መነሻ ገፅ

ቱርክ የኢትዮጵያ ሁለተኛዋ የንግድ እና ኢንቨስትመንት አጋር ሆነች

ቱርክ የኢትዮጵያ ሁለተኛዋ የንግድ እና ኢንቨስትመንት አጋር ሆነች

የኢትዮጵያና የቱርክ የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነትን የሚያጠናከር የቢዝነስ ኮንፈረንስ እና ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በቱርኩ የአለም አቀፍ የኢንዱስትሪ ትብብር ፎረም/ World Cooperation of Industries Forum-WCI Forum/ / እና በአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አማካኝነት የተሰናዳው ስምንተኛው የ ደብሊው ሲአይ / WCI የቢዝነስ ፎረም ዛሬ ተጀምሯል፡ ፡ በንግድ ፎረሙ ላይ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር  ዘለቀ ተመስገን፤ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት/ አዲስ ቻምበር/ ፕሬዚዳንት  ዘሀራ መሀመድ፤ የዲፕሎማቲክ እና የንግዱ ማህበረሰብ እና  ሌሎች ጥሪ ተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል፡ ፡ በመድረኩ ላይ መልእክታቸውን ያስተላለፉት የአዲስ ቻምበር ዋና ፀሀፊ መሰረት ሞላ የኢትዮጵያ እና የቱርክ አመታዊ የንግድ ልውውጥ መጠን እ.አ.አ በ2023 ከ…
Read More
ሻኩራ ፕሮዳክሽን የቻይና አምባሳደር ከተሰኘው ተቋም ጋር ስምምነት ፈጸመ

ሻኩራ ፕሮዳክሽን የቻይና አምባሳደር ከተሰኘው ተቋም ጋር ስምምነት ፈጸመ

በካሙዙ ካሳ የተቋቋመው ሻኩራ ፕሮዳክሽን የኢትዮጵያን ባህል ለማስተዋወቅ ከቻይና አምባሳደር ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። በቤጂንግ ከተማ የተፈረመው ይህ ስምምነት የኢትዮጵያን ባህል ለማስተዋወቅ ወደ ቤጂንግ ያቀናው "ኢትዮ ኪን" ባህል ቡድን አንድ አካል ነው። በስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ተቋማት የኢትዮጵያን እና ቻይናን ባህል፣ ኪነ ጥበብ፣ ትምህርት እና ሌሎች የመልካም ገጽታ ማስተዋወቅ ስራዎችን በጋራ ይሰራሉ ተብሏል። የቻይናው የባህል እና ሚዲያ አገናኝ ኩባንያ ፕሬዝዳንት የሆኑት ሚንግዙ ዛንግ በስምምነቱ ወቅት እንዳሉት "የአባይ ወንዝ መገኛ፣ ቡና መገኛ፣ ታላቅ ህዝብ እና ሀገር የሆነችው ኢትዮጵያ ባህል ለማስተዋወቅ እንፈልጋለን" ብለዋል። "የቻይና ባህል ባለፈው ታሪክ ላይ ብቻ የተመሰረተ አይደለም" ያሉት ፕሬዝዳንቱ ከፈጠራ ጋርም እንደሚያያዝ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም በቀጣይ የጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ…
Read More
ኢትዮጵያ በአሜሪካ ታሪፍ ምክንያት አማራጭ የቡና መዳረሻ እየፈለገች መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ በአሜሪካ ታሪፍ ምክንያት አማራጭ የቡና መዳረሻ እየፈለገች መሆኗን ገለጸች

የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳድር ኢትዮጵያን ጨምሮ በብዙ የዓለማችን ሀገራት ላይ አዲስ ታሪፍ መጣላቸው ይታወሳል። አዲሱ ታሪፍ ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልከው ጠቅላላ ምርት ላይ የ35 በመቶ ገቢ እንዲቀንስ የሚያደርግ እንደሆነ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ምክትል ዳይሬክተር ሻፊ ዑመር የአሜሪካ አስተዳደር ፖሊሲ ከሀገሪቱ የወጪ ንግድ ገቢ 35 በመቶ የሚሆነውን የሚነካ ነው ብለዋል። በዚህ ምክንያትም ከአሜሪካ ባለፈ አማራጭ የውጭ ገበያዎችን በመመልከት ላይ መሆናቸውንም ሻፊ ተናግረዋል። ይህንን ተከትሎም የኢትዮጵያን ቡና ወደ ሩቅ ምስራቅ እና መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የማስፋት እቅድ ተይዟል ተብሏል። በተያዘው በጀት ዓመት ውስጥም 20 አዳዲስ የቡና ወጪ ንግድ መዳረሻዎችን የመክፈት እቅድ እንደተያዘም ተገልጿል። እንዲሁም ዋነኛ የኢትዮጵያ ቡና ገዢ ወደ ሆኑት ቻይና፣ ጃፓን፣…
Read More
ሴኔጋላዊው አል ሀጂ ዲዮፍ የዋናው ስፖርት ኩባንያ አምባሳደር ሆነ

ሴኔጋላዊው አል ሀጂ ዲዮፍ የዋናው ስፖርት ኩባንያ አምባሳደር ሆነ

የሴኔጋሉ የእግር ኳስ ኮኮብ አልሀጂ ዲዩፍ በኢትዮጵያ ላለ አንድ የስፖርት ትጥቅ አልባሳት አምራች ኩባንያ አምባሳደር ሆነው ተሹመዋል። ስምምነቱ በአዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን "ከአፍሪካ ምርጡ ትጥቅ አምራች ጋር ስምምነት ፈፅሜያለሁ “ ብሏል ዲዩፍ። ሴኔጋላዊው የቀድሞ ታሪካዊ ተጨዋች ኤል ሀጂ ዲዩፍ የኢትዮጵያው ትጥቅ አምራች ብራንድ ዋናው አምባሳደር በመሆን መሾሙን ኩባንያው ገልጿል። ታሪካዊው ተጫዋች የዋናው ስፖርት አልባሳት በሚመረትበት አዲስ አበባ ሀብቴ ጋርመንት እና ህትመትን ከጎበኘ በኋላ ስምምነት ፈፅሟል። “ ከአፍሪካ ምርጡ ትጥቅ አምራች ጋር ስምምነት ፈፅሜያለሁ “ ሲል ዲዩፍ ከጉብኝቱ በኋላ ተናግሯል። አክሎም  "በቀጣይ ከትልልቅ ታሪካዊ ተጫዋቾች ጄጄ ኦኮቻ ፣ ኑዋንኩ ካኑ ፣ አዲባየር እና ካሊዱ ፋዲጋን በማምጣት ዋናውን በአለም ገናነቱን እናሳየለን "…
Read More
ኢትዮጵያ የምርጫና ፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ህጓን አሻሻለች

ኢትዮጵያ የምርጫና ፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ህጓን አሻሻለች

ሀገራዊ ፓርቲ ለመሆን በስድስት ክልሎች የድጋፍ ፊርማ ማሰባሰብን የሚያስገድደዉ አዋጅ ፀድቋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ የምርጫ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል። አዋጁ ከነባሩ አዋጁ 1162/2011ዉስጥ የነበሩ 26 አንቀጾችን ያሻሻለ ሆኖ የቀረበ ነዉ ተብሏል። አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመወዳደር ከ 6 ክልሎች የ60 በመቶ ድጋፍ ፊርማ ማሰባሰብን የሚያስገድድ አንቀፅ ይገኝበታል። ከዚህ ቀደም ሀገራዊ ፓርቲ ለመሆን የአራት ክልሎች የድጋፍ ፊርማ የሚያስፈልግ ሲሆን ይህንን አንቀፅ ለማሻሻል ያስፈለገበት ምክንያት የተጨመሩ ክልሎች መኖራቸዉን ታሳቢ አድርጎ መሆኑን ምክር ቤቱ ገልጿል። በዚህ መሰረት ሀገራዊ ፓርቲ ለመመስረት በስድስት ክልሎች የድርጅት አባል ማፍራት እንዳለባቸዉ የሚያደርግ ነዉ። አንድ የምክር ቤት አባል የሀገራዊ ፓርቲ ምስረታን…
Read More
በአንድ ዓመት ውስጥ ከ1.4 ሚሊዮን በላይ ፓስፖርት መሰጠቱ ተገለጸ

