Blog

የጠቅላይ ሚንስትሩ የቀድሞ አማካሪ በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ በሀይል እንደማይፈታ ተናገሩ

የጠቅላይ ሚንስትሩ የቀድሞ አማካሪ በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ በሀይል እንደማይፈታ ተናገሩ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሁለት ሳምንት በፊት በሚንስትሮች ምክር ቤት የተወሰነውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጽድቋል። ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት የቀድሞው የጠቅላይ ሚንስትሩ የደህንነት አማካሪ፣ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር እና የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለምክር ቤቱ አባላት ንግግር አድርገዋል። አቶ ገዱ ከሌሎች የምክር ቤቱ አባላት ለየት ባለ መልኩ በአማራ ክልል ስላለው ሁኔታ ባደረጉት ንግግር ከምክር ቤቱ አባላት ተቃውሞ ገጥሟቸው ተቋርጧል። አቶ ገዶ ንግግራቸው እስከተቋረጠበት ጊዜ ድረስ ባደረጉት ንግግር " ብልጽግና መራሹ መንግሥት ራሱ የፖለቲካ ችግር እየፈጠረ ነው" ብለዋል። "ፓርቲው የፈጠረውን የፖለቲካ ችግር ለመፍታት የሚሞክረው ከፖለቲካዊ መፍትሄ ይልቅ ወታደራዊ መፍትሄ ሆኗል" የሚሉት አቶ ገዱ ብልጽግና ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ…
Read More
የጸጥታ ሀይሎች በአማራ ክልል ሰላማዊ ዜጎችን መግደላቸው ተገለጸ

የጸጥታ ሀይሎች በአማራ ክልል ሰላማዊ ዜጎችን መግደላቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ሰላማዊ ዜጎች ከፍርድ ቤት ውጪ በአደባባዮች ላይ መገደላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ መግለጫ አውጥታል። ኮሚሽኑ በሪፖርቱ በአማራ ክልል ጎንደርና ሸዋሮቢት በርካታ አካባቢዎች ከፍርድ ቤት ትዕዛዘው ውጪ ሰላማዊ ሰዎች በፀጥታ ሀይሎች መገደላቸውን የሚያመላክቱ መረጃዎች እንደደረሱት ገልጻል። ተፋላሚ ሀይሎች ያለምንም ቅደመ ሁኔታ ግጭቶችን እንዲያቆሙ፣ ለሰላማዊ ንግግር ስፍራ እንዲያመቻቹና ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ኮሚሽኑ አክኖም በአማራ ክልል ያለው ግጭት በሰብዓዊ መብቶች ላይ እያሳደረ ያለውን ተፅዕኖ እየተከታተለ መሆኑን ገልጾ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመደንገጉ በፊትና በኋላ ከአዲስ አበባና ከሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መረጃዎችን እከተቀበለ እንደሆነም አስታውቋል። በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች…
Read More
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል የስድስት ወራት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጸደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል የስድስት ወራት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጸደቀ

የተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የውሳኔ ሀሳብን በአብላጫ ድምጽ በ16 ተቃውሞ እና በ12 ድምጽ ተአቅቦ ማጽደቁ ተገልጿል። የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት በአማራ ክልል እና እንደ አስፈላጊነቱ በሌሎችም ቦታዎች ተግባራዊ ይሆናል የተባለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጽደቁን ምክር ቤቱ በፌስቡክ ገጹ  አስታውቋል። የሚንስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል በትጥቅ የተደገፈ እንቅስቃሴ መኖሩን እና ይህንንም በመደበኛው የህግ ስርአት መቆጣጠር የማይቻልበት ሁኔታ መፈጠሩን በመግለጽ ነበር ለስድስት ወራት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የወሰነው። ምክር ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቦርድ አባላትን እና ሰብሳቢዎችንም መርጧል። በአማራ ክልል፣ በፌደራል መንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተፈጠው ግጭት ንጹሃን ሰዎች እንዲገደሉ ምክንያት መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት…
Read More
ጦርነት እና እግር ኳስ በኢትዮጵያ….

ጦርነት እና እግር ኳስ በኢትዮጵያ….

