Beijing

ሻኩራ ፕሮዳክሽን የቻይና አምባሳደር ከተሰኘው ተቋም ጋር ስምምነት ፈጸመ

ሻኩራ ፕሮዳክሽን የቻይና አምባሳደር ከተሰኘው ተቋም ጋር ስምምነት ፈጸመ

በካሙዙ ካሳ የተቋቋመው ሻኩራ ፕሮዳክሽን የኢትዮጵያን ባህል ለማስተዋወቅ ከቻይና አምባሳደር ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። በቤጂንግ ከተማ የተፈረመው ይህ ስምምነት የኢትዮጵያን ባህል ለማስተዋወቅ ወደ ቤጂንግ ያቀናው "ኢትዮ ኪን" ባህል ቡድን አንድ አካል ነው። በስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ተቋማት የኢትዮጵያን እና ቻይናን ባህል፣ ኪነ ጥበብ፣ ትምህርት እና ሌሎች የመልካም ገጽታ ማስተዋወቅ ስራዎችን በጋራ ይሰራሉ ተብሏል። የቻይናው የባህል እና ሚዲያ አገናኝ ኩባንያ ፕሬዝዳንት የሆኑት ሚንግዙ ዛንግ በስምምነቱ ወቅት እንዳሉት "የአባይ ወንዝ መገኛ፣ ቡና መገኛ፣ ታላቅ ህዝብ እና ሀገር የሆነችው ኢትዮጵያ ባህል ለማስተዋወቅ እንፈልጋለን" ብለዋል። "የቻይና ባህል ባለፈው ታሪክ ላይ ብቻ የተመሰረተ አይደለም" ያሉት ፕሬዝዳንቱ ከፈጠራ ጋርም እንደሚያያዝ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም በቀጣይ የጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ። አየር መንገዱ ወደ ሻንግሀይ ከተማ የካቲት 1973 የመጀመሪያ የቻይና በረራውን በማድረግ አገልግሎቱን የጀመረ ሲሆን ከጥቅምት 1973 ጀምሮ ደግሞ መዳረሻውን ወደ ቤጂንግ ከተማ በመቀየር አገልግሎን ቀጥሏል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት በ5 የመንገደኛ እና 9 የእቃ ጭነት መደበኛ በረራዎች በአጠቃላይ 66 ሳምንታዊ በረራዎችን ወደ 10 የቻይና ከተሞች በማድረግ ላይ ይገናል። ቤጂንግ፣ ጓንዡ፣ ሼንጁ፣ሻንግሀይ፣ ሸንዘን ፣ ውሀን፣ቻንግሻ፣ዢያመን፣ቸንዱ እና ሆንግ ኮንግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚበርባቸው የቻይና ከተሞች ናቸው። የአፍሪካ ግዙፍ የአቪዬሽን ተቋም የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች አሉት። በ1945 የተመሰረተው የኢትዮጵያ አየር መንገድ 70ኛ የምስረታ በዓሉን ከአንድ ዓመት በፊት…
Read More