በአንድ ዓመት ውስጥ ከ1.4 ሚሊዮን በላይ ፓስፖርት መሰጠቱ ተገለጸ

የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ2017 በጀት ዓመት ለ1.4 ሚሊዮን ዜጎች ፓስፖርት መስጠቱን አስታውቋል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት እንዳሉት ለፓስፖርት አመልካቾች የተቀላጠፈ አገልግሎት በመሰጠቱ ምክንያት የአመልካቾች ቁጥር ቀንሷል ብለዋል። ተቋሙ የኢ-ፓስፖርት ለመስጠት ያስቀመጠውን እቅድ በአዲስ አበባ ጎተራ ባለው ቅርንጫፍ ማስጀመሩም ተገልጿል። ይሁንና ተቋሙ ፓስፖርት ቤት ለቤት መስጠት እጀምራለሁ በሚል የያዘው እቅድ እስካሁን ስለመጀመሩ ዳይሬክተሯ አልገለጹም። ይህ በዚህ እንዳለም የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከ3800 በላይ ሰዎች በተጭበረበረ ሰነድ ፓስፖርት ለማውጣት ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል ተብሏል። ተቋሙ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ፓስፖርት ለማግኘት የሚሞክሩ ሰዎችን የመቆጣጠሩ አቅሙ ያደገው ተቋማዊ ደህንነትን የማረጋጫ ሥርዓት ዘርግቷልም ተብሏል።  ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ከሰራተኞች ጋር በመመሳጠር ተገልጋዮችን በማጉላላት እና…
Read More
መንግስት ከግምጃ ሰነድ ግዢዎች 173 ቢሊዮን ብር እንደሚሰበስብ ገለጸ

መንግስት ከግምጃ ሰነድ ግዢዎች 173 ቢሊዮን ብር እንደሚሰበስብ ገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን፣ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ማዕከላዊ ግምጃ ቤት ሰነዶች ሽያጭን በይፋ አስጀምረዋል። የገንዘብ ሚንስቴር ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በዚህ ጊዜ እንዳሉት መንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ የግምጃ ቤት ሰነዶችን ለገበያ ማቅረቡን ተናግረዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት ውስጥ መንግስት ከበጀተው 1.9 ትርሊዮን ብር ውስጥ 188 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት እንዳለበት ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ ከገጠመው የበጀት ጉድለት ውስጥም 173 ቢሊዮን ብሩን ግምጃ ቤት ሰነድ ለሽያጭ በማቅረብ ለመሰብሰብ መታቀዱንም አቶ አህመድ ተናግረዋል፡፡ የሀገር ውስጥ ብድሩ ከሰነድ ገዢዎች የሚሰበሰበው የዋጋ ግሽበትን በማያባብስና የማክሮ ኢኮኖሚውን በማያናጋ መልኩ እንደሚሆንም ገልጸው ነባር የግምጃ ሰነዶችን ወደ ኤሌክትሮኒክስ መንገድ ስራዎች እየተቀየሩ መሆኑን፣ አዳዲስ ግምጃ ሰነዶችም በዚህ መልኩ ለገበያ ይቀርባሉም…
Read More
ቻይና የኢትዮጵያን አኩሪ አተር ወደ ሀገሯ እንዲገባ ፈቀደች