ቢኒያም ተክለወይኒ እባላለሁ። ትውልዴ ሽረ ነው። ከጦርነቱ በፊት የፕሪሚየር ሊጉ ተካፋይ የሆነው የስሑል ሽረ ዋና ቡድን ተጨዋች ነበርኩ ። ሊብሮ ነኝ ። አሰልጣኝ ዳንኤል ፀሐዬ ዋና አሰልጣኛችን ነበር ። ኳስ እወዳለሁ ። ደጉ ደበበን አደንቃለሁ ። እንደ እርሱ የመሆን ምኞት ነበረኝ ። ተቀራኒ ሆነን ተጫውተናልም:: በኳስ ጨዋታ መከላከልን እወዳለሁ ። አዳነ ሳላ አማኑኤልን ጨምሮ ከብዙ ጎበዝ አጥቂዎች ተፋጥጫለሁ ። ሁሉንም ገትሬ አቁሜያለሁ ። ቡድኔ ጎል እንዳይቆጠርበት በአግባቡ መምራት መከላከል ከስሑል ሽረ ጋር በፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን መሆን የዘወትር ህልሜ ነበር ። ከሽረ ውጭ ሌላ ክለብ አላውቅም ። በኳስ ጨዋታ መንገዴ የእራሴንም የቤተሰቦቼንም ህይወት መቀየር ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተመርጦ መጫወት የሌት ተቀን…
Read More
እስራኤል ከአማራ ክልል 200 ዜጎቿን ከኢትዮጵያ አጓጓዘች

እስራኤል ከአማራ ክልል 200 ዜጎቿን ከኢትዮጵያ አጓጓዘች

እስራኤል ከአማራ ክልል 200 የሚሆኑ ዜጎቿንና አይሁዳውያንን ማስወጣቷን አስታወቀች። የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚንስቴርና የጠቅላይ ሚንስቴር ጽ/ቤት በጋራ ባወጡት መግለጫ በክልሉ በተነሳው ግጭት 174 እስራኤላዊያንና ወደ ሀገሪቱ ለመግባት ብቁ የሆኑ ቤተ-እስራኤላዊያን ከጎንደር እንዲወጡ ተደርጓል። ሌሎች 30 የሚሆኑ ዜጎች ደግሞ ከባህር ዳር መውጣታቸው ተነግሯል።  በአራት በረራዎች ከአማራ ክልል እንዲወጡ የተደረጉት ዜጎች አዲስ አበባ ደርሰዋል ተብሏል። ከአዲስ አበባም ወደ እስራኤል ያቀናሉ ተብሎ ይጠበቃል። የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኢላይ ኮን እስራኤላዊያኑ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እስኪወስኑ ድረስ በአዲስ አበባ እንደሚቆዩ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ መቆየትም እንደሚችሉም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ እስራኤል ዜጎቿን የትም ይሁኑ የት ጥበቃ እንደምታደርግላቸው መናገራቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኸን ዘግቧል። ጠቅላይ ሚንስትሩ "አጭር፣ ኮሽታ…
Read More
አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

የተለያዩ አገራት በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ኹከትና የዜጎች ሞት እንዳሳሰባቸው ገለጹ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት ልዑክን ጨምሮ የተለያዩ አገራት ኤምባሲዎች ሰሞኑን በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ኹከት፣ የዜጎች ሞትና አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። የአውሮፓ ኅብረት ልዑክ በኢትዮጵያን እና የኦስትሪያ፣ የቤልጂየም፣ የቼክ ሪፖብሊክ፣ የዴንማርክ ፣ የፊንላንድ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርን፣ የሃንጋሪ፣ የአየርላንድ ፣ የኢጣሊያ፣ የሉክሰምበርግ፣ የማልታ፣ የኔዘርላንድስ፣ የሮማኒያ፣ የፖላንድ፣ የፖርቱጋል፣ የስሎቬንያ፣ የስፔን እና የስዊድን ኤምባሲዎች የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታን አስመልክተው የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡ በመግለጫቸውም በክልሉ የተቀሰቀሰው ኹከት፣ የዜጎች ሞትና አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው የገለጹ ሲሆን፤ ኹሉም ወገኖች ሲቪሎችን እንዲጠብቁ፣ ጉዳት ለደረሰባቸው ህዝቦች የተሟላ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ቀጣይነት ያለው ሰብአዊ ተደራሽነት እንዲረጋገጥ፣ የውጪ ዜጎች ከግጭቱ አካባቢ ለቅቀው እንዲወጡ እና ደህንነቱ በተጠበቀ…
Read More
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአማራ ክልል አምቡላንሶቹ ከጥቃት እንዲጠበቁለት ጠየቀ

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአማራ ክልል አምቡላንሶቹ ከጥቃት እንዲጠበቁለት ጠየቀ

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአማራ ክልል በተከሰተው ጦርነት እና ድጋፍ ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል። የማህበሩ ዋና ጸሀፊ አቶ ጌታቸው ተአ እንዳሉት በአማራ ክልል በተከሰተው ጦርነት የቆሰሉ ሰዎች፣ የተጠፋፉ እና ሌሎች ጉዳቶች የደረሰባቸው ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል ። በዚህም መሰረት የህክምና እና ሰብዓዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች ለመርዳት ቀይ መስቀል ማህበር ተሽከርካሪዎቹን በማንቀሳቀስ ላይ በመሆኑ ተፋላሚ ወገኖች ከጥቃት እንዲጠብቁት ማህበሩ ጥሪ አቅርቧል። በቀይ መስቀል ተሽከርካሪዎች የጦር መሳሪያ፣ ወታደሮችን እና ታጣቂዎችን ማጓጓዝ ክልክል መሆኑን የገለጸው ማህበሩ ዓላማችን ተጎጂዎችን መርዳት በመሆኑ ህብረተሰቡ ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ጥሪ አቅርቧል። አሁን ላይ የቆሰሉ ሰዎችን ለመርዳት በክልሉ የደም እጥረት እና የህክምና ቁሳቁስ እጥረት በማጋጠሙ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያሉ በጎ…
Read More
በአዲስ አበባ ግብረሰዶም ይፈምባቸዋል የተባሉ መዝናኛ ቤቶች ታሸጉ

በአዲስ አበባ ግብረሰዶም ይፈምባቸዋል የተባሉ መዝናኛ ቤቶች ታሸጉ

አዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በከተማዋ የግብረ-ሰዶም ተግባር በሚፈጸምባቸው ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። ፖሊስ እርምጃውን እየወሰደባቸው ያሉት ሆቴሎች፣ ባሮችና ሬስቶራንቶች ሲሆኑ ከአዲስ አበባ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር እንደሆነ ገልጿል። የተመሳሳይ ጾታ መዝናና ቤቶች ከነባሩ የሀገሪቷ ባህል፣ ወግ፣ የአኗኗር ስርዓት እና ኃይማኖቶች ባፈነገጠ መልኩ ወንጀሎች ይፈጸምባቸው ነበርም ተብላል። ፖሊስ የግብረ-ሰዶም ተግባር በሚያስፈጽሙ ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ ፔንሲዮኖችና መሰል የመዝናኛ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ከህብረተሰቡ ጥቆማ እንደደረሰውም አስታውቋል ። የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የግብረ-ሰዶም ተግባር መፈጸምና ማስፈጸም በኢትዮጵያ በሥራ ላይ ባሉ ሕጎች የተከለከለ ናቸው ብሏል። ፖሊስ የተመሳሳይ ጾታ መዝናኛ ቤቶች ባለቤቶች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየታጣራባቸው እንደሆነም አስታውቋል።
Read More
ወደ አሜሪካ ካቀናው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ሁለት ሰዎች መጥፋታቸው ተገለጸ

ወደ አሜሪካ ካቀናው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ሁለት ሰዎች መጥፋታቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቅርቡ ወደ አሜሪካ አቅንቶ ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን አድርጎ ተመልሷል። ፌዴሬሽኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአሜሪካ ቆይታን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ብሔራዊ ቡድኑ በአሜሪካ ቆይታው አላማውን እንዳሳካ የፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ባህሩ ጥላሁን በመግለጫው ላይ ተናግረዋል። የዲሲ ዩናይትድ ድርሻ ያላቸው አቶ እዮብ ማሞ ከፌዴሬሽኑ ጋር በጋራ ለመስራት በሚያስችል ሁኔታ ላይ በቅርቡ ከስምምነት እንደሚደርሱም አቶ ባህሩ ገልጸዋል። ለዚህም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በቅርቡ ወደ አሜሪካ በማቅናት ስምምነቱን ይፈፅማሉም ብለዋል። ከዲሲ ዩናይትድ ጋር የሚደረገው ስምምነት ኢትዮጵያዊያን ተጫዋቾች በዲሲ ዩናይትድ የመጫወት እድልን እንዲያገኙ እንደሚያስችል አቶ ባህሩ አክለዋል። ይሁንና የቡድኑ የትጥቅ ሀላፊ አቶ ሀይሉ አውግቼ እና የፊዚዮቴራፒ ባለሙያው…
Read More
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 ውድድር መርሀ ግብር ይፋ ሆነ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 ውድድር መርሀ ግብር ይፋ ሆነ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 የውድድር ዓመት የጨዋታ እጣ ድልድልበአዲስ አበባ ይፋ ሆኗል። በዚህ መሰረት ሀምበርቾ ዱራሜ ከድሬዳዋ ከተማ የመክፈቻ ውድድር ጨዋታውን የሚያደርጉ ሲሆን ሻሸመኔ ከተማ ከወላይታ ዲቻ፣ ሀዋሳ ከተማ ከፋሲል ከተማ የፊታችን መስከረም 20 ቀን 2016 ዓ. ም ያደርጋሉ። እንዲሁም አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ኢትዮጵያ መድህን ከከባህርዳር፣ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ ቡና፣ ሀዲያ ሆሳዕና ከመቻ የፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎችን ይጫወታሉም ተብሏል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ካምፓኒ ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሰይፈ በዕጣ አወጣጥ ስነ ስርዓቱ ላይ እንዳሉት ለተወዳዳሪ ክለቦች መልካም የውድድር ዓመት እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል። በ2015 የውድድር ዓመት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ስያሜ መብትን ቤትኪንግ ይዞ እንደነበር የገለጹት ስራ አስኪያጁ የ2016 የሊግ…
Read More