቂ የግብርና አሰራሮችን መፍታት ላይ  መሆኑንም ተወዳዳሪዎቹ ተናግረዋል። ኢትዮጲያን የወከሉት ተወዳዳሪዎች ካሌብ ኤርሚያስ፣…
Read More
አቶ አንዷለም አድማሴ ሳፋሪኮምን ተቀላቀሉ

አቶ አንዷለም አድማሴ ሳፋሪኮምን ተቀላቀሉ

የኢትዮ ቴሌኮም የቀድሞው ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አንዷለም ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ተቀላቅለዋል፡፡ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እንዳስታወቀው የቀድሞውን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አንዷለም አድማሴን የውጭ ግንኙነት ሃላፊው ሆነው መሾማቸውን አስታውቋል። አንዷለም የኩባንያው የውጭ ግንኙነት ሃላፊ ኾነው የተሾሙት፣ የቀድሞው ሃላፊ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራ ሻወል ከኩባንያው ለቀው ቦይንግ ኩባንያን መቀላቀላቸውን ተከትሎ ነው። አንዷለም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ደቡብ ሱዳን ውስጥ ከሌሎች ግለሰቦች ጋር ያቋቋሙትን አንድ አዲስ የቴሌኮም ኩባንያ በሃላፊነት በመምራት ላይ ነበሩ:: ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የቴሌኮም አገልግሎት ነሀሴ 2014 ዓ.ም ላይ በድሬዳዋ ማስጀመሩ ይታወሳል፡፡ ድርጅቱ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ውስጥ ለ50 በመቶ ህዝብ እንዲሁም በቀጣዮቹ አስር ዓመታት ውስጥ ደግሞ 98 በመቶ ለሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን የቴሌኮም አገልግሎት…
Read More
የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያን በመልቀቅ ወደ ጎረቤት ሀገራት እየተሰደዱ ነው ተባለ

የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያን በመልቀቅ ወደ ጎረቤት ሀገራት እየተሰደዱ ነው ተባለ

በኢትዮጵያ የሚገኙት በርካታ የቻይና ባለሃብቶች በሀገሪቱ እያጋጠመን ይገኛል ባሉት ተግዳሮቶች ወደ ጎረቤት ሀገራት እየሄዱ መሆኑን ገለፁ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ላይ ቀዳሚ የሆኑት የቻይና ባለሀብቶች እና ኩባንያዎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ወደ ሌሎች ሀገራት እየተሰደዱ መሆኑን ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ዋነኛ ተዋናይ የሆኑት የቻይና ባለሃብቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያጋጠማቸው በመንግስት አመቺ የስራ ሁኔታዎች እየተሰጠ ባለመሆኑ ወደ ጎሮቤት ሃገራት ማለትም ወደ ኬንያ ፣ ኡጋንዳ እንዲሁም ታንዛኒያ እያማተሩ እንደሚገኙ ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል። በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ተወካይ እንደተናገሩት በብዙ ምክንያቶች ቻይናውያን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ያላቸውን ንግዳቸውን ወደ ጎሮቤት አገሮች አዙረዋል ። "ይህ ለኤምባሲው ብቻ ሳይሆን ለሀገርም ትልቅ ስጋት ነዉ ምክንያቱም የእኛ ተልዕኮ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለዉን ትብብር…
Read More
ኢትዮጵያ ግዙፉን የሲሚንቶ ፋብሪካ አስመረቀች

ኢትዮጵያ ግዙፉን የሲሚንቶ ፋብሪካ አስመረቀች

አዲሱ የሲሚንቶ ፋብሪካ በቀን አንድ መቶ ሃማሳ ሺህ ኩንታል ሲሚንቶ የማምረት አቅም አለው ተብሏል፡፡ ፋብሪካው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል፡፡ ፋብሪካው በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ልዩ ቦታው ለሚ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የተገነባ ሲሆን ፋብሪካው ከአዲስ አበባ በ134 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ነው። ተገንብቶ ለመጠናቀቅ ሁለት አመታትን ብቻ የወሰደው ፋብሪካ ዘመናዊ የሆነ ከሰው ንክኪ የራቀ ቴክኖሎጂ የሚጠቀም በመሆኑ የበለጠ ምርት ለማምረት የቀነሰ ኃይል የሚያስፈልገው ነው ተብሏል። በተለይም 174 ሜትር ርዝመት ያለው በአለም ረዥሙ የሆነውን የቅድመ ማሞቂያ ማማ እንደያዘ በምረቃው ወቅት ተገልጿል። የፋብሪካው የማምረት አቅም ከዚህ በፊት በማምረት ላይ ያሉ ተመሳሳይ ፋብሪካዎች ተደምረው የሚያመርቱትን ሃምሳ…
Read More