ቻይና የኢትዮጵያን አኩሪ አተር ወደ ሀገሯ እንዲገባ ፈቀደች

የቻይና ጉምሩክ ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ቻይና ከአሜሪካ ጋር እየተካረረ የመጣውን የንግድ ውጥረት ተከትሎ የፕሮቲን አቅርቦቶቿን ለማስፋት ባላት ፍላጎት ከኢትዮጵያ የሚገቡ የአኩሪ አተር ምርቶችን እንዲገቡ ፈቃድ መስጠቷን ኒውስ ሴንትራል ዘግቧል። የኢትዮጵያ አኩሪ አተር ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ ወደ ቻይና እንዲገቡ ተፈቅደዋል። ቻይና ለአገር ውስጥ የአኩሪ አተር ምርት በአብዛኛው በአኩሪ አተር ምርቶች ከብራዚል እና ከአሜሪካ ታስመጣለች። ቻይና በሰኔ ወር ከኡራጓይ የሚገቡ የአኩሪ አተር ምርቶች እንዲገቡ ፈቅዳለች፤ ኢትዮጵያ ደግሞ አሁን  ሩሲያ፣ ቤላሩስ፣ አርጀንቲና እና ብራዚልን ጨምሮ እውቅና የተሰጣቸውን የአቅራቢዎች ዝርዝርን  ተቀላቅላለች። ቻይና የኢትዮጵያ ቁጥር አንድ የንግድና ኢንቨስትመንት አጋር ስትሆን ዓመታዊ የንግድ ልውውጥ መጠን ከአራት ቢሊዮን ዶላር በላይ ደርሷል። ኢትዮጵያ በተለይም ባለፉት ሶስት ዓመታት ውስጥ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ የጣለውን አስገዳጅ የቦንድ ግዥ አነሳ

ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ የጣለውን አስገዳጅ የቦንድ ግዥ አነሳ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በሁሉም ንግድ ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ መወሰኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ባደረገው ውይይት የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል። ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ (Treasury Bond) እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (MFAD/TRBO/001/2022) እንዲነሳ ያሳለፈው ወሳኔ ተጠቃሽ ነው። "አሁን ላይ የመንግሥት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉ፣ እንዲሁም መንግሥት የበጀት ጉድለቱን ለሟሟላት የውጭና ገበያ መር የሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ በባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየውን ይህ አስገዳጅ መመሪያ አሁን ላይ ማንሣቱ ተገቢ መሆኑን ኮሚቴው አምኖበታል" ሲል መግለጫው ጠቅሷል። ኮሚቴው ያመነበት ይህ የገንዘብ…
Read More
ኢትዮጵያ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ የመላክ እቅዷን ሰረዘች

ኢትዮጵያ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ የመላክ እቅዷን ሰረዘች

መንግስት  ከኦጋዴን ተፋሰስ የተፈጥሮ ጋዝ በጅቡቲ በኩል በቧንቧ መስመር ወደ ውጭ የመላክ እቅዱን የገንዘብ እጥረትና የትግበራ መጓተትን በመጥቀስ በይፋ ሰርዟል። በኢትዮጵያ ኢነርጂ አውትሉክ 2025 የተረጋገጠው ይህ ስረዛ፣ በሀገራዊ የኢነርጂ ፖሊሲ ውስጥ ትልቅ ለውጥ የሚያሳይ ሲሆን፣ ከውጭ የመላክ ፍላጎት ወደ ሀገር ውስጥ አጠቃቀም እየተሸጋገረ መሆኑን ያመለክታል ሲል ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። “የኢትዮጵያ መንግስት በኦጋዴን ክልል የታቀደውን የተፈጥሮ ጋዝ ማውጣት እና የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ ለመላክ ወደ ጅቡቲ የሚዘረጋውን የቧንቧ መስመር ፕሮጀክት ሰርዟል” ሲል ሪፖርቱ ይገልጻል። በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና በነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በጋራ የተዘጋጀው የኢነርጂ አውትሉክ “የፕሮጀክት ፋይናንስን በማግኘት ረገድ ያሉ ችግሮች እና የፕሮጀክት ትግበራ…
Read More