15
Aug
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሁለት ሳምንት በፊት በሚንስትሮች ምክር ቤት የተወሰነውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጽድቋል። ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት የቀድሞው የጠቅላይ ሚንስትሩ የደህንነት አማካሪ፣ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር እና የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለምክር ቤቱ አባላት ንግግር አድርገዋል። አቶ ገዱ ከሌሎች የምክር ቤቱ አባላት ለየት ባለ መልኩ በአማራ ክልል ስላለው ሁኔታ ባደረጉት ንግግር ከምክር ቤቱ አባላት ተቃውሞ ገጥሟቸው ተቋርጧል። አቶ ገዶ ንግግራቸው እስከተቋረጠበት ጊዜ ድረስ ባደረጉት ንግግር " ብልጽግና መራሹ መንግሥት ራሱ የፖለቲካ ችግር እየፈጠረ ነው" ብለዋል። "ፓርቲው የፈጠረውን የፖለቲካ ችግር ለመፍታት የሚሞክረው ከፖለቲካዊ መፍትሄ ይልቅ ወታደራዊ መፍትሄ ሆኗል" የሚሉት አቶ ገዱ ብልጽግና ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ…